• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ግብፅ ሱዳንን ከኢትዮጵያ ለመነጠል ዲፕሎማሲያዊ ዘመቻ ጀመረች

February 6, 2014 10:01 am by Editor 4 Comments

የግብፅ መንግሥት በታላቁ የህዳሴ የኃይል ማመንጫ ግድብ በተመለከተ ሱዳን ለኢትዮጵያ የሰጠችውን ድጋፍ ለማጨናገፍ፣ ሱዳንን ከኢትዮጵያ ለመነጠል ዲፕሎማሲያዊ ዘመቻ መጀመርዋን ዘገባዎች አመለከቱ፡፡

የተለያዩ የግብፅ መገናኛ ብዙኃን ሰሞኑን እንደዘገቡት፣ የግብፅ መንግሥት የተለያዩ የመንግሥት አመራሮችና ፖለቲከኞች ከሱዳን መንግሥት አቻዎቻቸው ጋር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ጀምረዋል፡፡

ለአብነት ከተጠቀሱት መካከል የግብፅ አል ዋፍድ ፓርቲ ሊቀመንበር ሳይድ አል ባዳዊ በካይሮ ከሱዳን አምባሳደር ከማል ሐሰን ዓሊ ጋር በሁለቱ አገሮች ድንበር የፀጥታ ጉዳዮች ላይ በዋነኝነት መክረዋል፡፡ በሁለቱ አገሮች ድንበር የጦር መሣሪያ ዝውውር ለማስቆም የተነጋገሩት ሁለቱ ባለሥልጣናት፣ ኢትዮጵያ እየገነባችው ባለው የታላቁ ህዳሴ የኃይል ማመንጫ ግድብና በሱዳን አቋም ላይ ተነጋግረዋል፡፡

ከውይይታቸው በኋላ አል ባዳዊ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ ሱዳን በታላቁ የህዳሴ ግድብ ላይ ያላት አቋም ከኢትዮጵያ ጋር ተመሳሳይ ነው መባሉ በእውነት ላይ ያልተመሠረተ ተባራሪ ወሬ ነው ብለዋል፡፡

በግድቡ ላይ ሦስቱ አገሮች ጥልቅ ውይይት አካሂደው የሁሉንም ወገን ጥያቄዎች በሚመለስ ደረጃ መግባባት ይኖርባቸዋል የሚሉት አል ባዳዊ፣ ሱዳን የግብፅን የውኃ ፍላጐት በሚነካና ብሔራዊ ደኅንነቷን በሚጐዳ ጉዳይ ላይ አሉታዊ አቋም አትይዝም ሲሉ አስታውቀዋል፡፡

የሱዳን የመገናኛ ብዙኃን ባለፈው ሰኞ ዘገባዎቻቸው የሱዳን የመከላከያ ሚኒስትር በዚህ ሳምንት ወደ ካይሮ በማቅናት ከግብፅ አቻቸው ከፊልድ ማርሻል አብዱልፋታህ አል ሲሲ ጋር በሁለቱ አገሮች የጋራ የደኅንነት ጉዳዮች ላይ ይመክራሉ ተብሎ ይጠበቃል ብለዋል፡፡ በተመሳሳይ የሱዳን የመስኖ ሚኒስትር ወደ ግብፅ በዚህ ሳምንት እንደሚያመሩ የሱዳን ትሪቡን ዘገባ ያመለክታል፡፡

የግብፅ የመስኖ ሚኒስትር መሐመድ አብዱል ሙታሊብ ባለፈው ሰኞ በሰጡት መግለጫ ደግሞ ኢትዮጵያ የህዳሴውን ግድብ ግንባታ ማቆም እንደሚገባት ተናግረዋል፡፡ ‹‹ኢትዮጵያ በዓባይ ላይ የኃይል ማመንጫ ግድብ መገንባት ከፈለገች መጠኑ አነስተኛ መሆን ይገባዋል፤›› ብለዋል፡፡ እንደሳቸው አባባል የህዳሴው ግድብ ግንባታ ከታቀደው ስድስት ሺሕ ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም ወደ 30 በመቶ ዝቅ ማለት አለበት፡፡ በዚህ ስሌት የታላቁ የህዳሴ ግድብ ኤሌክትሪክ የማመንጨት አቅም ወደ 1,800 ሜጋ ዋት መውረድ አለበት፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ 45 አባላትን የያዘ የግብፅ የዲፕሎማሲ ቡድን ከጥር 28 ቀን 2006 ዓ.ም. ጀምሮ ለአምስት ቀናት በኢትዮጵያ ጉብኝት ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ግብፅ በኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ላይ ያላትን ተቃውሞ ለአፍሪካ ኅብረት እንደሚያሳውቅና የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናትንም እንደሚያነጋግር ለመረዳት ተችሏል፡፡

ኢትዮጵያን የሚጐበኘው የልዑካን ቡድን በግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የዲፕሎማሲ ኢንስቲትዩት ኃላፊ አምባሳደር ዓሊ ኣል ሃዲዴ የሚመራ መሆኑን በኢትዮጵያ የግብፅ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል፡፡ የልዑካን ቡድኑ ከአፍሪካ ኅብረት የሰላምና ፀጥታ ምክር ቤት ኃላፊና ከኅብረቱ የመሠረተ ልማትና ኢነርጂ ኮሚሽነር ጋር እንደሚመክር የተያዘው ፕሮግራም ያስረዳል፡፡

በተጨማሪም ከኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት፣ ከዓባይ ተፋሰስ ዳይሬክቶሬትና ከሕግ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ኃላፊዎች ጋር እንደሚነጋገር ታውቋል፡፡ እንዲሁም ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትሪያርክና ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ጋር በመገናኘት በህዳሴው ግድብ ላይ ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

በቅርቡ ሪፖርተር ያነጋገራቸው የውኃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር የወሰንና ወሰን ተሻጋሪ ወንዞች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ፈቅአህመድ ነጋሽ፣ ሱዳን በህዳሴው ግድብ ላይ ከኢትዮጵያ ጋር የወገነችው ለራሷ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እንደሆነ አብራርተዋል፡፡ በአጋጣሚ ለድርድር በካርቱም በቆዩባቸው ጊዜያት በተለያዩ መስጊዶች ውስጥ ሳይቀር የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ሱዳንን እንዴት ሊጠቅም እንደሚችል ሲሰበክ በግርምት መታዘባቸውን በመግለጽ፣ ሱዳን ከኢትዮጵያ ጐን ለራሷ ጥቅም ስትል መቆሟን መረዳት ይቻላል ብለዋል፡፡

የግብፅ ባለሥልጣናት ከኢትዮጵያ ጋር በሚደረገው ውይይትም ሆነ ድርድር ሱዳን የግብፅን ጥቅም የሚፃረር አቋም እንድትይዝ አለመፈለጋቸው ቢነገርም፣ ሱዳን እስካሁን የግድቡን ግንባታ እንደምትደግፍ ነው የሚታወቀው፡፡ ሱዳን ከኢትዮጵያ ጎን ለመሰለፍ የቻለችው በሦስቱ አገሮች ተወክሎ ሲሠራ የነበረውና ዓለም አቀፍ ባለሙያዎችን ያካተተው የኤክስፐርቶች ፓነል ሪፖርት ድምዳሜን አገናዝባ ነው፡፡ በሪፖርቱ ግድቡ በሱዳንም ሆነ በግብፅ ላይ ይህ ነው የሚባል ጉዳት እንደማያደርስ ማረጋገጡ ይታወሳል፡፡ ምንም እንኳ የግብፅ ባለሥልጣን የሱዳን አቋም ከኢትዮጵያ ጋር ወግኗል መባሉን ተባራሪ ወሬ ነው ቢሉም፣ የሱዳን ባለሥልጣናት በአደባባይ ድጋፋቸውን መግለጻቸው አይዘነጋም፡፡(ሪፖርተር)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. MESERET B. says

    February 6, 2014 11:02 am at 11:02 am

    please egptian dont disturb us we are on renaissance

    Reply
  2. mufti seid says

    February 6, 2014 08:10 pm at 8:10 pm

    orthodox…????

    Reply
  3. fekadu mekonnen says

    February 7, 2014 03:52 pm at 3:52 pm

    Thank you for your effort !

    Reply
  4. amare tesfaye says

    February 8, 2014 09:58 am at 9:58 am

    mechem wedehoala animelesim anakimamam anafegefgim ye ethiopia hizb babay gudaye yimotali ye esikezarew mognenet yibekani ”’be abayi kudayi enimotalen………………..!!!”’

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule