• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በሳውዲ የኢትዮጵያዊቷ የደመወዝ ጥያቄ ሽጉጥ አስመዘዘ

February 17, 2015 09:30 am by Editor Leave a Comment

ሳውዲ አረቢያ ቢሻ እየተባለ የሚጠራ አነስተኛ ከተማ ውስጥ አንዲት ኢትዮጵያዊት የቤት ሰራተኛ በሳውዲያዊ አሰሪዋ ከተተኮሰባት ጥይት ከሞት መትረፏን ምንጮች አረጋገጡ። በዚህች ኢትዮጵያዊት ላይ ስለደረሰው የነፍስ ማጥፋት ጥቃት በኢህአዴግ ተመልምለው የተሰየሙት ዲፕሎማቶች ምንም ዓይነት መረጃ የላቸውም፡፡

አደጋው የደረሰባት ወጣት በ20ዎቹ የዕድሜ ክልል ውስጥ መሆኗን የሚናገሩ የዜናው አቀባዮች ወጣቷ  እንደተራራ የገዘፈውን ህይወት በመጋፈጥ ቤተስቦቿን ከችግር ለመታደግ በወቅቱ ከነበሩ የኤጀንሲ ደላላዎች ጋር ተዋውላ ሳውዲ አረቢያ ለስራ መምጣቷን ይናገራሉ።

በተጠቀሰው ውል መስረት ወጣቷ አሰሪዋ የወር ደሞዝዋን በየወቅቱ እንዲከፍላት ለማስረዳት ብትሞክረም ከኢትዮጵያ ከመጣች ጀምሮ ላለፉት ሁለት አመት ያለደሞዝ ለመቆየት መገደዷን ለመረዳት ተችሏል። ሰሞኑን ኢትዮጵያዊቷ የቤት ሰራተኛ የሁለት አመት ኮንትራት ውሏን መጨረሷን ተከትሎ አሰሪዋ ደሞዝዋን በአግባቡ አስቦ እንዲከፍላት ጥያቄ ብታቀርብም በንግግሯ የተበሳጨው ሳዑዲያዊ ከመሳቢያ ሽጉጥ በማውጣት ኢትዮጵያዊቷን የቤት ሰራተኛ ለመግደል አከታትሎ እንደተኮሰባት  የሚናገሩ እማኞች ወጣቷ በሁለት ጥይት ተመታ እንደወደቀችና  በአካባቢው ሰዎች ትብብር በተለምዶ መሊክ አብደላ እየተባለ ወደሚጠራ  ሆስፒታል በመውሰድ ህይወቷን ለማትረፍ ተችሏል ብለዋል።

eth woman in saudi1ጅማ ውስጥ ተወልዳ እንዳደገች የሚነገርላት ይህች ወጣት ሳውዲ አረቢያ ውስጥ ጉዳዩን የሚከታተልላት ዘመድና ቀባሪ የሌላት በአሰሪና ሰራተኛ አገናኝ ኤጀንሲ ደላሎች እምነት ጥላ የሳውዲ አረቢያን ምድር ከረገጠች ወዲህ ከማንም ጋር በቴሌፎንም ሆነ በአካል እንዳትገናኝ በአሰሪዎችዋ ጥብቅ ቁጥጥር ይደረግባት ስለነበር ወጣቷ ከሃገር ይዛ የመጣቸው የቤተሰቦችዋ የስልክ አድራሻ በአሰሪዎቿ በመነጠቁ ረዳት የሌላቸውን እህት ወንድሞቿን መርዳት ቀርቶ በህይወት መኖራቸውን እንኳን በትክክል እንደማታውቅ ይነገራል።

በአሰሪዋ ጥይት ህይወቷ ከመነጠቅ ተርፋ ሆስፒታል የገባችው ኢትዮጵያዊት ወጣት በአሁኑ ሰአት ያለችበትን የጤንነት ሁኔታ የሆስፒታሉ የምርመራ ውጤት በትክክል ባይገልጽም የጥይት አረሩ ከሰውነቷ መውጣቱን ማረጋጋጥ ተችሏል። ወንጀሉን የፈፀመው ሳዑዲያዊ አሰሪ ላይ ምንም አይነት እርምጃ ባለመወሰዱ ወጣቷ ሊገለኝ ይችላል በሚል ስጋት በጭንቀት እንቅልፍ  በማጣት ላይ መሆኗን እና “ከሆስፒታል አውጡኝ፤ ሃገሬ ውስዱኝ” እያለች በኦሮምኛ ቋንቋ ስትማጽን ተሰምታለች።

የኢትዮያዊቷን ትክክለኛ የሃገር አድራሻ ለማወቅ አስሪዋ ፓስፖርቷን እንዲሰጥ ቢጠየቅም እስካሁን ፈቃደኛ አለመሆኑ ከአካባቢው የመጡ መረጃዎች ጠቁመዋል። ይህ ዜና እስከ ተጠናከረበት ጊዜ ድረስ ለዜጎች ህይወት ደንታ የሌላቸው ሪያድ እና ጅዳ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ዲፕሎማቶች አደጋ ስለደረሰባት ወጣት ምንም አይነት መረጃ እንደሌላቸው ማረጋገጥ ተችሏል።

ቀደም ሲል በኤጀንሲ ደላሎች  ወደ ሳውዲ አረቢያ ከገቡ በመቶ ሺህ ከሚቆጠሩ እህቶች ውስጥ ገሚሱ የወር ደሞዛቸው በአሰሪዎቻቸው ተነጥቆ ግፍ እና በድልን ተሸክመው ለአገራቸው ሲበቁ ቁጥራቸው በውል የማይታወቅ ዜጎች ሳውዲ ውስጥ ያሉበትን ሁኔታ በትክክል መግለጽ እንደማይቻል ይነገራል፡፡

ይህ በዚህ እንዳለ ከወራት በፊት ወደ ሳውዲ አረቢያ ለጉብኝት መጥተው እንደነበር የሚነገርላቸው አፈጉባዔ አባዱላ በኮንትራት ሰራተኞች ዙሪያ ከሳውዲ አረቢያ መንግሥት ባለስልጣናት ጋር ለመነጋገር ያደረጉት ሙከራ እንዳልተሳካ የሚገልጹ ታዛቢዎች የዜጎችን መብት የሚያስክብር ሁለትዮሽ «ኦፊሴላዊ» የጋራ ውል በሌለበት የኮንትራት ሰራተኞችን ወደ አረብ ሃገራት ለመላክ ለተወካዮች ምክርቤት እንደሚቀርብ የሚጠበቀው የሰራተኛ እና አሰሪ አገናኝ ረቂቅ ህግ ሃላፊነት የጎደለው ከዜጎች መብትና ጥቅም ይልቅ ቱባ ባለስልጣናትንና ተላላኪዎቻቸውን ኪስ ክቡር በሆነው የዜጎቻች ህይወት ለማደለብ የሚደረግ ሩጫ መሆኑን በጉዳዩ ላይ ቅርበት ያላቸው አስተያየት ሰጪዎች ይናገራሉ።

Ethiopian Hagere Jed BewadI ለጎልጉል የላኩት

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule