• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ይህንን ምን እንበለው? ኢህአዴግ እስካሁን ያለው ነገር የለም

April 15, 2014 07:33 am by Editor 5 Comments

“መኖሬን ጠላሁት። ራሴን እንዳልገድል ወንጀል ነው። ሰው እንዳልገድል ወንጀል ነው” በሚል ግራ መጋባት አንድ አዛውንት ይናገራሉ። ተበዳዮች ከእርሻ ስራ በኋላ የሚይዙትን በትር ፖሊስ ሰበሰበ። ከዚያም እገበያ ቦታ ላይ ገጀራና ጦር የያዙ ጎረምሶች እየጮሁ ጥቃት መፈጸም ጀመሩ። 16 ሰዎች፣ 26 ናቸው የሚሉ አሉ ጉዳት ደረሰባቸው። አንድ ሰው ተገደሉ።

ይህ ዜና የተወሰደው ተበዳዮች ራሳቸው ባንደበታቸው ሲናገሩ ከሚታዩበት ቪዲዮ ነው። የተገደሉት አቶ ጌጡ ክብረት ይባላሉ። የሰባት ልጆች አባት ናቸው። የተገደሉት በገጀራ ነው። ከተገደሉ በሁዋላ አይናቸውን አውጥተዋቸዋል። አንደኛው ተናጋሪ አዛውንት እንደተናገሩት ደግሞ “ብልታቸውን ሸንሽነዋቸዋል”።

ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ለህክምና ሲሄዱ “ሂድና አገርህ ታከም። ይህ የእኛ ሃኪም ቤት ነው” እንደተባሉ ምስክሮቹ ይናገራሉ። ይህ ሁሉ የሚሆነው በምዕራብ ሸዋ ዞን ደኖ ወረዳ በሶስት ቀበሌ ገበሬ ማህበራት በሚኖሩ የአማርኛ ተናጋሪዎች ላይ ነው።

ሰዎቹ እንደገለጹት ከጎንደር ከዛሬ 20 ዓመት በፊት ነው ወደ ስፍራው የገቡት። በህጋዊ ማመልከቻና በህጋዊ የአስተዳደር አካላት ውሳኔ ቀደም ሲል የዝንጀሮ መንጋ የሚኖርበትን ስፍራ እንዳለሙ ይናገራሉ። በዚህም ላይ ህጋዊ ግብር የሚከፍሉ ናቸው። አንድ እድሜያቸው የገፋ ተናጋሪ በቪዲዮው ላይ እንደተናገሩት “አስተዳደሩ ቻፓ (ማኅተም) መትቶ” አስረክቧቸዋል።

ከሃያ ዓመታት በኋላ አሁን “አማርኛ ተናጋሪ ናችሁ። መሬቱን ለቃችሁ ውጡ” የተባሉት ሰዎች ለፌደራል ባለስልጣናት አቤቱታ ማቅረባቸው ይበልጥ ጉዳት አስከትሎባቸዋል። “እስኪ ምን ታመጣለህ” በሚል ያካባቢው አስተዳደር አካላት ቀልደውባቸዋል። ከሁሉም በላይ ግን ላለፉት ሃያ ዓመታት አብረዋቸው የኖሩ ሰዎች ዛሬ እንዴት ጨክነው ገጀራ አነሱ? የሚለው ጉዳይ ስጋት የሚጭር ሆኗል። በተለይም የፍትህ አካላትና ራሱ ኢህአዴግ፣ ብአዴን ሰው በገጀራ ሲገደል ዝም ማለታቸው ድርጊቱን አሳዛኝ ያደርገዋል።

ከተፈናቃዮቹ በመከራም ሆነው ሃይማኖታቸውን ይጠብቃሉ
ከተፈናቃዮቹ በመከራም ሆነው ሃይማኖታቸውን ይጠብቃሉ

በተለያዩ ክልሎች የተለያዩ ብሔረሰብ ተወላጆች አሉ። ተስማምተውና ተከባብረው ኖረዋል። አሁንም እየኖሩ ነው። ኦሮሚያ ውስጥ ከጥንት ጀምሮ ተዋልደው፣ ወልደውና ከብደው የኖሩ አማሮች ቁጥር ቀላል አይደለም። ኢህአዴግ አገር መግዛት ከጀመረ በኋላ ኦሮሚያ ላይ በኢንቨስትመንት ስም ሰፋፊ መሬትና የማዕድን ቦታ የያዙ አሉ። ህዝብ እነዚህ ኦሮሚያን እያለቡ ያሉትን ጠንቅቆ ያውቃቸዋል። በተለይም ንጹህ ህሊና ያላቸው ጉዳዩን ከነስሌቱ ይረዱታል። ከነዚህ “ባለጊዜዎች” ዝም ተብለው ምስኪን ጭሮ አዳሪዎች ላይ እንዲህ ያለው ተግባር መፈጸሙ ውሎ አድሮ ወዴት የሚያሰኝ ይሆናል። ነገም በስፋት በተለያዩ ስፍራዎች ድርጊቱ ስላለመቀጠሉ ዋስትና የለም። በሁሉም ብሄር ብሄረሰቦች ላይ።

እነዚህ ከጎንደር እንደመጡና ላለፉት 20 ዓመታት በስፍራው ላይ በህጋዊነት የሰፈሩት ወገኖች እነሱ ካሉት ውጪ ቦታው ላይ መኖር የማይችሉበት ህጋዊ አግባብ ካለ፣ ህጋዊ ጥፋት ወይም የመረጃ ችግር ካለባቸው በህግ ክስ አቅርቦና አስወስኖ አስፈላጊውን ውሳኔ ማሳለፍ ይቻላል። ህግና ስርዓት ባለበት አገር በትር በመንጠቅ ምስኪኖችን በገጀራ ማስደብደብና ማስገደል ዘግናኝ ነው። ሰዎቹ እንዳሉት ሶስት ገበሬ ማህበር የሚሆኑ ናቸው። አንድ ገበሬ ማህበር ውስጥ ባማካይ 600 አባወራ አለ። በሶስት ሲባዛ የአባወራዎቹ ቁጥር ከፍተኛ ይሆናል። አሁንም እነሱ እንደገለጹት እያንዳንዳቸው ባማካይ ስድስትና ሰባት ቤተሰብ አላቸው። እናም ጉዳዩ በቀላል የሚታይ አይሆንም።

“አማራ በሚለው ደማችንና አጥንታችን አትውቀሱን” አልናቸው በማለት ሰዎቹ እንደገለጹት፣ ጥቃቱ የሚደርስባቸው በዘር ነው። ይህ ደግሞ ኢህአዴግ በተለይም ህወሃት የተከለው አጀንዳ ነው። ህወሃት በፕሮግራም ደረጃ አማራን የማጥፋት እቅድ ይዞ ሲታገል የኖረ፣ አሁን ደግሞ ብአዴን የሚባል ላንቲካ/ሲምቦል ድርጅት አስቀምጦ ይህንኑ የበታችነት ስጋቱ የፈጠረበትን ስሜት እያስተገበረ ነው። ብአዴን ውስጥ ያሉ ወገኖች ግን እስከመቼ በዚህ ይቀጥላሉ?

ለዜናው ጥንቅር የተጠቀምንበትን ቪዲዮ በፍኖተ ነጻነት የተዘጋጀ ሲሆን አዲስ ድምጽ ሬዲዮ ድረገጽ ላይ ነው ያገኘነው – ለመመልከት እዚህ ላይ ይጫኑ፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Zerihun says

    April 16, 2014 11:47 am at 11:47 am

    Amharas have started reaping what they keep sowing, namecalling Oromos and other ethenic groups in Ethiopia. I have witnessed recently some Amharas nameclling Oromo peasants from Finfinnee surroundings in one of Addis condominiums (Balderas) and I was heart broken. Why do you think the issue of racism happened in Bahir Dar? Because it is the capital of the racist Amharas who namecall and despise other ethenic groups (This was witnessed by the brave and hones Amhara Alemneh Makonnen). Oromos and other ethenic groups in Ethiopian have never namecalled Amhara. It’s time they go back to their fathers’ land they can’t keep insulting other ethenic groups and use their land at the same time!

    Reply
  2. Gonfa says

    April 17, 2014 01:48 am at 1:48 am

    you guys are always writing something bullshit with no evidence!!!!!!!!!!!!!!!!

    Reply
  3. Wolde says

    April 24, 2014 11:30 am at 11:30 am

    The oromos are obviously starting to pose war on Amharas.its clean every one can witness.not ony on the farmers,they also start in university students found in oromia region,like in jimma university.

    Reply
  4. andnet berhane says

    April 24, 2014 08:37 pm at 8:37 pm

    ማራው ተገደለ አማራው በገጀራ ተጨፈጨፈ የሚል ዜና በመስማት ተሰላችተናንል እስካሁን በሌላው ሕዝረተሰብ ግዛት ተሰማርተው እንድፈለጉት የሚጋልቡትን የትግራይ ተወላጆች ይህ አይነት በደልና ግድያ አልተፈጸመም ታድያ አማራው ሆነ አኛኩ አኦሞው ወይም ኮንሳው ደቡብና ኦሞው በዝምታ ካለፈው ይህ ጥያቄ የሁሉንም መልስ ሰለሚጠይቅ አማራውም እየታረድድ ልለቅ ብሎ ከሆነ ተቀብሏል ማለት ነው እንዲሁም ሌላው አማራው ሊወስድ የሚገባው አማራጭ የሌለው መንገድ ተመሳሳይ የሆነ እርምጃ መውሰድ ሊሆን ነው የሚወስደውም እርምጃ አማራጭ በትግራይ ተወላጆች ላይ ሊሆን ነው ምክንያቱም ግዛቱ የኦሮሞ ቢሆንም ገዳዮቹ የወያኔ ካድሬዎች በመሆናቸው እነሱን ቤተሰቦች የሆነኡትንና ትግራይ የሆኑትን ተመሳሳይ እርምጃ በመውሰድ ይህን አስከፊ ግድያና ማፈናቀል ማቆም የሚቻለው ራሱ ተበዳዩ ሕዝብ ብቻ ነው ምክንያቱም ወያኔ (ኢሓዴግ) በሚሰጠው መመርያ ሕዝቦችን ከማጋጨትና በመጋደል ቅራኔ ለማስገባት በመሆኑ ላለፉት 23 ዓመታት በተግባር የታየ በመሆኑ የእርስ በርስ ጦርነት ለመፍጠር ያቀደው በመሆኑ ምንም እንደማይል ሁሉም ወገኖች አውቀው የዘረጋቸውን ተባባሪ የሆኑትን የጥፋት ኃይሎች በገጀራ ሆነ በቆንጭራ እንድ አማራው፣ እንድ አኟኩ፣ እንዶሮሞው እንድ ኮንሶው እንዶሞው ደቡቡ የግፉን ምሬት ማስቀመስ ይኖርበታል ሁሉም ተገደልኩ ተፈናቀልኩ ብሎ አቤቱታ ከማቅረብ ራሱን ለማዳን መነሳት ይኖርበታል ይህን ለማድረግ ፈራ ተባ ካለ ምርጫው በመሆኑ ተደማጭና አጋር አያገኝም።

    Reply
  5. Jagema says

    May 1, 2014 08:59 pm at 8:59 pm

    ጥብቅ ማሳሰቢያ ለአማራው ህዝብና ለለአማራው ህዝብና ደጋፊ ሌሎች ብሄሮች
    አማራው ተገደለ አማራው በገጀራ ተጨፈጨፈ ተዘረፈ ወዘተ…..… አሁን ሊበቃ ይገባል፡፡ ለእያንዳደንዱ ጥቃት አጥፍ ድርብ የአጸፋ መልስ መስጠት የግድ ይላል፡፡ በማን ላይ ለሚለው ጥያቄ መለሱ አንድና አንድ ብቻ ነው፡፡ የትግራይ ተወላጆች ላይ፡፡ ምክንያቱም ጥቃቱ ያሚያደርሰው ሌላ ብሄር ቢሆንም እንኳን ያሚያቀነባበረው እና ግጭቱን የሚለኩሰው ትግራይ በቀሉ ህወሃት ከአባር ጀሌዎቹ ጋር በመሆኑ ነው፡፡ ስለሆነም ማንም ያድርሰው ማን በአማራ ላይ ለምትደርሰው እያንዳንዷ ትቃት አጥፍ ድርብ የአጸፋ መልስ በትግራይ ተወላጆች ላይ መውሰድ ግድ የሚልብት ሰዓት ልክ አሁን ነው፡፡ይገባልም፡፡ ይህ ጉዳይ መጀመር ያለበት ደግሞ በአማራ ክልል ውስጥ ተንደላቀውና ተዝናንተው እየኖሩ አማራ ከሌሎች ክልሎች አንዲፈናቀል፡ አንዲሰደድ፡ አንዲገደል ወዘተ….. መሰሪ ተንኮላቸውን በሚሸርቡት የትግራይ ተወላጆች ላይ መሆን ይኖርበታል፡፡ ጉዳዩን ለማጨናገፍ የሚሞክሩ የብአዴን አመራሮች ካሉ ተመሳሳይ እርምጃ በነሱ አና በቤተሰቦቻቸው እንዲሁም በዘመዶቻቸው ላይ መውሰድ አማራጭ የሌለው መፍትሄ ሆናል፡፡
    በተጨማሪም ትግሬን (አጋሜን) ከአማራ ክልል ጠራርጎ በማስወጣት ከሌሎች ክልሎች እየተፈናቀሉ ለሚመለሱ የአማራ ብሄሮች መስፈሪያ ቦታ ማዘጋጀት ዛሬውኑ ሊጀመር ይገባል፡፡ እርምጃ በሚወሰድባቸው የትግራይ ብሄሮች ላይ እርምጃ የተወሰደበትን ምክንያትና በቀጣይ እርምጃ የሚወሰድባቸውን ትግሬዎች (አጋሚዎች) ዝርዝር የያዘ ወረቀት በበድን አካላቸው ላይ መለጠፍ ይኖርበታል፡፡
    ወያኔን ከደርግ የተሻለ አድርገው በማሰብ ደርግን ገርስሶ እንዲያሰውግድ መንገዱን አልጋ ባልጋ ያደረጉ ጭቁን የአማራ ብሄረሰብ አባላት ዛሬውኑ ንሰሃ በመግባት ከሀጢያታቸው በመንጻት ትግሉን መቀላቀል ግድ ላቸዋል፡፡
    ዝምታ ችይነትና ትዕግስትን ከፍርሃት ለቆጠሩት መልስ መስጠት ውሎ ማደር አይገባውም!
    መሳሪያ ሳይሆን የሚስፈልገው ልብና ቆራጥነት ነው!
    ሞት አንድ ጊዜ ነው! ሁለት ሞት የለም!
    አትንኩኝ ሰል ለሚነኩት ተግባራዊ መልስ መስጠት ከማሰተማርም ጭምር ይቆጠራል፡፡
    ድል ለጭቁን የኢትዮጲያ ልጆች፡፡
    በተባበረ ክንድ አንኳን ሀወሀትን ጣሊያንን ትቢያ ማስገባት ተችሏል፡፡ ታሪምክ ይናገራል፡፡

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule