• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ዘላለማዊነት ለገንዳዎች!! ዘላለማዊ ክብር ለገንዳዎች”

April 14, 2014 07:24 am by Editor Leave a Comment

የገንዳዎች የደራጃ መዳቢ ድርጅት ሊቋቋም ይገባል። ገንዳዎች የኑሮ መሰረት የሆኑላቸው እየበረከቱ ስለሆነ በደረጃ መከፋፈል አለባቸው። የአጠቃቀማቸውም መመሪያም በግልጽ ሊቀመጥ ይገባል። የደረጃዎች መዳቢ ድርጅት ቢያንስ በገንዳዎች ውስጥ ስለሚጣሉ ቆሻሻዎች መመሪያ በማውጣት የሚበሉ ነገሮች ከሌሎች አይነት ቆሻሻዎች ተለይተው እንዲጣሉ ማዘዝ አለበት። ከሸራተንና ከቤተ መንግስት የሚወጡ የምግብ ትራፊዎች ተጠቃሚ ጋር ሳይደርሱ ፓስተር እንዲመረመሩ የሚያዝ መመሪያ ቢወጣም መልካም ነው። ቀጭኑ ዘ-ቄራ ማሳሰቢያ አለው።

ገንዳዎች የኢህአዴግን ስራና ሃላፊነት በመወጣት ለድህነት ሰለባዎች “የላቀ” አስተዋጽኦ እያበረከቱ ስለሆነ የሽልማት ኮሚቴ ይቋቋምላቸው። ገንዳዎች በሚወጣላቸው ደረጃ መሰረት ተለይተው ይሸለሙ። የጥሬ ስጋ ተጠቃሚዎችና አንዳንድ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ሽልማቱን ለግል ውዳሴ እንዳይጠቀሙበት አቶ ደመቀ መኮንን የሚመሩት ተቆጣጣሪ ይመደብ። ይህ የእለቱ ጥቆማዬ ነው። ገንዳዎች ባይኖሩ ኖሮ ምን ይኮን ነበር? “ዘላለማዊነት ለገንዳዎች!! ዘላለማዊ ክብር ለገንዳዎች!!”

gendaድህነት ክፉ ነው። ድህነት ስል የሚያምረውን ድህነት አይደለም። “የሚያምር ድህነት ምንድነው?” ለምትሉ መልስ የለኝም። ስለምንግባባ!! እኔ “ክፉ” የምለው መረን የወጣውን ድህነት ነው። ገደብ የለቀቀውን ማለቴ ነው። እረፍት ነስቶ ሞራል የሚያንኮታኩተውን ነው። ሞራል አድቅቆና ሰውነትን አዝሎ አንገት የሚሰብረውን ነው። መጥፎ ጠረንን በመጠየፍ አፍንጫን ጠቅጥቆ ገንዳ ውስጥ ለጉርስ የሚያስዋኘውን አይነት ድህነት ነው። እናት ልጇን ለወሲብ ገበያ አበረታታ እንደትልክ የሚያስገድዳትን ድህነት ነው። የወለዱ የከበዱ አባትና እናትን በስተርጅና ጎዳና ላይ የሚጥለውን ድሀነት ነው …

ብዙ ጉድ፣ ብዙ ዓይነት ጓዳ አለ። መልከ ብዙ ችግር፣ መልከ ብዙ ችጋር አለ። የመከረኛዋ አገር ኢትዮጵያ ጎጆዎች ይቁጠሩት። የሚቦካ አጥታችሁ ቦሃቃ ለሰቀላችሁ፣ ሌማት ለደረቀባችሁ፣ አቁላልቶ መብላት ቅዠት ለሆነባችሁ፣ የእናት ጓዳ ለተዘጋባችሁ፣ መማሪያ ክፍል ውስጥ ርሃብ ለሚፈነግላችሁ ህጻናት፣ ጧሪ ለሌላችሁ የወግ እናትና አባቶች … ጠኔ በየጓዳው ለከነቸራችሁ … ለናንተ ሁሉ መልካም የፋሲካ በዓል ይሁንላችሁ። ፋሲካ … አሁን ለናንተም ፋሲካ ሊሆን ነው። ያስለቅሳል።

ቀጭኑ ዘ- ቄራ ነኝ። ዛሬ እጅግ ስሜቴ ተነክቷል። አንድ ነርስ ወዳጄ ያጫወተችኝ ትዝ አለኝና አልቅስ አልቅስ አለኝ። እሷ በምትሰራበት የግል የርዳታ ድርጅት ውስጥ የኤችአይቪ/ኤድስ ተጠቂዎች ለሆኑ በወር በወር የሚሰጥ ገንዘብ አለ /በነገራችን ላይ የርዳታ ድርጅት ራሱ ሌላ ቫይረስ አለበት/ ርዳታው የሚሰጠው ምርመራ እየተደረገ ነው። በምርመራው ቫይረሱ የሌለበት ሰው ርዳታ አይሰጠውም። “ቫይረሱ ስለሌለብዎ እንኳን ደስ አለዎ” ተብሎ ሲነገራቸው የሚከፋቸው ብዙ ናቸው። አንዳንዶቹ “በዚህም ትለዩኛላችሁ፤ ርዳታ እንዳላገኝ ነው?” በማለት ይከራከሩ እንደነበር በተረበሸ የሃዘን ስሜት ታወጋኝ ነበር። መጨረሻ ላይ በዚህ ሁኔታ መቀጠል አቅቷት ስራ ቀየረች።

በወር 200 ብር ለመቀበል ድህነት የሚያስመኘውን አስቡት፤ የት እንደደረስን ገምቱ። ድህነት “ዛሬን ብቻ ይለፈኝ” የሚባልበት ደረጃ ደርሰናል። ይህ ደረጃ አደገኛ ነው። ዛሬን ብቻ ስለማለፍ የሚያስቡ በፍጥነት እየበረከቱ ነው። ዛሬን ማለፍ ብቻ አላማቸው ያደረጉ ሲበዙ ሁሉም ነገር “በዛሬ ይባዛል” ሁሉም ለራሱ የ”ጎበዝ አለቃ” ይሆናል። የጎበዝ አለቆች … የዚያኑ ያህል ለልጅ ልጅ የሚያካብቱ ጥቂቶች አሉ። እነዚህ ሃብታቸው ሞልቶ የገነፈለባቸውና ጥጋብ ልብ የነሳቸው የሚያደርጋቸውን አሳጥቷቸዋል። እነሱ ምድሪቱ ላይ፣ ጥጋብ ደግሞ እነሱ ላይ ህንጻ ገንብተዋል። የሰበሰቡት ሃብት፣ የገነቡትና የተገነባባቸው ህንጻ በድህነት ራዳር ውስጥ ናቸው። የድህነት ራዳር እንደ ራሱ እንደ ድህነት “ክፉ” ነው። አይምሬ ነው … ድህነት ሲያመር አመረረ ነው። አገርን ሁሉ “በዛሬን ልደር” ያጣፋል።

የማጣፋት ጨዋታ አደገኛ ነው። የጎበዝ አለቆች ሲያብቡ ጨዋታ ይፈርሳል። አዲስ ጨዋታ ይጀመራል። ህግ አልባ ጨዋታዎች ይጀመራሉ። በነገራችን ላይ አሁንም ህግ አልባ ጨዋታ የሚጫወቱ አሉ። ከቻሉ ኢትዮጵያን ከህዝቧ ነጥለው በፓራሹት ወደ ሌላ ስፍራ እንዲያዘዋውሯት የተፈቀደላቸው አሉ። እነዚህ የጎበዝ አለቆች የተበደሩትን ብር እየረጩ ይዘፈንላቸዋል። ይሞካሻሉ። የፈለጉትን አጥር ዘለው የተከበረ አንሶላና ብርድ ልብስ አስገድደው ይከፍታሉ። የህሊናቸው ጠረን በሰሩት ግፍ መጠን ሸቷል። ስብእናቸው ቀርንቷል። የሰውነት ማዕረግ የላቸውም። በእርም ሃብት ህሊናቸው ተጋርዶ “ሰው እኩል ይሆናል ብር” በሚል የወደቀ የሂሳብ ቀመር ውስጥ ተነክረዋል። የድህነት ራዳር እነዚህንም ይከታተላቸዋል።Circus therapy for young homeless

“የራበው ሰው የአፍ ጠረኑ ይቀይራል” የሚል ጓደኛ ነበረኝ። ሰው የአፉ ጠረን የሚቀየረው ጨጓራው የሚፈጨው አጥቶ ሲጨስ እንደሆነ ሁሌ ይናገራል። ለጋስ ነበር። ሰው መርዳት ያስደስተዋል። ሆን ብሎ የሚጎበኛቸው ድሃ እናትና አባቶች ነበሩት። ይኸው ባልደረባዬ “ከራበው ላይ የሚዘርፉ ደግሞ ህሊናቸው ይገማል” በማለት ይጠየፋቸዋል። ዛሬ እሱም ትዝ አለኝ። ነብሱን ይማረው!!

አዎ!! በቀን ሶስቴ እንደሚበላ የተወተወተ ህዝብ በወጉ አንዴም መጉረስ ተስኖታል። ከ22 ዓመት በኋላም ስለ ጉርስ ሳይሆን ስለ “ውርስ” ነው የምንሰማው። በቂም በቀል ዜጎች ከስራ እንዲባረሩ የወሰነ “ውርስ” ለማስተዋወቅ፣ ለመዘከር፣ መታሰቢያውን ለመትከል በጀት ከድሃ ጉሮሮ እየተነጠቀ ይፈስለታል። በቁም ድህነት ነቃቅሎ ያፈረሳቸው እያሉ ለሞተው ቂመኛ መንፈስ ግብር ይገባል። አዶ ከርቤ ይባላል። የኢትዮጵያን ታሪካዊ ፋይዳና ሚስጥራዊ የባህር በር ላዘጋ መንፈስ ስግደት … ቀጭኑ ጥያቄ አለው። ጥያቄው አንድ ነው። ከሙት መንፈስና ከነዋሪ የቱ ይብሳል። ለየቱ መገበር ይቀላል። የቱ ተግባር ህሊናን ያሸታል ወይም ያለመልማል?

አንድ ሳሪስ አዲስ ጎማ ሀዲዱ አካባቢ ያገኘሁት እብድ ትዝ አለኝ። ስለመቆም ይለፈልፋል። “የቆሙ የሚመስላቸው ብዙ ናቸው፣ ግን አልቆሙም። ያልቆሙት መቆም ስለማይፈልጉ አይደለም …” በፍጥነት ይናገራል። ይደጋግማል። “… መቆም እንዴት እንደሆነ ስላላወቁ ነው። መቆም የራሱ ምስጢር አለው። አንተ ግን ተደገፍ፣ ተደጋገፍ፣ ብቻህን አትቁም፣ እንኳን ሰው እንጨት ይደግፋል። ክራንች ይደግፋል። ብቻህን ከምትቆም …” ይናገራል። የስብከት አይነት ነው። ይሰብካል። “አንተ ግለኛ ሁሉ። ሆዳም ሁሉ። ስማ” እያለ ይጮሃል። ስለመብላት ሲናገር “የሞተ ነገር የምትበሉ ሁሉ” ይላል። ለምን እንደዚህ እንደሚል በወቅቱ አልገባኝም። ግን ታላቅ ነገር እንደተናገረ ሁሌም አስባለሁ። አዎ!! መደገፍ። እንኳን ህዝብ እንጨትም ምርኩዝ ይሆናል። ኢህአዴግ ድጋፉ ጠብ መንጃ ነው። ታንክና አጋዚ ነው። ፌደራል ሰራዊትና ስለላው ነው። ለዚህ ሁሉ ብር ይፈሳል። በህዝብ ተደግፎ ገንዘብ በመቆጠብ ጠኔ ለሚደፋቸው ማዋሉ አይቀልም? የህሊና መሽተትና መዋብ እዚህ ጋር ይነሳሉ። ድህነትም የሚያቅራራው እዚህ ወሳኝ ነጥብ ላይ ነው። ክፉ ነዋ!! ሲነሳበት ራዳሩን ሲያበራው … ዋ! ያኔ!! ሳይቃጠል በቅጠል አሉ!!

ስለ ጡረተኞች አስባችሁ ታውቃላችሁ። እንደው ለብቻቸው ገበያ የሚገበዩበት ስፍራ አላቸው? የነሱና የቤተሰቦቻቸው ፍላጎት በቀዶ ጥገና ተኮላሽቷል? አንዴ አንዲት አሮጊት እናት እንዲህ አጫውተውኝ ነበር። በደርግ ስርዓት አንድ ያከራዩት የጭቃ ቤት “ትርፍ ሃብት” ተብሎ ተወሰደባቸው። አበል 7 ብር ከሃምሳ አላቸው። ኢህአዴግ ገብቶ 18 ዓመት እስኪሞላው ገቢያቸው ያቺው 7 ብር ከሃምሳ ነበረች። በየወሩ ደሞዝ ለመቀበል ቀበሌ ሄደው ይሰለፋሉ። ደሞዝ!! እኚህ እናት ብዙ ብለውኛል። መፈጠርን የሚያስጠላ የድህትን ወለል አሳይተውኛል። ለነብስ ያሉ እየረጠቧቸው እንጂ እሳቸው የአንድ ጎልማሳ ዘመን ሸምተው አያውቁም። መለስ እኚህን አዛውንት ጨምሮ ነበር “በቀን ሶስቴ አስበላችኋላሁ /ይቅርታ አበላችኋለሁ/” ሲል የዋሹት። የቂም ፖለቲካ ምህንድስናው ወጥሮ ይዟቸው እንደሁ አላውቅም። እንደወጋችን እዚህ ላይ ነብስ ይማር ማለት አይቻለኝም። መለስን ነብስ ይማር ካልኩ፣ ኑሮ አድቅቆ ለሞት ያስረከባቸውን እናት ምን ልላቸው ነው? ከፈለጋችሁ ታዘቡኝ!!

ጅቡቲ እጇን አጣጥፋ ትበላለች። ቀን የጅቡቲ ጭሰኛ አደረገን። ቂምና የበታችነት መንፈስ ለጅቡቲ አምበረከከን። ጅቡቲ የለፋንበትን እየሰበሰበች ትገምጣለች። “እያንጓለለ” ይላል ይህ ነው። የተንኮል ፖለቲካ!! ጅቡቲን የሚያስፈስክ ሲስተም … አሁን ፋሲካ ነው። ለክርስትና ሃይማኖት ተከታዮች ሁሉ ፋሲካ ታላቅ በዓል ነው። ከላይ በመግቢያዬ ለጠቀስኳችሁ ሁሉ ምን እንደምመኝ አላውቅም። የፋሲካው ጌታ መላ ይበላችሁ። ከፋሲካው ጌታ በላይ ጌቶች ፈጥራችሁ በውርስ አምልኮ ለታሰራችሁ፣ ህሊናችሁ ለሸተተ፣ ልቡናችሁ በትዕቢትና በጥጋብ ለተወጠረ የፋሲካው አምላክ ይርዳችሁ!! የሞተ/አርዶ ለመብላት ካሁኑ መደራጀት የጀመራችሁ ግራና ቀኙን እዩ። የድሆች ራዳር በስራ ላይ ነውና!! እስከዛው ግን “ዘላለማዊ ክብር ለገንዳዎች”… እስኪ እንረፍ። መልካም እረፍት!! ቀጭኑ ዘ – ቄራ!

kechinu@goolgule.com

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule