• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በአዲስ አበባና አካባቢ የታክሲ ሥራ ማቆም ዓድማ እየተካሄደ ነው!

February 29, 2016 01:50 am by Editor 1 Comment

የካቲት 14 የጸደቀውን በተለይ ታክሲዎችን የሚመለከተው የአሽከርካሪዎች ሕግ በመቃወም ለሁለት ቀናት የተጠራው ዓድማ በአሁኑ ጊዜ እየተካሄደ ይገኛል፡፡

በአዲስ አበባ በሁሉም ክፍለከተሞች አድማው እየተካሄደ ከመሆኑ ባሻገር ዓድማውን በመጣስ ታክሲቸውን ሲያሽከረክሩ የነበሩ “አድርባይ ሹፌሮች” ላይ በተለይ በአውቶቡስ ተራ፣ በጦር ኃይሎች እና በፈረንሣይ ሌጋሲዮን አካባ የተገኙ ታክሲያቸው ላይ ጥቃት የደረሰ መሆኑን በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ የተሰራጩት መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡

አድማው ለሰኞ እና ማክሰኞ እንደተጠራ እሁድ የካቲት 20 ህወሃት/ኢህአዴግ በግሉ በከፈተው ፋና ብሮድካስቲንግ አማካኝነት በለቀቀው መረጃ ታክሲ ነጂዎች ባቀረቡት ጥያቄ መሠረት ለሦስት ወራት ተራዝሟል ቢልም ዓድማው ግን ቀኑን ጠብቆ ተካሂዷል፡፡addis taxi

በአሁኑ ሰዓት ከተለያዩ ወገኖች የሚሰማው መረጃ እንደሚጠቁመው ዓድማው ወደ ሌሎች የክልል ከተሞች እየተዛመተ መሄዱ ተገልጾዋል፡፡ ከወልቂጤ እና ከወሊሶ አካባቢ ወደ አዲስ አበባ ተሳፋሪ የሚያመላልስ ምንም ዓይነት አገልግሎት ሰጪ እንደሌለ ይነገራል፡፡ በሌሎችም ከተሞች ማለትም በሰንዳፋ፣ በለገጣፎ፣ በቡራዩ፣ ወዘተ እንዲሁ ዓይነት ችግር እየታየ እንደሆነ እና ተሳፋሪዎች መጓጓዣ በማጣት ወደ ሥራ ለመሄድ እንደተቸገሩ የሚወጡ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡

አዲስ አበባን ለማስፋት በሚል ስም ከገበሬ ላይ መሬት እየነጠቀ ጊዜው ለፈጠራቸው የሥርዓቱ ታማኞች እና የጥቅም ተካፋዮች ለመሸንሸን የታቀደው ማስተር ፕላን ለዘመናት የተጠራቀመውን የኦሮሞ ሕዝብ ብሶት በቀሰቀሰበት ጊዜ ህወሃት/ኢህአዴግ “ትቼዋለሁ” ቢልም ማዕበሉን ግን ሊያስቆመው አልቻለም፡፡

በተመሳሳይ ሁኔታ የታክሲዎችን አድማ ለማስቆም መመሪያውን ለሦስት ወራት ህወሃት/ኢህአዴግ አራዝሜአለሁ ቢልም ዓድማውን ማስቆም እንዳልቻለ እውን ሆኗል፡፡ በኦሮሞ ክልል የሚካሄደውን ሕዝባዊ ዓመጽ ጨምሮ ይህ በከተማ የተጀመረው የታክሲ ዓድማ ለህወሃት “በዕንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ” እንደሚሆን አገዛዙን በከፍተኛ ሁኔታ ሊያሽመደምድ እንደሚችል እየተነገረ ነው፡፡  (ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. gud says

    February 29, 2016 07:20 pm at 7:20 pm

    Ye addis abeba hizb keld

    Melkamya syatu yiwetalu

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule