• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ዜጎች በጎጃም መሬቸውን እየተነጠቁ፤ በወለጋ ደግሞ እየተፈናቀሉ ነው!

April 28, 2014 06:30 pm by Editor Leave a Comment

አርሶ አደሮች መሬታቸውን ያለካሳ እየተነጠቁ ነው

መራዊ፡- በምዕራብ ጎጃም ዞን ሜጫ ወረዳ ያለ ፈቃዳችን መሬታቸውን አሳልፈን አንሰጥም ያሉ አርሶ አደሮች እስርና ድብደባ እየደረሰባቸው መሆኑን ከአካባቢው የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡ በመራዊ አካባቢ ሜጫ ወረዳ እናሸንፋለን ቀበሌ መንግስት የከርሰ ምድር ውሃ ቁፋሮ እናካሂዳለን በሚል ከ400 በላይ የሚሆኑ አርሶ አደሮች ከመሬታቸው እንዲለቁ የተደረገውን እርምጃ አርሶ አደሮቹ በመቃወማቸው እስርና ድብደባ እየደረሰባቸው መሆኑን የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ጠቁመዋል፡፡

በአካባቢው ከአሁን ቀደም ተመሳሳይ እርምጃዎች የተወሰዱ ሲሆን የአርሶ አደሮቹ መሬት በአበባ ኢንቨስትመንት ላይ ለተሰማሩ ባለሀብቶች ተሰጥቶባቸዋል፡፡ ይህም በአሁኑ ወቅት መንግስት ውሃ ለመቆፈር በሚል አርሶ አደሮቹ ከመሬታቸው እንዲለቁ የሚወስደው እርምጃ በተመሳሳይ ለአበባ እርሻ ሊሰጥባቸው እንደሆነ በማመናቸው ከመሬታቸው አንለቅም ብለዋል፡፡ እስካሁን ለአበባም ሆነ ለሌሎች ተግባራት መንግስት ከአርሶ አደሮቹ መሬት ሲወስድ ያለ ምንም ካሳ በመሆኑ አርሶ አደሮቹ አሁንም ቢሆን ያለ ካሳና ያለምንም ፈቃድ እየተነጠቁ በመሆኑ ተቃውሟቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ አድርጓዋል፡፡

ከአርሶ አደሮች ባሻገር በከተሞች የሚኖሩ የአርሶ አደሮቹ ቤተሰቦች ጭምርም ችግር እየደረሰባቸው መሆኑን ምንጮች ጨምረው ተናግረዋል፡፡ በተለይም ታሳሪዎቹን የሚጠይቁት የአርሶ አደሮቹ ቤተሰቦችና ሌሎች የአካባቢውና በየከተማው የሚኖሩ ግለሰቦችም ለእስር መዳረጋቸውን ለመረዳት ተችሏል፡፡ አርሶ አደሮቹ መሬታቸውን ያለ ፈቃዳቸው አሳልፈው እንደማይሰጡ በመግለጽ ጠንካራ ተቃውሞ ማንሳታቸውን ተከትሎ በአካባቢው ፖሊስና መከላከያ በብዛት መሰራጨቱን ምንጮች አክለው ገልጸዋል፡፡

በምስራቅ ወለጋ ዜጎች እየተፈናቀሉ ነው

በምስራቅ ወለጋ ስቡ ስሪ ወረዳ ‹‹ይህ አገር የእናንተ አይደለም፡፡ አገራችሁን ግቡ፡፡›› በሚል 200 ያህል አርሶ አደሮች እንደተፈናቀሉ አስታወቁ፡፡

በ1990ዓ.ም ጀምረው በአካባቢው የኖሩት እነዚህ ዜጎች ‹‹የመኖሪያ መታወቂያ ተሰጥቶን፣ውጡ ተብለን እየታሰርንና እየተባረርን እንኳ ግብር እያስከፈሉን፣ ንብረት አፍርተን አገራችሁ አይደለም ተብለን እየተፈናቀልን ነው›› ሲሉ ምሬታቸውን ለዝግጅት ክፍላችን ገልጸዋል፡፡ አርሶ አደሮቹ ከዚህ ቀደም በ1992 በተመሳሳይ ቤትና ንብረታቸው ወድሞ ተፈናቅለው የነበረ ቢሆንም መንግስት እንደገና እንዳቋቋማቸው ይገልጻሉ፡፡

‹‹በአንድ በኩል አገራችሁ አይደለም ውጡ!›› የሚሉት የአካባቢው ባለስልጣናት በሌላ በኩል ደግሞ ‹አካባቢውን ልንሰራበትና ልናሰራበት ነው ይሉናል፡፡ በ1992ም መንግስት እንደገና አቋቁሞናል፡፡ አሁንም ቦታው ከተፈለገ መንግስት ተገቢውን ካሳ ሊሰጠን ይገባል፡፡› ብለን ስንጠይቅ ደግሞ ‹እናንተን መንግስት አያውቃችሁም፡፡ ይሉናል› በሚል እየደረሰባቸው ያለውን ህገ ወጥ ተግባር ይናገራሉ፡፡

ተፈናቃዮቹ ከጥር 22 2006 ዓ.ም ‹‹ለቃችሁ ውጡ፡፡ ለቃችሁ ካልወጣችሁ ለቤትና ንብረታችሁ ብቻ ሳይሆን ለህይወታችሁም ኃላፊነት የላችሁም›› መባላቸውን ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ተደጋጋሚ እስራትና ድብደባ እንደደረሰባቸው ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

‹‹ለቃችሁ ውጡ!›› በተባሉበት ወቅት አቤቱታ ሲያቅረቡ የነበሩ 42 ሰዎች ያለ ምንም ምግብ ለ30 ቀናት ታስረው መቆየታቸውንና በየጊዜው ፖሊስ ከፍተኛ ድብደባ እንደሚያደርግ ገልጸዋል፡፡ ከቀያችን ተፈናቅለን፣ ልጆቻችን ትምህርታቸውን አቋርጠው፣ በችግር ላይ እንገኛለን የሚሉት ተፈናቃዮቹ ‹‹ሀገርና ተቆርቋሪ የሌለን ዜጎች ሆነናል፡፡ ከ16 አመት በላይ የኖርንበትን ቀያችን ለቀን ወደ የት እንሂድ? የሚመለከታችሁ አካላት ሁሉ በተግባር እርዱን›› ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ (ምንጭ፡ ነገረ ኢትዮጵያ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm
  • “ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንግቤ እዋጋለሁ” የሚሉ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል – የመከላከያ ሠራዊት August 1, 2023 09:25 am
  • ደቡብ አፍሪካ የመሸጉ ወንጀለኞች ለሕግ ተላልፈው ሊሰጡ ነው July 31, 2023 09:27 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule