• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኢትዮጵያ ውስጥ የስፖርት ጋዜጠኛ ወይስ ተርጓሚ ነው ያለው?

February 6, 2015 06:43 am by Editor Leave a Comment

“የምን ማራዶና የምን ፔሌ ፔሌ 

እኛም አገር አለ ገብረመድኅን ኃይሌ”

ደምሴ ዳምጤ ጎልታ የምትጠቀስለት መንቶ ግጥሙ ነበረች፡፡ ለአገሪቱ ስፖርት ዕድገት በተለይም እግር ኳሱ እንዲያብብ በሙያው ያደረገው ጥረት ኢትዮጵያውያን ተጫዋቾች ክሂላቸው ከማንም እንደማያንስ በማንፀባረቅ ነበር፡፡ በ1970ዎቹ መጨረሻና በ80ዎቹ መጀመርያ ጎልተው ወጥተው የነበሩት እነሙሉጌታ ከበደ፣ ሙሉጌታ ወልደየስ፣ ገብረመድኅን ኃይሌን ሲያወድስ ገጣሚ ሆኖ በመገኘት ነበር፡፡

ስፖርት እንደ አንድ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊ እና ምጣኔ-ሃብታዊ ጉዳይ ራሱን የቻለ ሰፊ ርዕሰ ጉዳይ እየሆነ የመጣ ሲሆን ሊሰጠው የሚገባው ግምትም ያን ያህል እየከበደ መጥቷል፡፡ በመሆኑም እነዚህን ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊ እና ምጣኔ-ሃብታዊ ጉዳዮች ብቻ የሚተነትኑ የተለያዩ መገናኛ ብዙሃን እንዳሉ ሁሉ ስፖርታዊ ጉዳዮችን ብቻ የሚተነትኑ ጋዜጦች፣ ሬድዮኖች፣ የቴሌቪዥን ጣቢያዎች፣ ድረ-ገጾች እና ሌሎች መገናኛ ብዙሃን በርካታ ናቸው፡፡

በአሁኑ ወቅት በሃገር ቤት እየተተገበረ ያለው የስፖርት ጋዜጠኝነት ምን ያህል ሙያዊ እና ስነምግባራዊ ነው ለሚለው እኔም በርካታ አሉታዊ አስተያየቶች አሉኝ፡፡

eth football team1በአብዛኛው ለሃገርቤት መገናኛ ብዙሃን ስፖርት ማለት የእግር ኳስ ጨዋታ ሆኗል ያውም የአውሮፓ ክለቦች የእግር ኳስ ጨዋታ፡፡ የእግር ኳስ ጨዋታ ካለው አዝናኝነት፣ ከተመልካቹ ብዛት እና ከሚያንቀሳቅሰው ከፍተኛ ገንዘብ አንጻር በጋዜጣ ላይ የሰፋውን ቦታ እና በሬድዮ እና ቴሌቪዥን ጣቢያዎች ላይ ደግሞ የበዛውን የአየር ሰዓት ቢይዝ የጎላ ጥያቄ ላያስነሳ ይችላል፡፡ ሆኖም በእኔ ዳሰሳዊ ግምት በተለያየዩ የኤፍ ኤም እና የኤ ኤም ሬድዮ ጣቢያዎች ከሚቀርቡ የስፖርት ዝግጅቶች ብዙውን ግዜ ሙሉ በሙሉ ሊባል በሚችል ሁኔታ እና አንድ አንድ ግዜ ከዘጠና በመቶ በላይ የእግር ኳስ ጉዳይ የሚተነተን ሲሆን ከዚህም የሚበዛው የአውሮፓ የእግር ኳስ ክለቦች ጨዋታ ጉዳይ ነው፡፡

ይህ የሆነበት ምክንያት በተለያዩ ጉዳዮች ተፅዕኖ ሊሆን ይችላል አንደኛ የእግር ኳስ በተለይም ደግሞ የአውሮፓ ክለቦች የእግር ኳስ ጨዋታ ከሌሎች ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች የተሻለ አዝናኝ ነው ተብሎ ስለሚገመት፤ ሁለተኛ በሃገር ውስጥ አብዛኛው የስፖርት አድናቂ ማህበረሰብ የእግር ኳስን በተለይም ደግሞ የአውሮፓ ክለቦች የእግር ኳስ ጨዋታን የበለጠ ይወዳል ተብሎ ስለሚገመት፣ ሦስተኛ ደግሞ በተለይ ከአውሮፓ ሃገራት መገናኛ ብዙሃን የሚለቀቁ እጅግ ብዛት ያላቸው እና የየክለቦቻቸውን ሁኔታ የሚተነትኑ መረጃዎች በተትረፈረፈ ሁኔታ ማግኘት መቻሉ የጋዜጠኞችን ትኩረት በመሳቡ ሊሆን ይችላል፡፡ በእነዚህም ሆነ በሌሎች ምክንያት የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን የአውሮፓ ክለቦችን የእግር ኳስ ጨዋታ ተንታኝ ሆኗል፡፡

ዋናው ርዕሰ ጉዳይ ተረስቶ ከጨዋታው ጋር የማይያያዙ ጉዳዮች በበለጠ ትኩረት ሲዘገቡ ይስተዋላል፡፡ እከሌ የተባለው አንድ የአውሮፓ ክለብ ተጫዋች የሴት ጓደኛ ስትደሰት እና ስትበሳጭ ምን እንደምታደርግ ጠቀመውም አልጠቀመውም ለኢትዮጵያዊ ስፖርት ተከታታይ ይቀርብለታል፡፡ አሁንም ጠቀመውም አልጠቀመው ስለተጫዋቹ አባት፣ እናት እና ሌሎች ዘመዶች ማንነት እና ምንነት እንዲያነብ ወይንም እንዲያዳምጥ ይደረጋል፡፡

የእኛ ሐገር የስፖርት ጋዜጠኞች በተደጋጋሚ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን ሊያሠለጥኑ በሚመጡ የውጭ ሐገር አሠልጣኞች ጭምር መሣለቂያ ሆነዋል የቅርቡን ብናስታውስ እንኳን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በማሊ ብሔራዊ ቡድን መሸነፉን ተከትሎ በተዘጋጀው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ሐገር ቤት የሚገኙ የመንግስት እና የመንግስት ደጋፊ ጋዜጠኞች ለቡድኑ መሸነፍ አሰልጣኙን ተጠያቂ ለማድረግ የተለያዩ ጥያቄዎችን የጠየቁ ሲሆን ለጋዜጠኞቹ ምላሽ የሠጡት የብሔራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ በጋዜጠኞቹ አቅም እና እውቀት ተሳልቀዋል፡፡eth football team2

አንድ የኢቲቪ ጋዜጠኛ አሰልጣኙን “ቀኝ ተከላካይ ቦታ ችግር እያለ ለምን ሌላ ተጫዋች አልቀየሩም” ብሎ ሲጠይቅ አሰልጣኙ በግርምት “እንግዲህ ጎበዝ የቀኝ ተከላካይ እጥረት እንዳለ አውቃለው በዚህ ቦታ ጎበዝ ተጫዋች የባርሴሎናው ዳንኤል አልቬስ ነው እርሱ ደግሞ ብራዚላዊ ሆነ እንጂ ኢትዮጵያዊ ቢሆን አሰልፈው ነበር በተረፈ ደካማ ተጫዋች ለመኖሩ ተጠያቂ የሐገሪቱ አሰራር እንጂ የእኔ አሰለጣጠን አይደለም” ሲሉ አክለዋል፡፡

ሌላው አስገራሚ ጉዳይ “እኛ የተሸነፍነው በማሊ ብሔራዊ ቡድን እንጂ በኦሮሚያ ብሔራዊ ቡድን አይደለም” ሲሉ ጋዜጠኞቹ ጫጫታ አሰምተዋል፡፡ አሰልጣኙ ትክክል ናቸው ምክንያቱም ለኦሮሞ ጎሳ ብሔረሠብ የሚል ስያሜ ከሠጠን ለአማራውም ጎሳ ብሔረሰብ የሚል ስያሜ ከሠጠን እና ብሔር ማለት ደግሞ የአንድ ሐገር ነዋሪ መሆኑን የሚያውቅ ጭንቅላት ካለን ለምን የኦሮሚያ ብሔራዊ ቡድን የአማራ ብሔራዊ ቡድን ሲባል ንዴት ውስጥ እንገባለን፡፡ ዘይትገርም ነው ነገሩ የመንግስት ጋዜጠኛው የብሔርን ትክክለኛ ትርጓሜ ሣያውቅ በየደቂቃው ብሔር ብሔረሠብ ሲል ይውልና የኦሮሞ የአማራ ብሔራዊ ቡድን ተብሎ ሲጠራ እምቧከረዩ ይላሉ ብሔር አለ ካላቹህ የአማራ ወይም የኦሮሞ ብሔራዊ ቡድን ሲባል ምን ያናድዳችኋል፡፡

eth footballአብዛኛው ኢትዮጵያዊ የስፖርት ጋዜጠኛ የውጭ ሐገር ስፖርት ሲተነትኑ ለሚሰማቸው ኢትዮጵያዊ የስፖርት ታዳሚ አፍ የሚያስከፍት ቃላት ሲያወጡ ይሠማል በጥቂቱ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ክህሎት ላለው ግለሠብ ግን የእነርሱን ወሬ ከእንግሊዝ የስፖርት ታብሎይዶች የተተረጎመ መሆኑን እማኝ ሳያስፈልገው የመረጃውን ምንጭ በመግለፅ ያስረዳችኋል፡፡ ይህን ጊዜ እኛ ሐገር ያለው የስፖርት ጋዜጠኛ ሳይሆን የእንግሊዝ የስፖርት ጋዜጣዎችን ወደ አማርኛ እና ወደተለያዩ የሀገራችን ቋንቋ ተርጉሞ የሚያቀርብ የስፖርት ጋዜጣ ተርጓሚ መሆኑንን ልብ ይሏል፡፡

ለዚህም ይመስለኛል አንድ ኢትዮጵያዊ የስፖርት ጋዜጠኛ ስለ ኢትዮጵያ ቡና እግር ኳስ ክለብ ድክመት ከሚያወራ ይልቅ ስለ አርሠናል ድክመት እና ስለ ማንችስተር ቀጣይ እቅድ ቢያወራ ይቀለዋል፡፡ የቀለለው በርካታ መረጃን ስለሚያገኝ እንዲሁም ያንን መረጃ ወደአማርኛ ተርጉሞ ለማቅረብም ምቹ ስለሆነ ነው፡፡ ስለ ኢትዮጵያ ቡና ስለምን ለምን አታወሩም ሲባሉ መልሳቸው ስለ ቡና መረጃ ከየትም አናገኝም የሚል ነው፡፡ ይህ እጅግ አሳፋሪ እና አሸማቃቂ መልስ ነው የአርሠናልን ጉዳይ የእንግሊዝ ታብሎይድ ላይ የሚፅፍ አንድ ብሪታንያዊ ጋዜጠኛ መረጃው መጥቶለት ሳይሆን ሄዶ ጠይቆ ነው መረጃውን ያመጣው፡፡ የኢትዮጵያ ጋዜጠኛ ግን የቡና ወይም የኤልፓ ዜና እቤቱ ድረስ በኢንተርኔት መስኮት እንዲመጣለት ይጠብቃል፡፡ ከዛም ውጪ አዲስ አበባ ስታዲየም ገብቶ ጨዋታ አንብቦ ትንተና ለመስጠት ያለው እውቀት አነስተኛ መሆኑን ተረድቶ አልያም ለመሸፈን ሲል ስለ ሮናልዶ የወገብ ቁጥር ይነግረናል፡፡

በአንድ ወቅት ፌስቡክ ላይ “ብሔራዊ ቡድኑ ከተሸነፈ ለመንግስት ጋዜጠኛው ጥፋተኛ ፌዴሬሽኑና አሰልጣኙ እንጂ ፌዴሬሽኑን እና አሰልጣኙን በበላይነት የሚመራው የስፖርት ሚኒስትር አይደለም” የሚል ፅሁፍ ማስነበቤን ይታወሳል፡፡ ይህ ነገር ዛሬም ሳይቀየር የመንግስት ሚዲያውን ስከታተል እንደጠበኩት አሰልጣኙን ሲሰድቡ ነው የሚያረፍዱት፡፡ አሠልጣኑ ምን ማድረግ እንደነበረበት ግን አይነግሩንም ምክንያቱም ይህን ለማድረግ እውቀት ያስፈልጋል አልያም የገነነ መኩሪያ አይነት ስፖርታዊ እይታ ያስፈልጋቸዋል፡፡genene

እግር ኳሳችን እንዳያድግ እንቅፋት የሆነው የስፖርት ሚኒስቴር እንጂ አንድ አሰልጣኝ ሊሆን አይችልም አሰልጣኝ በመቀያየር ውጤት ሊመጣ አይችልም፡፡ አሰልጣኝ ከተቀየረም እንደ ገነነ መኩሪያ በእውቀት ተመርተን ሐሳብ ማቅረብ ይኖርብናል፡፡ ካልሆነ ግን ዘወትር የስፖርት ሚኒስተርን ችግር ይፋ ሳናወጣ እና እንደገነነ መኩሪያ ሊብሮ Genene Mekuria Libro የመሳሰሉትን ድንቅ ኢትዮጵያዊያን አቅም እውቀት ትተን የትም ልንደርስ አንችልም፡፡ በህይወቴ በሐገራችን ስፖርት ዙሪያ ሳስብ የገነነ መኩሪያን አቅም ኢትዮጵያችን እንድትጠቀም አለመደረጉ ሁሌም የሚያነገበግበኝ ጉዳይ ነው፡፡ ገነነ ብሔራዊ ቡድኑን ይመራ ዘንድ የግድ በባለስልጣናቱ ተወዳጅ መሆን የለበትም፡፡

እጅግ የሚከፋው ግን እንዲህ ከላይ የጠቀስኳቸውን ስህተቶች በሙሉ ባካተተ መልኩ የሚተገበረው የስፖርት ጋዜጠኝነት ትክክለኛው ስፖርት ጋዜጠኝነት እንደሆነ እየተወሰደ መምጣቱ ነው፡፡ አንድ ጉዳይ በተሳሳት መልኩ በተደጋጋሚ ሲተገበር እና ለየት ባለ መልኩ በተስተካከለው መንገድ ጉዳዩን የሚያቀርበው ሲጠፋ ያ የተሳሳተ መንገድ በዘልማድ ተቀባይነት ያገኘ መንገድ ሆኖ ይቀጥላል፡፡ ስፖርት ጋዜጠኝነትም በዚህ መልኩ እየነጎደ ሲሆን ይኄ ሙያውንም ባለሙያውንም ቀስ በቀስ መጉዳቱ አይቀርም፡፡
‪#‎ሁኔ አቢሲኒያ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule