• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“እኛን ያዳኑን ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ናቸው”

April 22, 2015 08:39 am by Editor Leave a Comment

አይሲስ በሊቢያ ተጨማሪ ኢትዮጵያውያንን መያዙን ከአይሲስ ያመለጠው ኢትዮጵያዊ ለቪኦኤ ገለጸ፡፡ እርሱንና ሌሎችን በአይሲስ እንዳይወሰዱ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ማስጣላቸውን ተናገረ፡፡

isis_parade_libyaይኸው ስሙ እንዳይገለጽ የጠየቀው ወገን እንደተናገረው እኛን  ከአይሲሲ ያዳኑን ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ናቸው፤ በሀገራችን በፍቅር ነው የኖርነው ክርስቲያኖቹን ለይታችሁ አትወስዱም በማለት ሙስሊሞቹ እንደተከራከሩላቸው፤ እንደጮሁላቸው አስረድቷል፡፡ በዚህም ምክንያት እርሱና ሌሎች ላሁኑ ከመሞት ተርፈዋል፤ ከዚህ ወዲህ የሚሆነውን ግን ለመናገር እንደማይችልና ሁሉንም “እግዚአብሔር ነው የሚያውቀው” በማለት በእምነት እየጠበቁ መሆናቸውን ከተሰወረበት ቦታ ለአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ ጋዜጠኛ ተናግሯል፡፡

ይኸው ከአይሲስ ያመለጠው ኢትዮጵያዊ ከዚህ በፊት ቤንጋዚ ላይ ከሌላ የትግራይ ተወላጅ ጋር ተይዘው በኤሌክትሪክ እንደተቃጠሉና ከሞት እንደተረፉ አስረድቷል፡፡ ድብደባውባ ቃጠሎው የደረሰባቸው አይሲሶች “እስልምናን እንዲቀበሉ” በሚያስገድዷቸው ጊዜ እንቢ በማለታቸው እንደሆነ ገልጾዋል፡፡

ይኸው ሊቢያ ትሪፖሊ የሚገኘው ኢትዮጵያዊ ወገን ለቪኦኤው ሰለሞን አባተ እንደገለጸው ማክሰኞ እለት ቁጥራቸውን ለመግለጽ ያልቻለው እጅግ በርካታ ኢትዮጵያውያንን ታፍሰው መወሰዳቸውንና እርሱና ሌሎች ተደብቀው ማምለጣቸውን ተናግሯል፡፡ ከተወሰዱት መካከል እርጉዝ ሴት፣ ህጻን ልጅ እና ሰሞኑን ቀዶ ጥገና ተደርጎላት ከሆስፒታል የወጣች እንደሚገኙበት አስረድቷል፡፡

በተለይ ቤንጋዚ ላይ “በግድ እስልምናን” እንዲቀበሉ ሲያስገድዷቸው እምቢ ያሉትን ከሙስሊም ኢትዮጵያውያን ለይተው ለመውሰድ አሲሶች በሞከሩበት ጊዜ “ባህላችን አይፈቅድልንም፤ አብረን (ከክርስቲያኑ ጋር) ተፋቅረን የኖርን ነን፤ እዚህ በስደት ልንለያይ አንችልም” ብለው ሙስሊም ኢትዮጵያውያኑ እሪ በማለታቸው በርካታዎች ከግድያ ማምለጣቸውን በድጋሚ ገልጾዋል፡፡

የወደፊቱን ለማወቅም ሆነ ለመናገር እንደማይችል “እግዚአብሔር አንድ ነገር እንዲያደርግ” ከመጸለይ ሌላ ምንም እንደሌለው በቃለ ምልልሱ ወቅት ተናግሯል፡፡

የቪኦኤውን ሙሉ ዘገባ እዚህ ላይ ይገኛል፡፡

ቅንብር: ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule