• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ኤርትራ የትግራይ ናት”

December 14, 2015 12:27 pm by Editor 12 Comments

ኤርትራ የትግራይ አካል ናት የሚል አስተምህሮና የፖለቲካ ዝግጁነት ቅስቀሳ መጀመሩ ተሰማ። የጎልጉል ታማኝ ምንጮች ኤርትራ የትግራይ አካል ስለነበረች እንደገና መልሶ በመቀላቀል ታላቋን የአክሱም መንግስት ለመመሥረት የተያዘው አጀንዳ ተግባራዊ ለማድረግ ይቻል ዘንድ አስፈላጊው ሥራ እየተሰራ መሆኑንንም ጠቁመዋል። ለኢትዮጵያ እንደሆነ የሚጠቀሰው “ትልቅ ነበርን ትልቅ እንሆናለን” የሚለው የህወሃት መፈክር ኤርትራን ከትግራይ በመቀላቀል የአክሱምን “ዳግም ልደት” (ህዳሴ) ለመተግበር የታቀደ ነው ተብሏል፡፡

አጀንዳው ባልታሰበ ወቅት ብቅ ያለው በመሃል አገርና በተለያዩ አካባቢዎች እየተነሳ ያለው ተቃውሞ መበራከቱ ያሳሰባቸው ለሚያነሱት የስጋት ጥያቄ መልስ ለመስጠት ነው። የሻዕቢያን ተቃዋሚዎች በማደራጀት፣ በመደገፍና የስደት ፓርላማ በማቋቋም በህወሃት እየተካሄደ ያለው ሥራ የዚሁ ዕቅድ አካል እንደሆነ መረጃውን የሰጡት ክፍሎች አመልክተዋል። ህወሃት ውስጥ ያሉ ኤርትራዊ ደም ያላችው ባለሥልጣኖች የዚህ ዓላማ አካል ናቸው ተብሎ እንደሚገመትም አክለው ይናገራሉ።eritrea opposition conference

ስለ ኤርትራ ከተወላጆቹ በበለጠ በልበሙሉነትና ባለቤትነት መንፈስ በገሃድ የሚሟገቱት የቀድሞው የህወሃት መሪና የነፍስ አባት ስብሃት ነጋ አሁን የሚመሩት የሰላምና የልማት ዓለም አቀፍ ተቋም “የሃገሪቱን ገፅታ ለመገንባት የኢትዮ-ኤርትራን የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ወደ ተሻለ ምዕራፍ ለማድረስ የሚያስችሉ ስራዎችን እያከናወነ” ሲሉ ኢህአዴግ በፓርላማ ስም ለሚመራው የምክርቤት ኮሚቴ መናገራቸውን ሰኔ 5፣2007 የታተመው የኢቲቪ (ኢብኮ) ዘግቧል፡፡ የውጭ መከላከያና ደህንነት ጉዳዮች ቋሚ ኮቴውም የስብሃትን ዘገባ ካደመጠ በኋላ “ኢንስቲትዩቱ የኢትዮ-ኤርትራ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማሳደግ የጀመረውን ስራ አጠናክሮ እንዲቀጥል” ማሳሰቡ ጨምሮ ተገልጾዋል፡፡

“የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ የሚለውን ስም የማትቀይሩት ለምንድን ነው?” የሚል ጥያቄ ለሴት ጓደኛው ሲያቀርብ “መጀመሪያ ኤርትራን ወደ ውድ እናት አገሯ መመለስ ይቀድማል” የሚል መልስ ማግኘቱን ትምህርት ሚኒስቴር እንደሚሰራ የተናገረ የጎልጉል ደንበኛ ከሁለት ወር በፊት ገልጾ ነበር። ይህ ለትግራይ ሕዝብ የማይጠቅም እንዲያውም ለከፍተኛ ችግር የሚዳርግ እና በስሙ የሚፈጸም ሤራ ተቃዋሚዎች እንዳሉት ቢገመትም በግልጽ ደጋፊዎችም አሉት፡፡

በዴንማርክ የምትኖር አንዲት የትግራይ ተወላጅ እዚያው ለሚገኝ የጎልጉል አምደኛ ተመሳሳይ መልስ ሰጥታለች። “ደሚት (የትግራይ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ) የሚባለው ሃይል የህወሃት ልዩ አጀንዳ አስፈጻሚ እንጂ የህወሃት ተቃዋሚ አይደለም” ስትል ስሜት በተቀላቀለበት ሁኔታ ተናግራለች። ስዊድን አገር ለትምህርት ተልካ ዴንማርክ የቀረችው ይህቺው የትግራይ ልጅ “ኢሳያስ በቅርብ ይወገዳል” ስትል መሃላ የተቀላቀለበት ትንቢት ተናግራለች። “እጁን ሰጥቷል፤ ፈርሷል፤ ወደ ልማት ተመልሷል፤…” የሚባልለት የሞላ አስገዶም ደሚት በቃል ለኢትዮጵያ ነው የምታገለው እያለ በትግራይ ስም መቋቋሙና መቀጠሉ ገና ከጅምሩ ለብዙዎች ጥያቄ የፈጠረ ጉዳይ ነበር፡፡

ህወሃት ደሚትን “አሸባሪ” በሎ ያላስፈረጀው ብቸኛ ነፍጥ ያነገበ ድርጅት መሆኑ የዘወትር መወያያ መሆኑ ይታወቃል።

የኢትዮጵያን ታሪካዊ ታላቅነት በማሰብ እንደገና ገናና አገር እንደምትሆን የሚያመላክቱ ናቸው የሚባልላቸው ሕዝብን ቀስቃሽ መፈክሮች ህወሃት ለራሱ ድብቅ ዓላማ ሊጠቀምበት ያሰበ ስለመሆኑ ሲነገር ቆይቷል፡፡ “ህዳሴ” (ዳግም ልደት – renaissance)፣ “ትልቅ ነበርን ትልቅ እንሆናለን”፣ … እየተባሉ የሚለፈፉ መፈክሮች የኢትዮጵያን ሳይሆን የአክሱምን ገናናነት እንደገና እንዲወለድ በማድረግ በድጋሚ ትልቅ ለመሆን የተወጠነ ነው በማለት የሚከራከሩ፤ ትግራይ ካለ ዓቅሟ የምታካሂደው የኢኮኖሚ፣ የትምህርት፣ የወታደራዊ፣ ወዘተ “ልማታዊ እንቅስቃሴ” በተያያዥነት ሊጠቀስ እንደሚገባ በአስረጂነት ይጠቅሳሉ፡፡

ኤርትራ የትግራይ ታሪካዊ አካል ስለመባሏ አስተያየት የተጠየቀ በአውሮፓ የኢሳያስ ተቃዋሚ ኃይሎች አመራር አባል የሆነ የኤርትራ ተወላጅ የዴንማርክ ነዋሪ “እኛና የትግራይ ህዝብ አብርን ልንኖር አንችልም። ምኞታቸው ይገርማል። ከሚመለከታቸው ጋር ተነጋገሬ አስተያየት እሰጣለሁ” የሚል መልስ ሰጥቷል።

ህወሃት ታላቋን ትግራይ የመመስረት (ነጻ የማውጣት) ፕሮግራም ይዞ የሚንቀሳቀስ ተገንጣይ ድርጅት ነው።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Tomi says

    December 14, 2015 03:12 pm at 3:12 pm

    Kkkkkkk nice comedy after what they say Arab is for them.Dirtyilless Tplf time finish for them

    Reply
  2. Eri Anbesa says

    December 14, 2015 03:12 pm at 3:12 pm

    Hi eye Weyane man benante yemitalel ale y Eritrea hone y Etiopia hizd yenant tenkol kifat minknga leba yemayawek yelemna yetigray hizb lb ystew

    Reply
  3. dongolo says

    December 15, 2015 10:18 am at 10:18 am

    ye 3000 amet kijet tenesabachu

    Reply
  4. koster says

    December 15, 2015 01:04 pm at 1:04 pm

    I knew the evil Agenda of the fascists for Long. They are in Menelik Palace because of the power vaccum and since it is ideal to loot and build greater TIGRAI but the fascists have never and ever said that they are Ethiopians. http://vimeo.com/18242221

    Reply
  5. Tamirat says

    December 16, 2015 11:42 pm at 11:42 pm

    Melese Zenawi openly said the following regarding his longterm ambition:
    1. When asked haw he wanted to be remembered, he said as the founding father of the nation (tigray)
    2. He once openly invited OLF to come to the negotiation tableby stating that “at the end of the day, we dont have differences in longterm objective”
    3. Regarding port of Asab “we will not take it even if Shabia agree to give the port”
    4. Why he hate Amharas? You know the answer.
    5. “We will fight to Eritrian freedom if forces from ethiopia try to invade that country”
    6. Why he keeps absolute monoply of power and wealth?
    7. Why he wants to create contradiction between tigryans and the rest of ethiopians?
    Why he inserted article 39?
    8.why ethinic based fedralism?
    ………

    Reply
  6. Ramedan says

    December 19, 2015 09:44 am at 9:44 am

    Historical poropoganda is nothing to change tigry poeple because the are corrupting in any area
    lose ertira land and unethiopian!! !!

    Reply
  7. Semka says

    December 23, 2015 10:03 am at 10:03 am

    Nice joke of 2015, አንዃን ኤርትራ ይልቅ ትግራይን የትግራይማረግ ይሞክሩ መጀመሪያም ታሪካጽቸው በደም ኣያውቁም።

    Reply
  8. Semka says

    December 23, 2015 10:26 am at 10:26 am

    ኣክሱም ውን ሲሆን በዛን ግዜ የትግራይ ኣልነበረም። የነሱ የታሪክ ትንታኔ ሲተት ስለሆነ ስህተትም አንዳስቡ ያረጋቸዋል፣ ለምንድነው አንደዛ ያልኩት፣ በኣክሱሜት ወይ ኣፕሲኒኣን ማለት ህበሻ ብሎ የሚጠራው ግዜ ወይም ክፍለዘመን አትዮጵያ፣ ትግራይ፣ አርትራ የሚል ስም ኣልነበረም። እነሱ የሚሉት ኣክሱም ባሁኑ ባለው የትግራይ ክፍለሃገር ወይም ክሊል ስለሚገኝ ኣክሱም የትግራይ ነው የሚሉት እንጂ ኣነሱም አኮ በዛም ግዜ ኣልነበሩም። ለዚህ ነው አኔ የስህተት ታሪክ ትንታያቸው ስህተት አንዲኣስቡ ያረጋቸው ያልኩት። አንድያው ኣክሱም ሃወልት በነሱ ክሊል መሰራቱ አድለኞች ናቸው አንጂ አነሱም የዛን ግዜ ኣክሱም ኣይመስሉም።

    Reply
  9. tarik says

    December 25, 2015 09:08 am at 9:08 am

    weyane is day dreaming, Eritreans and Tigrians can never be one country!!
    1 They do not like each other
    2 Eritreans do not believe they are Tigrians
    3 There are about eight tribes in Eritrea
    4 Tigrina people in Eritrea never believe they are Tigrians

    Reply
  10. Amman says

    December 26, 2015 01:25 am at 1:25 am

    የማይጨበጥ የሕልም ተስፍ ነው። ወያነ ሲረገዝ እና ሲወለድ ጀማሮ በሕልም እየዋኘ ነው የሚነረው ወያነ ትንሽዋን ትፍግራይ በሐይል የሊላ ሰው መሬት በመዝረፍ ታላቅዋን ሪፓብሊክ ለመመስረት ይፈልጋል የሕ ግን ሕልም ብቻ ነው.ወያን እንካን ሪፓብሊክ ትግራይ ለመመስረት ይቅር ባሐይል የዘረፈውን የበገመድር መሬት አንድ ቀን ይመለሳል። ያለንበት ዘመን 21 ከፍለዘመን በሐይል እንደ ፈለግ ማድረግ አይችልም። ደግሞ ወያነ በመጨረሻ ሳዓት ነው የለው በሞት አፋፍ ነው የሚገኘው የማድረግ ብቃት የለውም ። ለማይቀረው ሞት መዘጋጀት ነው።

    Reply
  11. Geresu duki says

    December 30, 2015 05:45 pm at 5:45 pm

    ofcourse seraye was part of tigray before the italian occupation of ertra, the other part of ertrea was midere bahiri ( bahere negash was the prince of the area. Bahere negash was one of the princes of Ethiopia. The axumite empire was an Ethiopian empire , axum was the capital city of Ethiopia. Ertrea belongs to Ethiopia. and ertreans are Ethiopians, this is the reality, period. any how at this time the two bandits shabya and woyane , mischieviousily they are twisting history, they are serving the interest of anti-Ethiopians . Most of them are the son of traitors. Their objective is to dismantle Ethiopia. Their strategy is 1. to secede province Ertrea from Ethiopia, then to put ertrea in continuous war ., to be instrumental for the immigration of ertrean youth out of ertrea , in other words to sell the youth of ertrea to the arabs and europeans . At the end the future generation would not be there , then the arabs would have an access to control ertrea and the sea cost at large. 2. To create an ethnic animosity between ertreans and tigreans to put them in a continuous war , the two provinces of Ethiopia are the base of Ethiopianism , if you put them in to antagonistic situation , they think that they can create a base to dismantle Ethiopia
    3. to propagate the Four provinces of ethiopia , gondor, gojam , shewa and wollo as Amhara the enemy of the other tribes of Ethiopia
    4. wellega, bale,arsi,harerege shewa ,…as oromos to categorize them as the enemy of Ethiopianism
    5.To create a favourable condition to dismantle, and loot Ethiopia , such as allowing Ethnic federalism , the right to secede .
    6, To create religious animosity between the christians and islams
    Neverthless , the Ethiopian people is strong. A nation which has been there for the last three thousand years , has proved that he is beyond the tribal divisions. Ethiopianism is love , this nation will prevail.

    Reply
    • Amman says

      January 3, 2016 01:21 am at 1:21 am

      ሰራየ የትግራይ ግዛት ሆኖ አይቅም ከጣልያን በፊት ሆነ በሃላ በሰራየ በኩል መረብ ወንዝ ነው የሚለያቸው ወያነ ግን ኤርትራ እንደወልቃይት አይደለችም በደንብ ያቃል።ከትግራይ ሕዝብ ምንም ጥላቻ የለንም አንድ አገር መሆን ግን አንፈልግም። ወያነ የሞተ ውሻ በሁለም የተጠላ ፍሽት ነው ጨካን ነው 3 ሜላን አማራዎች የገደለ ዘረኛ ማን ይፈልገዋል?

      Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule