• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ዳር ሆነው የሚመለከቱት የጎሳ ፖለቲካ ምሱ “ደም”!!

January 27, 2014 12:55 pm by Editor 1 Comment

“ህወሃት” የሚባለው የትግራይ ነጻ አውጪ ትግራይን መቼና ከማን ነጻ እንደሚያወጣ በውል የተቆረጠ ቀን ባይኖርም ህገ መንግስታዊ ዋስትና ግን አለው በሚል እየተተቸ 23 ዓመታትን አስቆጥሯል። አገር እየመራም ነጻ አውጪ፣ በረሃም እያለ ነጻ አውጪ፣ በአህጉርና በዓለም አቀፍ ደረጃ ሲወከልም ነጻ አውጪ!!

ይህንን የተለመደና ግራ የሚያጋባ እውነት ያነሳነው ወደን አይደለም። ይህ የህወሃት ግልጽ መለያና ከመለያው የሚነሳው ትንታኔ ለማንም የተወሳሰበ ይሆናል ብለንም አንገምትም። ኢህአዴግ የሚባለው የ”ሎሌዎች” ስብስብ ያበጀውና የሚመራው ህወሃት ከሌሎቹ በተለየ በነጻ አውጪ ስም 23 ዓመት አገር ሲገዛ ሌሎቹ “የነጻ አውጪ” ስም አለመያዛቸው ግን ሁሌም ሊመረመር የሚገባው ጉዳይ ይመስለናል።

አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ “ነጻ” መውጣት ያለባቸው ህወሃቶች ሳይሆኑ ሌሎች የአገራችን ህዝቦች፣ የትግራይን ንጹሃንን ጨምሮ ነው። ህወሃት ሲጠነሰስ ጀምሮ የነበሩትን ቀደምት አመራሮች በሂደት እየበላ አራት ኪሎ የደረሰው፤ ህወሃት መጥበብ የጀመረው ገና ከጥንስሱ ጊዜ ጀምሮ ነው። ስለ ህዋሃት የሚወጡ የምስክሮች ሪፖርቶችና መረጃዎች እንደሚያረጋግጡት ህወሃት በደም የታጠበ፣ በደም የተለወሰ፣ የበርካታ ንጹሃን ደም ያጨማለቀው፣ ታሪኩ ሁሉ በደም ዙሪያ የተሰራ፣ አሁንም ከዚሁ የደም ቁማር ነጻ መሆን ያልቻለ መሆኑን ነው።

ህወሃት ግዛቱን እያሰፋ ሲሄድና አጋጣሚው ሲያመቸው ከተቋቋመለት መሰረታዊ ሃሳቡ ዘሎ “መንግስት” መሆን ሲያምረው “ኢህአዴግ” የሆነው ዓላማውን በወጉ ከ”መጥበብ ወደ መስፋት” በመቀየር ሳይሆን “በሰፍቶ መጥበብ ውስጥ” እየተጫወተ አገርና ህዝብን ረግጦ ለመግዛት ነው። ለዚህም ይመስላል ኢህአዴግን አሁን ድረስ “አገዛዝ” ከማለት በዘለለ በመንግሥትነት ሊጠሩት የማይፈልጉ የበረከቱት።

በግብር እንደታየው በህወሃት “የሰፍቶ መጥበብ” ጨዋታ ውስጥ ቅድሚያ ትግራይ መወለድ፣ ሲቀጥል የትውልድ ቦታንና ስምን በመቀየር ማጭበርበር፣ ከዛም ታማኝ መሆን፣ ከሁሉም በላይ አነስተኛ ክልል በሚል ስልታዊ አካሄድ ብርና ኮብራ እየሸለሙ ማታለል፣ የአገዛዙ መለያ ሆነ። አሁን ድረስም ይዘቱ ባይቀየርም አፈጻጸሙ ግን ከክልል ወደ አውራጃ፣ ከአውራጃም ወደ ወረዳና ቀበሌ፣ ከወረዳና ቀበሌ ወርዶ ስጋና ደም የሚቆጠርበት የስልጣን ቅርምት ደረጃ “እድገት” አሳይቶ ይገኛል።

በዚህ መልክ በተዋቀረው የህወሃት አገዛዝ ቁጥጥርና ክትትል አስቸጋሪ በመሆኑ አገሪቱ በሙስና በሰበሰች። ሙስናው ፈር ለቅቆ በድሃው ህዝብ ላይ ነገሰ። አወቃቀሩ ስርዓቱን በመታደግ ላይ የተመሰረተና የህወሃትን ባለጊዜዎች ስልጣን ማስጠበቅ በመሆኑ ሁሉም ነገር ሸተተ፤ ገለማ። ያቋራጭ ሃብታሞች ናኙ። ግንባታው ጨሰ። “ህዳሴው” ለተወሰኑ ወገኖች ፈንጠዝያ የተሰጠ ስያሜ ሆነ። ግድያ፣ እስር፣ እንግልትና አፈና እደግ ተመንደግ ተባለ። ነገሩ እንዲስተካከል ትግል የሞከሩ ተባረሩ፣ ታሰሩ፣ የተገደሉም አሉ። የተሰደዱ ጥቂት አይደሉም። አገር ውስጥ የቁም እስረኛ ሆነው ጊዜ የሚጠብቁ ቁጥራቸው ቀላል አይደለም።

ሲጀመር በብሔር ብሔረሰቦች ስም ሲምሉና ሲገዘቱ የነበሩት የህወሃት መሪዎች፣ የራሳቸውን ሰዎች ሳይቀር ወረዳ እየለዩ የፈጸመባቸው ተግባር፣ በሌሎች የአገሪቱ ህዝቦች ላይ ከስርዓቱ መርህ በመነሳትና “በጥጋብ” የተፈጸመው በደል፤ “የገዢው መደብ ነኝ” በሚል ንጹሃንን ከስራና ከሃብታቸው ከማፈናቀል ጀምሮ የተሰራባቸው ግፍ ከጎሳ ፖለቲካ ፕሮፓጋንዳ ጋር ተዳምሮ የተካረረ ደረጃ ደርሷል።

የከፋቸው በዝተው ቂማቸው እየተናነቃቸው ይገኛሉ። የህወሃት አመራሮች ከፊታቸው ክፉ ዘመን ስለመኖሩ ብዙም የተጨነቁ አይመስሉም። የቂም በትር ቀጠሮ የለውም። ቂም ቦታ አይመርጥም። የጎሳ ፖለቲካ በባህሪው ምሱ ደም ነው። የጎሳ ጣጣ ባለባቸው አገሮች የታየው ይኸው እውነት ነው። በተለይ ህወሃቶች አሁን ባጨመላለቁት ደረጃ እንለካው ከተባለ አደጋ አለ፤ ያውም ግልጽ የሆነ አደጋ። ችግሩ ሲነሳ፣ ቂም በትር ሲሰነዝር፣ ጥላቻ ልጓሙ ሲበጠስ፣ በብርና በመሳሪያ ብዛት መታደግ የሚቻል አይሆንም። ይህንን ስንል ላገራችን ችግርና የደም አታሞ ለመምታት አይደለም። የቆምንለት ዓላማና የሙያ ቃልኪዳናችን ከጎሠኝነት ይልቅ ሰብዓዊነትን ማስቀደም መሆኑን የሚጠሉንም ጭምር ያውቁታል፡፡ በዚህ የሰፋ ራዕይ ውስጥ ስላለን የመጥበብ አደጋ ምን እንደሆነ በግልጽ ይታየናል፡፡ ስለዚህ የአደጋ ማስጠንቀቂያ እንሰጣለን፡፡

ዛሬ ዳር ቆመን የምንመለከተው የጎረቤታችን ደቡብ ሱዳን የጎሳና የዘር ጭፍጭፍ “እኛም ቤት እሳት አለ” ስለሚያሰኝ ነው። የሚታሰሩ፣ የሚገረፉ፣ የበይ ተመልካች የሆኑ፣ የተገደሉ፣ አሁን ድረስ በስቃይ ላይ ያሉ … ቤቱ ይቁጠራቸውና ዘመድ፣ ወገን፣ ተቆርቋሪ፣ አለኝታ፣ ታዳጊ አላቸው። ብሶት ህወሃትን ብቻ አይወልድምና ሁሉም ረጋ ብሎ ያስብ። ህወሃት ብቻ የብሶት የበኩር ልጅ አይደለም፤ ሊሆንም አይችልም። ሲያሻ ህግ እየተጠቀሰ፣ ሲያሻ በተቀነባበረ ድራማ፣ ሲፈለግ በተፈለገው መንገድ የሚፈነጭበት ጊዜ ሳያረጅ ለሰላም ሁሉም እጁን ያንሳ!! የጎሳ ፖለቲካ ምሱ ደም ነውና ሃዘን ሳይመታን በእውነተኛ እርቅ ጊዜው ሳያልፍብን የጎሳ ፖለቲካን ምስ እናምክን!! ተቃዋሚዎችም ጭምር!!


ይህ ርዕሰ አንቀጽ የ“ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ®” አቋም ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Editorial Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Ibsa Harerge says

    January 28, 2014 03:50 pm at 3:50 pm

    Bielive it or not TPLF & its pumpet parties will pay for all what they did in the last 23 within a short parody of time. They sow huteranse amoung the people to divert the attention so that they can smoothly transport the GOLD from LEGEDEMBI and other resources from all over the country by luphtanza air plane. no body is questioning them.They do lots of homeworks especially on Oromos so that such a great nation will not collabrate with others in the way to bring justice and democracy to the country. I think it is time for We(Oromos) to be wise in collaborating with others to bring democracy to this country. if there is democracy and justice all over the country WE Oromos are the first benificiaries. Course we will test it with all others as Human beings. let us collabrate for Justice by turning deaf ear to TPLF who plant huteranse amoung different groups.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm
  • “ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንግቤ እዋጋለሁ” የሚሉ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል – የመከላከያ ሠራዊት August 1, 2023 09:25 am
  • ደቡብ አፍሪካ የመሸጉ ወንጀለኞች ለሕግ ተላልፈው ሊሰጡ ነው July 31, 2023 09:27 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule