• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኢትዮጵያ ውስጥ የስፖርት ጋዜጠኛ ወይስ ተርጓሚ ነው ያለው?

February 6, 2015 06:43 am by Editor Leave a Comment

“የምን ማራዶና የምን ፔሌ ፔሌ 

እኛም አገር አለ ገብረመድኅን ኃይሌ”

ደምሴ ዳምጤ ጎልታ የምትጠቀስለት መንቶ ግጥሙ ነበረች፡፡ ለአገሪቱ ስፖርት ዕድገት በተለይም እግር ኳሱ እንዲያብብ በሙያው ያደረገው ጥረት ኢትዮጵያውያን ተጫዋቾች ክሂላቸው ከማንም እንደማያንስ በማንፀባረቅ ነበር፡፡ በ1970ዎቹ መጨረሻና በ80ዎቹ መጀመርያ ጎልተው ወጥተው የነበሩት እነሙሉጌታ ከበደ፣ ሙሉጌታ ወልደየስ፣ ገብረመድኅን ኃይሌን ሲያወድስ ገጣሚ ሆኖ በመገኘት ነበር፡፡

ስፖርት እንደ አንድ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊ እና ምጣኔ-ሃብታዊ ጉዳይ ራሱን የቻለ ሰፊ ርዕሰ ጉዳይ እየሆነ የመጣ ሲሆን ሊሰጠው የሚገባው ግምትም ያን ያህል እየከበደ መጥቷል፡፡ በመሆኑም እነዚህን ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊ እና ምጣኔ-ሃብታዊ ጉዳዮች ብቻ የሚተነትኑ የተለያዩ መገናኛ ብዙሃን እንዳሉ ሁሉ ስፖርታዊ ጉዳዮችን ብቻ የሚተነትኑ ጋዜጦች፣ ሬድዮኖች፣ የቴሌቪዥን ጣቢያዎች፣ ድረ-ገጾች እና ሌሎች መገናኛ ብዙሃን በርካታ ናቸው፡፡

በአሁኑ ወቅት በሃገር ቤት እየተተገበረ ያለው የስፖርት ጋዜጠኝነት ምን ያህል ሙያዊ እና ስነምግባራዊ ነው ለሚለው እኔም በርካታ አሉታዊ አስተያየቶች አሉኝ፡፡

eth football team1በአብዛኛው ለሃገርቤት መገናኛ ብዙሃን ስፖርት ማለት የእግር ኳስ ጨዋታ ሆኗል ያውም የአውሮፓ ክለቦች የእግር ኳስ ጨዋታ፡፡ የእግር ኳስ ጨዋታ ካለው አዝናኝነት፣ ከተመልካቹ ብዛት እና ከሚያንቀሳቅሰው ከፍተኛ ገንዘብ አንጻር በጋዜጣ ላይ የሰፋውን ቦታ እና በሬድዮ እና ቴሌቪዥን ጣቢያዎች ላይ ደግሞ የበዛውን የአየር ሰዓት ቢይዝ የጎላ ጥያቄ ላያስነሳ ይችላል፡፡ ሆኖም በእኔ ዳሰሳዊ ግምት በተለያየዩ የኤፍ ኤም እና የኤ ኤም ሬድዮ ጣቢያዎች ከሚቀርቡ የስፖርት ዝግጅቶች ብዙውን ግዜ ሙሉ በሙሉ ሊባል በሚችል ሁኔታ እና አንድ አንድ ግዜ ከዘጠና በመቶ በላይ የእግር ኳስ ጉዳይ የሚተነተን ሲሆን ከዚህም የሚበዛው የአውሮፓ የእግር ኳስ ክለቦች ጨዋታ ጉዳይ ነው፡፡

ይህ የሆነበት ምክንያት በተለያዩ ጉዳዮች ተፅዕኖ ሊሆን ይችላል አንደኛ የእግር ኳስ በተለይም ደግሞ የአውሮፓ ክለቦች የእግር ኳስ ጨዋታ ከሌሎች ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች የተሻለ አዝናኝ ነው ተብሎ ስለሚገመት፤ ሁለተኛ በሃገር ውስጥ አብዛኛው የስፖርት አድናቂ ማህበረሰብ የእግር ኳስን በተለይም ደግሞ የአውሮፓ ክለቦች የእግር ኳስ ጨዋታን የበለጠ ይወዳል ተብሎ ስለሚገመት፣ ሦስተኛ ደግሞ በተለይ ከአውሮፓ ሃገራት መገናኛ ብዙሃን የሚለቀቁ እጅግ ብዛት ያላቸው እና የየክለቦቻቸውን ሁኔታ የሚተነትኑ መረጃዎች በተትረፈረፈ ሁኔታ ማግኘት መቻሉ የጋዜጠኞችን ትኩረት በመሳቡ ሊሆን ይችላል፡፡ በእነዚህም ሆነ በሌሎች ምክንያት የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን የአውሮፓ ክለቦችን የእግር ኳስ ጨዋታ ተንታኝ ሆኗል፡፡

ዋናው ርዕሰ ጉዳይ ተረስቶ ከጨዋታው ጋር የማይያያዙ ጉዳዮች በበለጠ ትኩረት ሲዘገቡ ይስተዋላል፡፡ እከሌ የተባለው አንድ የአውሮፓ ክለብ ተጫዋች የሴት ጓደኛ ስትደሰት እና ስትበሳጭ ምን እንደምታደርግ ጠቀመውም አልጠቀመውም ለኢትዮጵያዊ ስፖርት ተከታታይ ይቀርብለታል፡፡ አሁንም ጠቀመውም አልጠቀመው ስለተጫዋቹ አባት፣ እናት እና ሌሎች ዘመዶች ማንነት እና ምንነት እንዲያነብ ወይንም እንዲያዳምጥ ይደረጋል፡፡

የእኛ ሐገር የስፖርት ጋዜጠኞች በተደጋጋሚ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን ሊያሠለጥኑ በሚመጡ የውጭ ሐገር አሠልጣኞች ጭምር መሣለቂያ ሆነዋል የቅርቡን ብናስታውስ እንኳን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በማሊ ብሔራዊ ቡድን መሸነፉን ተከትሎ በተዘጋጀው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ሐገር ቤት የሚገኙ የመንግስት እና የመንግስት ደጋፊ ጋዜጠኞች ለቡድኑ መሸነፍ አሰልጣኙን ተጠያቂ ለማድረግ የተለያዩ ጥያቄዎችን የጠየቁ ሲሆን ለጋዜጠኞቹ ምላሽ የሠጡት የብሔራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ በጋዜጠኞቹ አቅም እና እውቀት ተሳልቀዋል፡፡eth football team2

አንድ የኢቲቪ ጋዜጠኛ አሰልጣኙን “ቀኝ ተከላካይ ቦታ ችግር እያለ ለምን ሌላ ተጫዋች አልቀየሩም” ብሎ ሲጠይቅ አሰልጣኙ በግርምት “እንግዲህ ጎበዝ የቀኝ ተከላካይ እጥረት እንዳለ አውቃለው በዚህ ቦታ ጎበዝ ተጫዋች የባርሴሎናው ዳንኤል አልቬስ ነው እርሱ ደግሞ ብራዚላዊ ሆነ እንጂ ኢትዮጵያዊ ቢሆን አሰልፈው ነበር በተረፈ ደካማ ተጫዋች ለመኖሩ ተጠያቂ የሐገሪቱ አሰራር እንጂ የእኔ አሰለጣጠን አይደለም” ሲሉ አክለዋል፡፡

ሌላው አስገራሚ ጉዳይ “እኛ የተሸነፍነው በማሊ ብሔራዊ ቡድን እንጂ በኦሮሚያ ብሔራዊ ቡድን አይደለም” ሲሉ ጋዜጠኞቹ ጫጫታ አሰምተዋል፡፡ አሰልጣኙ ትክክል ናቸው ምክንያቱም ለኦሮሞ ጎሳ ብሔረሠብ የሚል ስያሜ ከሠጠን ለአማራውም ጎሳ ብሔረሰብ የሚል ስያሜ ከሠጠን እና ብሔር ማለት ደግሞ የአንድ ሐገር ነዋሪ መሆኑን የሚያውቅ ጭንቅላት ካለን ለምን የኦሮሚያ ብሔራዊ ቡድን የአማራ ብሔራዊ ቡድን ሲባል ንዴት ውስጥ እንገባለን፡፡ ዘይትገርም ነው ነገሩ የመንግስት ጋዜጠኛው የብሔርን ትክክለኛ ትርጓሜ ሣያውቅ በየደቂቃው ብሔር ብሔረሠብ ሲል ይውልና የኦሮሞ የአማራ ብሔራዊ ቡድን ተብሎ ሲጠራ እምቧከረዩ ይላሉ ብሔር አለ ካላቹህ የአማራ ወይም የኦሮሞ ብሔራዊ ቡድን ሲባል ምን ያናድዳችኋል፡፡

eth footballአብዛኛው ኢትዮጵያዊ የስፖርት ጋዜጠኛ የውጭ ሐገር ስፖርት ሲተነትኑ ለሚሰማቸው ኢትዮጵያዊ የስፖርት ታዳሚ አፍ የሚያስከፍት ቃላት ሲያወጡ ይሠማል በጥቂቱ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ክህሎት ላለው ግለሠብ ግን የእነርሱን ወሬ ከእንግሊዝ የስፖርት ታብሎይዶች የተተረጎመ መሆኑን እማኝ ሳያስፈልገው የመረጃውን ምንጭ በመግለፅ ያስረዳችኋል፡፡ ይህን ጊዜ እኛ ሐገር ያለው የስፖርት ጋዜጠኛ ሳይሆን የእንግሊዝ የስፖርት ጋዜጣዎችን ወደ አማርኛ እና ወደተለያዩ የሀገራችን ቋንቋ ተርጉሞ የሚያቀርብ የስፖርት ጋዜጣ ተርጓሚ መሆኑንን ልብ ይሏል፡፡

ለዚህም ይመስለኛል አንድ ኢትዮጵያዊ የስፖርት ጋዜጠኛ ስለ ኢትዮጵያ ቡና እግር ኳስ ክለብ ድክመት ከሚያወራ ይልቅ ስለ አርሠናል ድክመት እና ስለ ማንችስተር ቀጣይ እቅድ ቢያወራ ይቀለዋል፡፡ የቀለለው በርካታ መረጃን ስለሚያገኝ እንዲሁም ያንን መረጃ ወደአማርኛ ተርጉሞ ለማቅረብም ምቹ ስለሆነ ነው፡፡ ስለ ኢትዮጵያ ቡና ስለምን ለምን አታወሩም ሲባሉ መልሳቸው ስለ ቡና መረጃ ከየትም አናገኝም የሚል ነው፡፡ ይህ እጅግ አሳፋሪ እና አሸማቃቂ መልስ ነው የአርሠናልን ጉዳይ የእንግሊዝ ታብሎይድ ላይ የሚፅፍ አንድ ብሪታንያዊ ጋዜጠኛ መረጃው መጥቶለት ሳይሆን ሄዶ ጠይቆ ነው መረጃውን ያመጣው፡፡ የኢትዮጵያ ጋዜጠኛ ግን የቡና ወይም የኤልፓ ዜና እቤቱ ድረስ በኢንተርኔት መስኮት እንዲመጣለት ይጠብቃል፡፡ ከዛም ውጪ አዲስ አበባ ስታዲየም ገብቶ ጨዋታ አንብቦ ትንተና ለመስጠት ያለው እውቀት አነስተኛ መሆኑን ተረድቶ አልያም ለመሸፈን ሲል ስለ ሮናልዶ የወገብ ቁጥር ይነግረናል፡፡

በአንድ ወቅት ፌስቡክ ላይ “ብሔራዊ ቡድኑ ከተሸነፈ ለመንግስት ጋዜጠኛው ጥፋተኛ ፌዴሬሽኑና አሰልጣኙ እንጂ ፌዴሬሽኑን እና አሰልጣኙን በበላይነት የሚመራው የስፖርት ሚኒስትር አይደለም” የሚል ፅሁፍ ማስነበቤን ይታወሳል፡፡ ይህ ነገር ዛሬም ሳይቀየር የመንግስት ሚዲያውን ስከታተል እንደጠበኩት አሰልጣኙን ሲሰድቡ ነው የሚያረፍዱት፡፡ አሠልጣኑ ምን ማድረግ እንደነበረበት ግን አይነግሩንም ምክንያቱም ይህን ለማድረግ እውቀት ያስፈልጋል አልያም የገነነ መኩሪያ አይነት ስፖርታዊ እይታ ያስፈልጋቸዋል፡፡genene

እግር ኳሳችን እንዳያድግ እንቅፋት የሆነው የስፖርት ሚኒስቴር እንጂ አንድ አሰልጣኝ ሊሆን አይችልም አሰልጣኝ በመቀያየር ውጤት ሊመጣ አይችልም፡፡ አሰልጣኝ ከተቀየረም እንደ ገነነ መኩሪያ በእውቀት ተመርተን ሐሳብ ማቅረብ ይኖርብናል፡፡ ካልሆነ ግን ዘወትር የስፖርት ሚኒስተርን ችግር ይፋ ሳናወጣ እና እንደገነነ መኩሪያ ሊብሮ Genene Mekuria Libro የመሳሰሉትን ድንቅ ኢትዮጵያዊያን አቅም እውቀት ትተን የትም ልንደርስ አንችልም፡፡ በህይወቴ በሐገራችን ስፖርት ዙሪያ ሳስብ የገነነ መኩሪያን አቅም ኢትዮጵያችን እንድትጠቀም አለመደረጉ ሁሌም የሚያነገበግበኝ ጉዳይ ነው፡፡ ገነነ ብሔራዊ ቡድኑን ይመራ ዘንድ የግድ በባለስልጣናቱ ተወዳጅ መሆን የለበትም፡፡

እጅግ የሚከፋው ግን እንዲህ ከላይ የጠቀስኳቸውን ስህተቶች በሙሉ ባካተተ መልኩ የሚተገበረው የስፖርት ጋዜጠኝነት ትክክለኛው ስፖርት ጋዜጠኝነት እንደሆነ እየተወሰደ መምጣቱ ነው፡፡ አንድ ጉዳይ በተሳሳት መልኩ በተደጋጋሚ ሲተገበር እና ለየት ባለ መልኩ በተስተካከለው መንገድ ጉዳዩን የሚያቀርበው ሲጠፋ ያ የተሳሳተ መንገድ በዘልማድ ተቀባይነት ያገኘ መንገድ ሆኖ ይቀጥላል፡፡ ስፖርት ጋዜጠኝነትም በዚህ መልኩ እየነጎደ ሲሆን ይኄ ሙያውንም ባለሙያውንም ቀስ በቀስ መጉዳቱ አይቀርም፡፡
‪#‎ሁኔ አቢሲኒያ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule