• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“በኢትዮጵያዊያን የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት ሀገሪቱን ማተራመስ አለብን” አይማን አብድልአዚዝ ግብጻዊው ፖለቲከኛ

July 5, 2022 12:57 pm by Editor Leave a Comment

በግብጽ በጣም ታዋቂ ፓለቲከኛ ነው። በአገሪቷ የ2005ቱ ምርጫ የቀድሞውን ፕሬዘዳንት ሆስኒ ሙባረክን የተገዳደረ ብቸኛው ሰው ሲሆን የግብጽ ፓርላማ አባልም ነበር።

የኤል ጋህድ ፓርቲ መስራችና ለሊቀመንበር ሲሆን በግብጽ ካሉ ከባድ ሚዛን ፓለቲከኞች አንዱ ነው፤ አይማን አብድልአዚዝ ኑር።

ይህ ግብጻዊ ፓለቲከኛ በይፋ በሚናገርበት አንድ ቪዲዮ ያስተላለፈው መልዕክት አሁን በኢትዮጵያ ላይ ከሚታዩት የጽንፈኞችና አሸባሪዎች ድርጊት ጀርባ ግብጻዊያን የደህንነት ሰዎች እጃቸው እንዳለበት አመላካች ነው።

ግለሰቡ በዚሁ ስብሰባ ላይ “ይህንን ጉዳይ በግል መናገር ይኑርብኝ አይኑርብኝ አላውቅም፤ ነገር ግን ከእኔ በፊት እንደተናገሩት ጓደኞቼ ሁሉ እኔም የምለው በኢትዮጵያ ውስጥ አሁን የሚታዩ ለውጦችን መጠቀም አለብን” ሲል ይናገራል።

በአትዮጵያ ውስጥ በርካታ የፖለቲካ ተፎካከሪዎች አሉ በማለት እነዚህን ሃይሎች መጠቀም እንደሚገባ የሚጠቅሰው አይማን አብድልአዚዝ፤ “ኢትዮጵያ ውስጥ ኤምባሲ አያስፈልገንም ይልቁንም የሚያስፈልገን በፖለቲካ እና በደህንነት ጉዳዮች ላይ የሚሰራ ግብረ ሃይል ነው” ሲል እቅዳቸውን በግልጽ አስቀምጧል።

በኢትዮጵያ ሁሉም ጉዳዮች ላይ የራሳችንን ሚና መጫዎት አለብን፤ እኔ እንደማስበው ስጋታችንን ለመቀልበስ በጣም አዋጭና በትንሽ ዋጋ የምንጠቀምበት አማራጭ ይህ ነው፤ በኢትዮጵያዊያን የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት ሀገሪቱን ማተራመስ አለብን” ሲልም ነው አይማን አብድልአዚዝ ኢትዮጵያን ስለማተራመስ መልዕክቱን በግልጽ ያስተላለፈው።

በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች የሚፈጸሙ የንጹሀን ግድያዎች በአሸባሪዎቹ ሸኔ እና ህወሓት የሚፈጸሙ ቢሆንም በዋናነት ከእነዘህ ግድያዎች ጀርባ መንግስት እና የተለያዮ የፓለቲካ ተንታኞች በተደጋጋሚ የውጭ አገራት እጅ እንዳለበት እያስታወቁ ይገኛሉ።

በተመሳሳይም ሱዳን የፈጸመችው የድንበር ወረራና ትንኮሳ የሶስተኛ አገር አጀንዳን ለማስፈጸም እንደሆነ ሲነገር ሰምተናል።

በቅርቡ አስተያየት የሰጡ ረ/ፕሮፌሰር ጌትነት አልማው እንደሚሉት የኢትዮጵያ እድልና ፈተና ከሶት ነገሮች ጋር የተያያዘ ነው። ቀይ ባህር፣ አባይ እና አድዋ ናቸው።

እነዚህ ሶስት ዋና ዋና ጉዳዮች ስለኢትዮጵያ እድልም ተስፋም ናቸው የሚሉት ረ/ፕሮፌሰሩ አሁን ላይ የሚያጋጥሙን ፈተናዎች ከነዚህ ጉዳዮች ጋር ጥብቅ ቁርኝት እንዳላቸው እና ግብጽን ጨምሮ በቀጠናው የበላይነት ለመያዝ የሚጥሩ ሃይሎች የፈተናዎቻችን ምንጮች እንደሆኑ ያብራራሉ።

ይህንን የረ/ፕሮፌሰሩን ሃሳብ የሚያጠናክረው ደግሞ “በኢትዮጵያ ኤምባሲ ከፍተን የምናደርገው ድርድር በአባይ ላይ ያለንን ጥቅም አያስጠብቅልንም፤ ይልቁንም ኤምባሲያችንን ዘግተን በኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ የደህንነት ስራችንን በማጠናከር ሀገሪቱን ማተራመስ አለብን” የሚለው የግብጻዊያን ፓለቲከኞች ምክክር ነው። (ኢ ፕ ድ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, Politics Tagged With: Egypt, GERD, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule