• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አጀንዳ ካልተላከልኝ አልሰበሰብም ሲል የነበረው ሕወሓት ምርጫውን ማስቆም “ጦርነት ማወጅ ነው” አለ

September 4, 2020 11:00 am by Editor Leave a Comment

በዓለምአቀፍ የአሸባሪዎች ቋት በሽብርተኝነት እስካሁን ተመዝግቦ የሚገኘውና በትግራይ መሽጎ የተቀመጠው ህወሓት የተሰኘው የበረሃ ወንበዴዎች ቡድን ነገ ለሚደረገው የፌዴሬሽን ምክርቤት ስብሰባ አጀንዳ ካልተላከልኝ አልሰበሰብም በማለት ነሐሴ 27 ቀን 2012 ዓ.ም ለፌዴሬሽን ምክር ቤት በጻፈው ደብዳቤ አስታውቆ ነበር።

ከዚህ በመቀጠል ደግሞ አገር አስገንጣይ በረኸኞቹ የተከማቹበት ምክርቤቱ በትግራይ ክልል ሊካሄድ የታሰበውን ምርጫ ለማስቆም በፌዴሬሽን ምክር ቤት የሚተላለፍ ማንኛውም ውሳኔ ጦርነት አዋጅ እንደሚቆጥረው ባወጣው መግለጫ አስታውቋ። ከአሃዱ ሬዲዮና ከቢቢሲ አማርኛ ያወጡትን ዘገባ ከዚህ እንደሚከተለው አቅርበናል።

መግለጫው የወጣው የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ከቀናት በፊት ነገ ቅዳሜ የሚካሄድ አስቸኳይ ስብሰባን መጥራቱን አስመልክቶ ነው።

የፌዴሬሽን ምክር ቤት ለአባላቱ ባስተላለፈው ጥሪ ላይ 5ኛ የፓርላማ ዘመን 5ኛ ዓመት የሥራ ጊዜ አስቸኳይ ስብሰባ ነሐሴ 30/2012 ዓ.ም እንደሚካሄድ ከማሳወቅ ውጪ በምን አጀንዳ ላይ ውይይት እንደሚካሄድ የገለጸው ነገር ባይኖርም፤ የትግራይ ክልል ሥራ አስፈጻሚ በክልሉ በሚካሄድ ምርጫ ላይ የሚሰጥን ውሳኔ እንደማይቀበለው ከወዲሁ አሳውቋል።

የክልሉ ሥራ አስፈጻሚ መግለጫ የፌደሬሽን ምክር ቤት የጠራውን አስቸኳይ ስብሰባ “ያልተለመደና አጀንዳው የማይታወቅ” ሲል ቢጠቅሰውም በትግራይ የሚካሄደው ምርጫን የሚመለከቱ ውሳኔዎች ሊተላለፉ እንደሚችሉ ባስቀመጣቸው ሃሳቦች አመልክቷል።

የሥራ አስፈጻሚው መግለጫ እንዳለው “ምርጫውን ለማስቆም ወይም ለማደናቀፍ የፌዴሬሽን ምክር ቤት የሚወስደው ማናቸውም ውሳኔ እንደጦርነት አዋጅ ይቆጠራል” ከማለቱ በተጨማሪ “በዚህ ምክንያት ለሚፈጠር ችግር ተጠያቂው የፌዴሬሽን ምክር ቤትና ጠቅላይ ሚኒስትሩ መሆናቸው ሊታወቅ ይገባል” ሲል ብሏል።

በዚህም ምርጫውን ለማስቆም የሚተላለፍ ውሳኔ ተቀባይነት እንደሌለው በመግለጽ “ሕዝቡ በምርጫ የሚያስተዳድረውን አካል እንዲመርጥ ሊበረታታ የገባዋል እንጂ ይህን ሂደት ለማስቆም የሚደረግ ጥረት ፀረ ዲሞክራሲያዊ” መሆኑን አመልክቷል።

መግለጫው በትግራይ ክልል ስድስተኛው ዙር ምርጫ ጊዜውን ጠብቆ እንዲካሄድ ከወራት በፊት ውሳኔ መተላለፉን አስታውሶ፤ ይህንንም ለማሳካት በክልሉ ያሉት የሚመለከታቸው አካላት የሚጠበቅባቸውን እያከናወኑ በመሆናቸው ክልሉ በምርጫው “ሕግና ሥርዓትን ተከትሎ በሕዝብ ውሳኔ መሰረት ቀጣዩ የክልሉ መንግሥት የሚቋቋም ይሆናል” ብሏል።

ቀደም ሲል የትግራይ ክልል ከሌሎቹ የአገሪቱ ክልሎች በተለየ ምርጫውን በተናጠል ለመካሄድ መወሰኑን ተከትሎ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ይህ ውሳኔ ሕገወጥ መሆኑን በመግለጽ ክልሉ ምርጫ ለማካሄድ ከሚያደረገው እንቅስቃሴ እንደቆጠብ አሳስቦ ነበር። ክልሉም ይህንን በመቃወም ምላሽ ሰጥቶ ምርጫውን በማካሄድ ገፍቶ ለምርጫው ከአንድ ሳምንት ያነሰ ጊዜ ቀርቷል።

ሐሙስ ምሽት የወጣው መግለጫ ሕዝቡን በማሳተፍ ለሁሉም ግልጽ በሆነ ሁኔታ ምርጫውን ለማካሄድ ወደ ፍጻሜው መደረሱን ጠቅሶ በዚህ ጊዜ የሚደረግ ማንኛውንም ጣልቃ ገብነት “በአገሪቱ ህልውና ላይ አደጋን የሚጥል መሆኑ ሊታወቅ ይገባል” ሲል አስጠንቅቋል።

በዚህም መሰረት ምርጫው በአገሪቱና በክልሉ ሕግ መሰረት የሚካሄድ በመሆኑ በማንኛውም ጣልቃ ገብነትና ጫና ሂደቱ እንደማይቆም አመልክቶ “ሕዝቡም ይህንን ለመመከት እንዲዘጋጅ” ጥሪ ከማቅረቡ በተጨማሪ የአገሪቱ “ብሔር ብሔረሰቦችና ፌደራሊስት ኃይሎች” ከጎኑ እንዲቆሙ ጠይቋል።

በመላው አገሪቱ በነሐሴ ወር መጨረሻ ላይ ሊካሄድ ታቅዶ የበረው አገራዊና ክልላዊ ምርጫ በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ስጋት ምክንያት ለሌላ ጊዜ እንዲተላለፍ በሕዝብ ተወካዮች እና በፌዴሬሽን ምክር ቤት ቢወሰንም የትግራይ ክልል ምርጫውን በተናጠል ለማካሄድ ወስኖ ጳጉሜ 04/2012 ዓ.ም ለማካሄድ ተዘጋጅቷል።

ይህንን በተመለከተም የፌዴሬሽን ምክር ቤት በሐምሌ ወር መጨረሻ ላይ የትግራይ ክልል መንግሥት ምርጫ ለማካሄድ የሚያደርገውን እንቅስቃሴ እንዲያቆም የሚያሳስብ ደብዳቤ ለክልሉ መጻፉ ይታወሳል።

ምክር ቤቱ በዚህ ደብዳቤው ላይ እንዳመለከተው የትግራይ ክልል የተሰጠውን ማሳሰቢያ ሳይቀበል ቀርቶ “ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን አደጋ ላይ በሚጥል” ድርጊቱ የሚገፋ ከሆነ፤ የፌዴሬሽን ምክር ቤት “በሕገ መንግሥቱና በሌሎች ሕጎች የተሰጠውን ስልጣን ለመተግበር እንደሚገደድ” አስጠንቅቆ ነበር።

ለዚህም የትግራይ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባዔ በሰጡት ምላሽ የደረሳቸው ማስጠንቀቂያ ሕገ መንግሥታዊ መሰረት የሌለው መሆኑን በመግለጽ “የሕገ መንግሥት መርሆዎችን የሚጥስ፣ የብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦችን ሉአላዊ የስልጣን ባለቤትነትን የሚጻረር” በመሆኑ የትግራይ ክልል መንግሥትና ሕዝብ እንደሚቃወሙት ገልፀው እንደማይቀበሉት አሳውቀዋል።

በክልሉ የታቀደው ምርጫ ሊካሄድ ቀናት የቀሩት ሲሆን አጀንዳው ምን እንደሆነ እስካሁን ያልታወቀ አስቸኳይ ስብሰባ የፌዴሬሽን ምክርቤት ለማካሄድ ጥሪ ማቅረቡን ተከትሎ ነው የትግራይ ክልል ይህንን መግለጫ ያወጣው።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News, Politics Tagged With: fake election, tigray tplf election, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule