• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በአዲስ አበባና አካባቢ የታክሲ ሥራ ማቆም ዓድማ እየተካሄደ ነው!

February 29, 2016 01:50 am by Editor 1 Comment

የካቲት 14 የጸደቀውን በተለይ ታክሲዎችን የሚመለከተው የአሽከርካሪዎች ሕግ በመቃወም ለሁለት ቀናት የተጠራው ዓድማ በአሁኑ ጊዜ እየተካሄደ ይገኛል፡፡

በአዲስ አበባ በሁሉም ክፍለከተሞች አድማው እየተካሄደ ከመሆኑ ባሻገር ዓድማውን በመጣስ ታክሲቸውን ሲያሽከረክሩ የነበሩ “አድርባይ ሹፌሮች” ላይ በተለይ በአውቶቡስ ተራ፣ በጦር ኃይሎች እና በፈረንሣይ ሌጋሲዮን አካባ የተገኙ ታክሲያቸው ላይ ጥቃት የደረሰ መሆኑን በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ የተሰራጩት መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡

አድማው ለሰኞ እና ማክሰኞ እንደተጠራ እሁድ የካቲት 20 ህወሃት/ኢህአዴግ በግሉ በከፈተው ፋና ብሮድካስቲንግ አማካኝነት በለቀቀው መረጃ ታክሲ ነጂዎች ባቀረቡት ጥያቄ መሠረት ለሦስት ወራት ተራዝሟል ቢልም ዓድማው ግን ቀኑን ጠብቆ ተካሂዷል፡፡addis taxi

በአሁኑ ሰዓት ከተለያዩ ወገኖች የሚሰማው መረጃ እንደሚጠቁመው ዓድማው ወደ ሌሎች የክልል ከተሞች እየተዛመተ መሄዱ ተገልጾዋል፡፡ ከወልቂጤ እና ከወሊሶ አካባቢ ወደ አዲስ አበባ ተሳፋሪ የሚያመላልስ ምንም ዓይነት አገልግሎት ሰጪ እንደሌለ ይነገራል፡፡ በሌሎችም ከተሞች ማለትም በሰንዳፋ፣ በለገጣፎ፣ በቡራዩ፣ ወዘተ እንዲሁ ዓይነት ችግር እየታየ እንደሆነ እና ተሳፋሪዎች መጓጓዣ በማጣት ወደ ሥራ ለመሄድ እንደተቸገሩ የሚወጡ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡

አዲስ አበባን ለማስፋት በሚል ስም ከገበሬ ላይ መሬት እየነጠቀ ጊዜው ለፈጠራቸው የሥርዓቱ ታማኞች እና የጥቅም ተካፋዮች ለመሸንሸን የታቀደው ማስተር ፕላን ለዘመናት የተጠራቀመውን የኦሮሞ ሕዝብ ብሶት በቀሰቀሰበት ጊዜ ህወሃት/ኢህአዴግ “ትቼዋለሁ” ቢልም ማዕበሉን ግን ሊያስቆመው አልቻለም፡፡

በተመሳሳይ ሁኔታ የታክሲዎችን አድማ ለማስቆም መመሪያውን ለሦስት ወራት ህወሃት/ኢህአዴግ አራዝሜአለሁ ቢልም ዓድማውን ማስቆም እንዳልቻለ እውን ሆኗል፡፡ በኦሮሞ ክልል የሚካሄደውን ሕዝባዊ ዓመጽ ጨምሮ ይህ በከተማ የተጀመረው የታክሲ ዓድማ ለህወሃት “በዕንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ” እንደሚሆን አገዛዙን በከፍተኛ ሁኔታ ሊያሽመደምድ እንደሚችል እየተነገረ ነው፡፡  (ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. gud says

    February 29, 2016 07:20 pm at 7:20 pm

    Ye addis abeba hizb keld

    Melkamya syatu yiwetalu

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule