• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“በኢትዮጵያዊያን የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት ሀገሪቱን ማተራመስ አለብን” አይማን አብድልአዚዝ ግብጻዊው ፖለቲከኛ

July 5, 2022 12:57 pm by Editor Leave a Comment

በግብጽ በጣም ታዋቂ ፓለቲከኛ ነው። በአገሪቷ የ2005ቱ ምርጫ የቀድሞውን ፕሬዘዳንት ሆስኒ ሙባረክን የተገዳደረ ብቸኛው ሰው ሲሆን የግብጽ ፓርላማ አባልም ነበር።

የኤል ጋህድ ፓርቲ መስራችና ለሊቀመንበር ሲሆን በግብጽ ካሉ ከባድ ሚዛን ፓለቲከኞች አንዱ ነው፤ አይማን አብድልአዚዝ ኑር።

ይህ ግብጻዊ ፓለቲከኛ በይፋ በሚናገርበት አንድ ቪዲዮ ያስተላለፈው መልዕክት አሁን በኢትዮጵያ ላይ ከሚታዩት የጽንፈኞችና አሸባሪዎች ድርጊት ጀርባ ግብጻዊያን የደህንነት ሰዎች እጃቸው እንዳለበት አመላካች ነው።

ግለሰቡ በዚሁ ስብሰባ ላይ “ይህንን ጉዳይ በግል መናገር ይኑርብኝ አይኑርብኝ አላውቅም፤ ነገር ግን ከእኔ በፊት እንደተናገሩት ጓደኞቼ ሁሉ እኔም የምለው በኢትዮጵያ ውስጥ አሁን የሚታዩ ለውጦችን መጠቀም አለብን” ሲል ይናገራል።

በአትዮጵያ ውስጥ በርካታ የፖለቲካ ተፎካከሪዎች አሉ በማለት እነዚህን ሃይሎች መጠቀም እንደሚገባ የሚጠቅሰው አይማን አብድልአዚዝ፤ “ኢትዮጵያ ውስጥ ኤምባሲ አያስፈልገንም ይልቁንም የሚያስፈልገን በፖለቲካ እና በደህንነት ጉዳዮች ላይ የሚሰራ ግብረ ሃይል ነው” ሲል እቅዳቸውን በግልጽ አስቀምጧል።

በኢትዮጵያ ሁሉም ጉዳዮች ላይ የራሳችንን ሚና መጫዎት አለብን፤ እኔ እንደማስበው ስጋታችንን ለመቀልበስ በጣም አዋጭና በትንሽ ዋጋ የምንጠቀምበት አማራጭ ይህ ነው፤ በኢትዮጵያዊያን የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት ሀገሪቱን ማተራመስ አለብን” ሲልም ነው አይማን አብድልአዚዝ ኢትዮጵያን ስለማተራመስ መልዕክቱን በግልጽ ያስተላለፈው።

በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች የሚፈጸሙ የንጹሀን ግድያዎች በአሸባሪዎቹ ሸኔ እና ህወሓት የሚፈጸሙ ቢሆንም በዋናነት ከእነዘህ ግድያዎች ጀርባ መንግስት እና የተለያዮ የፓለቲካ ተንታኞች በተደጋጋሚ የውጭ አገራት እጅ እንዳለበት እያስታወቁ ይገኛሉ።

በተመሳሳይም ሱዳን የፈጸመችው የድንበር ወረራና ትንኮሳ የሶስተኛ አገር አጀንዳን ለማስፈጸም እንደሆነ ሲነገር ሰምተናል።

በቅርቡ አስተያየት የሰጡ ረ/ፕሮፌሰር ጌትነት አልማው እንደሚሉት የኢትዮጵያ እድልና ፈተና ከሶት ነገሮች ጋር የተያያዘ ነው። ቀይ ባህር፣ አባይ እና አድዋ ናቸው።

እነዚህ ሶስት ዋና ዋና ጉዳዮች ስለኢትዮጵያ እድልም ተስፋም ናቸው የሚሉት ረ/ፕሮፌሰሩ አሁን ላይ የሚያጋጥሙን ፈተናዎች ከነዚህ ጉዳዮች ጋር ጥብቅ ቁርኝት እንዳላቸው እና ግብጽን ጨምሮ በቀጠናው የበላይነት ለመያዝ የሚጥሩ ሃይሎች የፈተናዎቻችን ምንጮች እንደሆኑ ያብራራሉ።

ይህንን የረ/ፕሮፌሰሩን ሃሳብ የሚያጠናክረው ደግሞ “በኢትዮጵያ ኤምባሲ ከፍተን የምናደርገው ድርድር በአባይ ላይ ያለንን ጥቅም አያስጠብቅልንም፤ ይልቁንም ኤምባሲያችንን ዘግተን በኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ የደህንነት ስራችንን በማጠናከር ሀገሪቱን ማተራመስ አለብን” የሚለው የግብጻዊያን ፓለቲከኞች ምክክር ነው። (ኢ ፕ ድ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, Politics Tagged With: Egypt, GERD, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule