• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን?

August 27, 2014 04:48 pm by Editor Leave a Comment

“የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን” የኢትዮጵያ ሬድዮና ቴሌቪዥን የሚለውን ቃል ለምን በትእምርተ ጥቅስ እንዳስቀመጥኩት የገባችሁ ይመስለኛል፡፡ ጣቢያው ስሙ እንደሚጠቁመው የሀገር የብዙኃን መገናኛ ሳይሆን እራሳቸውን በመንግሥት ስም ያደራጁ በአብዛኛው ከሀገርና ከሕዝብ ጥቅም ተፃራሪ የሆነ ጥቅም ፍልጎትና ዓላማ ያለው ቡድን ዓላማ ማራመጃ ከሆነ ዐሥርት ዓመታት አልፏልና ነው መትእምርተ ጥቅስ ማስቀመጤ፡፡

ይህ የብዙኃን መገናኛ ሕግና ሕዝብ እንዲሆን የሚጠብቀው ነገር ግን የመንግሥት (የሕዝብ) መሆን ያልቻለው ብሔራዊ የቴሌቪዥንና ሬዲዮ (የምርአየ ኩነትና የነጋሪተ ወግ) ጣቢያ ትናንትና በ19-12-2006 ዓ.ም. የግል የኅትመት የብዙኃን መገናኛዎችን በተመለከተ “ያልተገሩ ብዕሮች” በሚል ርእስ ዘጋቢ ፊልም ሲል በሠየመው ዝግጅት ዝግጅቱ ምንም እንኳን ዘጋቢ ፊልም (ምትርኢት) ለመሰኘት የሚያበቃውን ሞያዊ መስፈርት (discipline) የያዘ ፊልም (ምትርኢት) ባይሆንም ባለሞያ በሌለበት ቤት ይህ ይሆናል ብለን አንጠብቅምና ብቻ ግን ሊሉ የፈለጉትን ነገር ባይሉም ሊሉ የፈለጉት ነገር ገብቶናልና በቀረበው ዝግጅት ላይ ከ1 ብሔራዊ የብዙኃን መገናኛ ፈጽሞ በማይጠበቅ የወረደ አዘገጃጀት ወይም ደረጃ ከወትሮአቸው የተለየ ባይሆንም በእውነት አሳፋሪ የሆነ ፍጹም ጭፍን እና ሚዛናዊነት የጎደለው ዝግጅት አቅርቦ ነበር፡፡ ነገሩ “አመድ በዱቄት ሲስቅ” ዓይነት ነው የሆነብኝ፡፡

ስለ እውነት ከሆነ ይህንን ዝግጅት ያዘጋጁ ሰዎች ጭንቅላት ያላቸው ቢሆኑና ለሞራል (ለቅስም) ሕግጋት ተገዥ ቢሆኑ ኖሮ “እኛስ ማን ነንና” በሚል ተገቢ የኅሊና ጥያቄ ጣታቸውን በሌላ ላይ ለመጠቆም ባልደፈሩም ነበር፡፡ ነገር ግን እጅግ በሚያሳዝን ሁኔታ ሰዎቹ ከሰብእናቸው አኳያ ይህ የኅሊና ጥያቄ ጨርሶ የሚሰማቸው አይደሉምና እነሱም በብዙ ጊዜ እጥፍ የረከሱበትን ጉዳይ በሌሎች ላይ ሲያነሡ ቅንጣት እንኳን አልሰቀጠጣቸውም ፡፡ ይህ እነሱ በግሉ የኅትመት የብዙኃን መገናኛዎች ላይ ያነሡትን ጥያቄ ለጣቢያው ቢነሣበት ምን ያህል በስንት ጊዜ እጥፍ ቀለው እንደሚገኙ አሳምሮ ለሚያውቀው ለኢትዮጵያ ሕዝብ ለማቅረብ መድፈራቸው የሚያሳየው ነገር ቢኖር ወይ የሰዎቹን ጤነኛ አለመሆን፣ ወይ ድንቁርናቸውን፣ ወይ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ያላቸውን ንቀት ካልሆነ በስተቀር ሌላ ሊገልጽ የሚችለው አንዳችም ቁምነገር የለም፡፡

ይህ ዝግጅት የግሉን የብዙኃን መገናኛ

  1. በፈጠራ ወሬ
  2. ሚዛናዊ ባለመሆን
  3. በስም ማጥፋት
  4. የሀገርንና የሕዝብን ጥቅም ለአደጋ በመዳረግ ወንጀሎች ከሷል ፡፡

ስለእውነት ጊዜና ቦታ አይበቃንም እንጅ እነዚህን እያንዳንዳቸውን ክሶች በመጥቀስ ጣቢያውን ከሀገርና ሕዝብ ጥቅም በተፃራሪ ወይም የተለየ የራሳቸው ጥቅም ፍላጎትና ዓላማ ያለውን ቡድን ጥቅም ፍላጎትና ዓላማ ለማስጠበቅ ጣቢያው በአሁን ሰዓት በሕዝብ ዘንድ ያለው አመኔታ “መቸም አታምኑንም አሁን ሰዓቱ ከምሽቱ 2 ሰዓት ሆኗል” ተብሎ በሚገለጽበት ደረጃ ደርሶ ምን ምን ዓይነት የፈጠራ ወሬዎችን ሲነፋብን እንደኖረና እንዳለ፣ ሚዛናዊነት የሚባል የሞያው ደረጃ መኖሩን ቃሉን እናኳን ጨርሶ ሰምተው የሚያውቁ እስከማይመስሉበት ድረስ የሕገ መንግሥታቸውን ድንጋጌዎች አሽቀንጥረው በመጣል ፍጹም ኢፍትሐዊ የሆነ የአንድ ወገን ወይም የቡድን ጥቅም ፍላጎትና ዓላማ መንዣ ወይም ማራመጃ እንደሆነ፣ የስንት ዜጎችን ክብርና ማንነት ከብዙኃን መገናኛ ፈጽሞ በማይጠበቅ ሁኔታ ኢትዮጵያዊ ባለሆነና በማናውቀው ባእዳዊ ሥነምግባር በጎደለው አቀራረብና ሰብእና ስም እንዳጠፋ ክብር እንዳጎደፈ፣ የሀገራችንን እና የሕዝቧን ብሔራዊ ጥቅምና ሉዓላዊነት የጎዱ ያጠፉና ለአደጋ የዳረጉ ለማፈራረስ ለማባላት ያሴሩ የጥፋት ፕሮፖጋንዳዎችን (ልፈፋዎችን) እና መርዘኛ ስብከቶችን ለመርጨት በምን ያህል የጠላትነት ስሜትና የሞራል (የቅስም) የሞያ ዝቅጠት ወርዶ እንደረከሰባቸው እንደፈጸማቸው አሳምረን መተንተን በቻልን ነበር ፡፡

የመንግሥት (የሕዝብ) የብዙኃን መገናኛዎች ምርጫ ደረሰም አልደረሰ ኖረም አልኖረ ተቃዋሚ ወይም ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች (የእምነተ አስተዳደር ማኅበራት) አማራጭ ፖሊሲዎቻቸውን (መመሪያዎቻቸውን) እና የፖለቲካ (የእምነተ አስተዳደር) አስተሳሰብ አመለካከታቸውን ያለ ምንም ቅድመ ሆኔታዎችና ክልከላ ለሕዝብ ማድረስ እንዲችሉ ወይም እንዲያስተናግዱ ሕገመንግሥታዊ ግዴታ ተጥሎባቸው ነበር፡፡ መሬት ላይ ያለው ሀቅ ግን እንኳን የፖለቲካ ፓርቲዎች ዘፈኖችን አንኳን ሳይቀር ደጋፊነቱ በግልፅ የማይታወቅ ዘፋኝ ዘፈን የማይደመጡበትና የማይስተናገዱበት  ደረጃ ላይ ደርሰናል፡፡ ደጋፊ አለመሆኑ ወይም ተቃዋሚ መሆኑ የታወቀ ዘፋኝ ዘፈን ከሆነማ ዘፈኑ መደመጡ ወይም መስተናገዱ ጨርሶ የማይታሰብ ነው፡፡ ይህ አሠራር ግን ፍጹም ሕገ ወጥ ነው፡፡ አገዛዙ ይሄንን ማድረግ የሚችለው ወይም መብቱ ያለው እንደ ሬዲዮ ፋና ባሉ የራሱ የሬዲዮ (የነጋሪተ ወግ) ጣቢያዎቹ እንጅ በመንግሥት(በሕዝብ) የብዙኃን መገናኛዎች አልነበረም፡፡ ነገር ግን ሕግ አይገዛቸውምና ያለ አንዳች መሳቀቅ ይሄንን ሕገ ወጥ ድርጊት የገዛ ሕገ መንግሥታቸውን በመጻረር መንቀሳቀሳቸውን በሰፊው ተያይዘውታል፡፡ እንግዲህ ይህ የሕዝብ (የመንግሥት) የብዙኃን መገናኛ ከገዛ ሕገ መንግሥታቸው ድንጋጌ በተፃራሪ ከስሙ በስተቀር ከመንግሥት (ከሕዝብ) ንብረትነት ወጥቶ የቡድን መጠቀሚያና ንብረት አድርገው እንዴት እየተገለገሉበት እንዳሉ በግልፅ ማየት ይቻላል፡፡

ከእርሰ ጉዳችን ያወጣናል እንጅ ይህ ጉዳይ ማለትም ከሕግ ውጭ ከመንግሥት (ከሕዝብ) ንብረትነት እጅ ወጥቶ የቡድን አድርጎ የመጠቀሙን ነገር በብዙኃን መገናኛው ላይ ብቻ የቆመ አይደለም፡፡ ሀገሪቱን ጨምሮ የመንግሥት (የሕዝብ) ንብረት የሆኑ ተቋማትን ሁሉ ያጠቃልላል፡፡ በትምህርት ተቋማት ዜጎች መሠረታዊ ከሆኑ ከዜግነት መብቶቻቸው አንዱ የሆነውን ያለምንም ልዩነት የመማር መብት ተነፍገው  በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት አባል ካልሆናቹህ መማር አትችሉም ተብሎ ምን ዓይነት ግፍ እየተሠራ እንደሆነ የምናየው ነገር ነው፡፡ ወያኔ ይህን ማለት ይችል የነበረው በራሱ በግሉ በፓርቲው የግል ገንዘብ ያሠራው የትምሕርት ተቋም ቢኖር ኖሮ ነው እንጅ በኢትዮጵያ ሕዝብ ገንዘብ በተገነቡት አልነበረም፡፡ በገሀድ እያየነው ያለነው ጉድ ግን ለምን! አይሆንም! የሚላቸው መብቱን ጠያቂ ሕዝብ ስለሌለ ሌላው ቀርቶ የእምነት ተቋማት እንኳን ከሀገርና ከሕዝብ ንብረትነት ወጥተው የቡድኑ ንብረት እንዲሆኑ በመደረጋቸው የቡድኑን ኢፍትሐዊ ጥቅም እንዲያስጠብቁ ተደርገዋል፡፡ ስለእውነት ከሆነ ይህ ሕዝብ በታሪኩ እንደዚህ ዘመን የተናቀበት የተዋረደበት የተደፈረበት መጫወቻ መቀለጃ የሆነበት ዘመን አፍን ሞልቶ ከቶውንም የለም አልነበረም ማለት ይቻላል፡፡ ለዚህ ሁሉ ውርደት ንቀትና መደፈርም ግንባር ቀደም ተጠያቂው እራሱ ሕዝቡ እንደሆነ አስባለሁ፡፡

አሁን የመንግሥት (የሕዝብ) የብዙኃን መገናኛዎች እጅግ በባሰ ሁኔታ እያጠፉ ስለሆነ የግሎችም የማጥፋት መብት አላቸው እያልኩ አይደለም ያለሁት፡፡ እዚህም እዛም ስሕተት ይኖር ይሆናል ከስሕተት የጸዳ ነገር የለምና፡፡ እኔ እያልኩ ያለሁት እንደ ስሕተት የተቆጠሩባቸው ነገሮች 95% በላይ ወይ ያልተደረጉ አልያም ስሕተት ተደርጎ ሊቆጠር የማይገባ ነው፡፡

በየትኛውም ሀገር ማየት እንደሚቻለው የግል ብዙኃን መገናኛዎች ማለት አማራጭ የብዙኃን መገናኛዎች ናቸው፡፡ ይህም ማለት በመንግሥት የብዙኃን መገናኛዎች በተለያየ ምክንያት ሽፋን የተነፈጋቸውን ወይን እንዲስተናገዱ ላልተፈለጉት ለሕዝብ ለሀገር ለዜጎች ጉዳዮች ሽፋን በመስጠት በአማራጭነት ሕዝብን ማገልገል ማለት ነው፡፡ አለዛማ ማለትም የመንግሥት የብዙኃን መገናኛዎች ተቀይደው ተይዘው የሚያወሩትን ለመድገም ከሆነ የግል የብዙኃን መገናኛዎች ምን ጥቅም ሊኖራቸው ይችላል? ምንም ዓይነት ፋይዳ አይኖራቸውም “መንግሥት” እንዲባልለት የፈለገውን ነገርማ በተሻለ አቅም የመንግሥት (የሕዝብ) የብዙኃን መገናኛዎች ይከውኑታልና፡፡ ውስን የሆነውን የሀገርና የሕዝብን ሀብትና ንብረትን ከማባከን ውጭ ምንም የሚተክሩት ነገር የለም፡፡ በመሆኑም አገዛዙ ሐሳብን ያለገደብ በነፃነት የመግለጽ ሕገመንግሥታዊ መብት ሰጥቻለሁ እያለ የግል የብዙኃን መገናኛዎችንም ሕገ ወጥ በሆነ ምንገድ ጨምድዶ ይዞ እየተጠቀመባቸው አንዳለው የመንግሥት (የሕዝብ) የመገናኛ ብዙኃን ሁሉ በአንድ ዓይነት ወይም በተመሳሳይ ቅኝት ሥሩ ብሎ ሊያስገድድ የሚችልበት አንድም ዓይነት ሕጋዊ መሠረት ያለው አሠራር ጨርሶ እንደሌለ ሕዝብ እንዲያውቀው እወዳለሁ፡፡

እዚህ ላይ በአማራጭ ድምፅነት ሊያገለግሉ የሚችሉት የግል የብዙኃን መገናኛዎች ብቻ ላይሆኑ ይችላሉ፡፡ እንደ የአሜሪካ ድምፅ እና ዶቸቨሌ ያሉ የሰብአዊ እና የዴሞክራሲያዊ (በይነሕዝባዊ) መብቶች ጉዳይ ይገዱናል ያገቡናል ያሳስቡናል የሚሉ መንግሥታት የሬዲዮ (የነጋሪተወግ) ጣቢያዎችም በአማራጭ ድምፅነት ሊያገለግሉ ይችላሉ፡፡ እራሳቸውን እንደሚገልጹትም የተመሠረቱት የኢትዮጵያን ሕዝብ በአማራጭ ድምፅነት ማለትም “ከመንግሥት” የብዙኃን መገናኛዎች የማያገኘውንና ሊያገኘው የማይችለውን መረጃ ለመስጠት እና ለማገልገል ነው፡፡

ይሁን እንጂ እነዚህ ሁለት የብዙኃን መገናኛዎች በጣት ከሚቆጠሩ ዓመታት ወዲህ በተለይም የአሜሪካ ድምፅ በረጅሙ የወያኔ እጅ አቅማቸው ተዳክሞና እጃቸውን ተጠምዝዘው ቀድሞ የነበራቸው ጥንካሬ ትጋትና አቅም ድራሹ ጠፍቶ የነበራቸው ክብርና ሞገስ ተደማጭነትና ተአማኒነት እያሽቆለቆለ አማራጭነታቸው ቀርቶ አገዛዙ በሕገወጥ መንገድ እየተጠቀመባቸው እንዳሉት የመንግሥት (የሕዝብ) የብዙኃን መገናኛዎች ስለአገዛዙ የሚደሰኩሩትን መልሰው የሚያስተጋቡ ለመሆን ተገደዋል፡፡

በዚህ ዘጋቢ ፊልም (ምትርኢት) በጅምላ የተከሰስነው የተወነጀልነው የግል የኅትመት የብዙኃን መገናኛ ብዙኃን ጸሐፍትና ጋዜጠኞች ምን ምን ዓይነት አጸያፊና ዘግናኝ የግፈኞችንና የአንባገነኖችን ሰቆቃና ግፍ በመጋፈጥ በሚቀፍ በሚዘገንን ማስፈራሪና ዛቻ ሥጋትና ሰቀቀን ውስጥ በማለፍና ዋጋም በመክፈል ሥራው እንደሚሠራ ቀን ወጥቶልን ፍትሕ ሰፍኖልን እስኪሰማ ድረስ ምሬቱንና መቅፈፉን ሊገምት የሚችል ዜጋ መኖሩን እጅግ እጠራጠራለሁ፡፡ ይህ ሁሉ እናት ሀገራችንንና ተወዳጅና የሚያሳዝን ሕዝቧን ከገቡበት ማጥ ለማውጣት ልጆቿ የግድ የሚከፍሉት ዋጋ በመሆኑ ይሄው ዐይናችንን አፍጥጠን ተጋፍጠናል፡፡ ከእነዚህ አገዛዙ ከሚፈጥራቸው ጫናዎች መሰናክሎች ወከባዎች ጋር መሥራት ምን ያህል ፈታኝ እንደሆነም መገመት አያዳግትም፡፡ የግሉ የኅትመት የብዙኃን መገናኛ ይሄ ሁሉ ጉድ እያለበት ወያኔ እንዳቀረበብን ክስ ሁሉ እሱም በጅምላ በመኮነን ክስና ወቀሳ የሚያቀርብ አካል ካለ በእውነት ማስተዋልና ማገናዘብ የተሳነው የዜግነት ኃላፊነትና ግዴታ የማይሰማው የማይገደው በመሆኑ በራሱ እጅግ ሊያፍር ይገባል፡፡ በጣምም እናዝናለን፡፡

ወያኔ እንደምንም ብሎ ሀገሪቱ ሌሎች የዜግነት ግዴታቸውን የተረዱ ዋጋ ቢያስከፍልም ግድ መሆኑን የተረዱ ደፋር ጋዜጠኞችንና ጸሐፍትን እስክታፈራ ድረስ ሰሞኑን በቀረበባቸው ከባድ ክስ ምክንያት ሳይወዱ በግድ ተሰደው የተለዩን ወንድሞችን ለመተካት ዓመታትን ማስቆጠራችን ግድ መሆኑ አይቀርም፡፡ ወንድሞች ሆይ! ስለተለያቹህን ኃዘኔ እጅግ የበረታ ነው ነጻ ሆነን የምንገናኝበት ቀን ሩቅ እንደማይሆን ተስፋየ የጸና ነው፡፡

ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው
ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው

ወያኔ በግል የብዙኃን መገናኛዎች የወሰደው እርምጃ የለየለትና ዐይን ያወጣ አምባገነንነት ነው፡፡ ሕዝባችን ይህንን ኢፍትሐዊና አምባገነናዊ እርምጃ በምንም ዓይነት በዝምታ ሳትመለከት በፍጥነት መብቶችህን በእጅህ እስክታስገባ ድረስ  ለትእግሥትህ ልክ በማበጀት ይህንን  የበሰበሰ ግፈኛ አገዛዝ በቃህ! ማለት አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው፡፡

አገዛዙ ይህንን የሚያደርግበት ብቸኛው ምክንያት ከጊዜ ወደጊዜ እየከፋ እየተባባሰ የመጣውንና የሚሄደውንም ግፍ፣ ሙስና፣ በደል፣ የሀገር ክህደት ወንጀሎች እንዳይገለጡ እንዳይጻፉ እንዳይታወቁ እና ወደአንተ እንዳይደርሱ ለማድረግ ነውና፡፡ ይህንን ልትታገስ አይገባም፡፡ ካልሆነ ግን ያለ አባትህ ባርነትህን አምነህ እንዳረጋገጥክላቸው ዕወቀው፡፡ በዚህም የከፋ ቀን እንጂ የተሻለ ቀን እንደማይመጣ ላረጋግጥልህ እወዳለሁ፡፡ታዲያ ፍላጎትህ ይህነውን?

ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!!!

 

amsalugkidan@gmail.com

(ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule