• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኦፌኮ ከለዘብተነት ወደ ነውጠኝነት

January 20, 2020 08:13 am by Editor Leave a Comment

ህግ ያልገዛውን ሀይል ይገዛዋል

ዛሬ ጦርነቱ ግልፅ ሆኗል። ኦፌኮ መንግሥትን ምንም አታመጣም እስኪ የምታደርገውን አይሃለሁ እያለው ነው። ኦቦ መረራ በስተርጅና ዋልታ ረገጥ ሆነው ፈንድተዋል። ሀይማኖት ውስጥ ያሸመቁ መናፍቃን ባደባባይ ፖለቲካውን ተቀላቅለዋል። ነውጠኛው ጃዋር ራሱን እንደ አሜባ አራብቷል። ጦርነቱ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ላይ ብቻ ላይ አይደለም ያጠነጠነው የሀገሪቱን መሰረት የመፈነቃቀል ስትራቴጂ ፊት ለፊት አንግቦ እንጂ።

ይህ ሀገር ላይ የተመዘዘ ሰይፍ የቱንም እምነት አይምርም። ሀገር ሳለች ነው እምነት፣ ክብርም፣ ራሱ መኖርም። ማንም ራሱን ካላሞኘ በስተቀር፣ ሁሉም በሰላም በማይኖርባት አገር ውስጥ የብቻዬን የሰላም ደሴት እፈጥራለሁ ሊል የሚቻለው አይደለም። እነሆ ዛሬ አንዳች ስውር፣ አንዳች ያልተገለጠ ምስጢር የለም። ዕቅዱ በገሀድ መተግበር ጀምሯል።

የባንዲራ መቃጠል፣ መረገጥና መዋረድ ሀገሪቱን ሊገጥማት ከሚችለው አደጋ አኳያ እየተስተዋለ ይሰጠው የነበረው አፀፋ እጅግ የለዘበ ነበር። ይህ አስተውሎና ሀላፊነት የተሞላው እሳቤ የነውጠኞችን ልብ ከማሳበጥና የአሸናፊነት ስነልቦናን እንዲጎናፀፉ ከማድረግ በቀር አንዳች ሲፈይድ አልታየም።

ዘለግ ብሎ ላሰበው ይቺ ሰንደቅ የተቀዳችው ከማርያም መቀነት ነው መባሉ የልዩነት ብሎም የመካረር ምክንያት ባልሆነ ነበር። እናታችን ማርያም በሁሉም ሀይማኖቶች ቅድስት ነችና። ቀስተዳመናም ቢሆን ለሁላችን አንድ በሆነው ሰማይ ላይ የሚዘረጋ፣ ላይናችን ትሩፋት፣ ለልባችን ትፍስህት የሆነ የፈጣሪ ድንቅ ጥበብ ነበር። አሁን ማ ይሙት ሰማዩ በቀስተዳመና ጥለት ሲጎናፀፍ ተመልክቶ ሀሴት የማያደርግ ሰብአዊ ፍጡር ለመሆኑ ማን ይሆን?

ጎበዝ ነገሩ ሁሉ እንዳይጥም እንዳይጥም እየሆነ ነው። እስኪ አሁን ይቺ መከረኛ ቤተክርስቲያን ማንን አሳልማ ነው ማንን የነፈገችው? እውን ለብርሀኑ የተዘረጋ መስቀል ለመረራ ታጠፈ? እስኪ አሁን መራራን የትኛው ካህን፣ የትኛው ደብር ነው መስቀል እንዳይሳለሙ ያቀባቸው?

ሰማእቱ አባታች ብፁእ አቡነ ጴጥሮስ “ምነው ኢትዮጵያን ጨከንሽባት፣ ምነው መቀነትሽን ታብቂባባት” አሉ እንጂ የት ጋር ነው ኦሮሚያ የሚል ቃል ካንደበታቸው የወጣው? ከነከሳት መርዝ ልቅመስ በፈጃት እቶን ልንደድላት ያሉት ለእምዬ ኢትዮጵያ እንጂ ለኦሮሚያ ነበርን?

አገር ከፈረሰ፣ እምነት ከተፋለሰ በኋላ ምን ላይ ተቆሞ ነው ዴሞክራሲውስ የሚገነባው፣ ፍትሁስ የሚበየነው? መንግስት ባለበት ሀገረመንግስት ባደባባይ የምፅአት ቀን ሲታወጅ ለማን አቤት ይሏል።

የኦሮሚያ ፖለቲካ የመናፍቃን ዋሻ ሆኗል። የአክራሪዎች ሰይፍ በቅድስት ቤተክርስቲያን ላይ ተመዟል። ሸዋ በራሱ ቤተክርስቲያን ላይ ጦር እንዲሰብቅ ክተት ተብሏል። ክርስቲያን በክርስቲያን ላይ እንዲነሳ ነጋሪት ተጎስሟል። የገብረጉራቻ ህዝብ አባት አያቱ በደም ሳይቀር፣ በነብስ ሳይቀር የተዋጁላትን እምነቱን እንድትዋረድ፣ እንድትመክን የጃዋር አበጋዝ የእርኩሰት መነባንቡን ሲያዝረበርብ ተስተውሏል። ደብረሊባኖስ በፅንፈኞች መዳፍ ስር እንድትወድቅ በፒኮሎው ጃዋር በኩል ቄሮና ቀሬ ክተቱ ተብለዋል። ይህ እየሆነ ያለው ኦፌኮ በሚዘውረው፣ ጃዋር በሚሾፍረው የአክራሪዎች ጎራ ነው።

እዚህ ከተደረሰ ቀጣዩን ለመተንበይ ጠንቋይ መሆን አያስፈልግም። ካህናትን እረዱ፣ ምእመናንን ጨፍጭፉ፣ አብያተ ክርስቲያናትን አቃጥሉ መባሉ ሳይታለም የተፈታ ነው።

እቺ ቤተክርስቲያን ጠላቶቿ ተበራክቷል። ከከፍታዋ ለማውረድ፣ ክብሯን ለመናድ፣ ህልውናዋን ለማጥፋት ረጅም፣ በጣም ረጅም መንገድ ተኬዷል።

መላው የእስልምናም፣ የፕሮቴስታንትም ሆነ የዋቄፌታ አማኞች ከዚች ግፉእ ቤተክርስቲያን ጎን ልትቆሙ ይገባል። የአንዱ መኖር ለሌላው ዋስትና እንጂ ጠር አይደለም። ካንዱ በደል ሌላው ቢያጎል እንጂ አይከስብም።

ቤተክርስቲያንም ብትሆን ምእመኑን ከአመፅ ማቀቧ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ ከአመፅ በመለስ ባሉ ማናቸውም ተቃውሞዎች ጎምዘዝ ኮምጨጭ ማለት አለባት። አባቶች የጀመሩትን እስኪጨርሱ ድረስ መዘናጋት የለባቸውም። ስሜት ሲንር ጠብቆ የሚፈነዳ፣ አንዴ ቦግ አንዴ እልም የሚል ሳይሆን ግብ ሳይደርስ የማይቆም ትግል ያስፈልጋል። ፅንፈኞች የሚዘሯቸው መርዞች በህግ አግባብ እየተነቀሱ በሰላማዊ መንገድ ለህግ አስፈፃሚ አካላት እንዲቀርቡ ሊደረግ ይገባል።

የፖለቲካ ድርጅቶችም ከትርምስ ለማትረፍ፣ ጠላትን ለመቀጥቀጥና ሌላ ፅንፍ ለማደራጀት ከመጠቀም ይልቅ መንግስት ላይ ጠንካራ ተፅእኖ በማሳረፍ፣ ለምርጫ ቦርድ የተሰነዱ መረጃዎችን በማቅረብ፣ ጠቅላይ አቃቤ ህግም በነዚህ ወንጀለኞች ላይ ክስ እንዲመሰረት ለማድረግ በዚህና በዚህ መሰል እውነቶች ላይ አንድነት ልትፈጥሩ ይገባል። ለምርጫ ቦርድም እንዲህ አይነት አካሄዶችን በዝምታ ማለፍ ሌሎች ተመሳሳይ ድርጊቶችን ማስከተሉ አይቀርምና፣ አሁን ያልተወሰደ እርምጃ ለወደፊቱ በሚደረጉ ተመሳሳይ ድርጊቶች ላይ ህጋዊ እርምጃ ለመውሰድ የሞራል ልእልናን ያሳጣልና፣ ጠንከር ያለ ህጋዊ እሮምጃ መውሰድ የጊዜው አይታለፍ ጥያቄ ነው።

መንግስት እንደመንግሥት መከበር፣ መታፈር አለበት። መንግሥት እንደ መንግሥት መከበርና መታፈር ካልቻለ የሚዋረደው ህዝብ ነው፣ የሚደፈረው ሀገር ነው። ስለዚህ ለህግ አንገዛም ላለ ሞገደኛ ሀይል ጉልበት አማራጭ ሆኖ ሊገራው ይገባል። ያለችን አንድ ሀገር ናት፣ ልንኮራባትና ልንታበይባት ሲገባን እስከመቼ ተሸማቀንና ተሸምቀን እንኑርባት። እስከመቼ ባበጡ ተረኞች አንገታችን ይሰበር፣ ልባችንስ እንክት ይበል። መረጥንህም አልመረጥንህም ሀገራችን በእጅህ ናትና ትጠብቃት ትታደጋት ዘንድ ግዴታም አደራም አለብህና ኢትዮጲያ ከነውጠኞች ከአክራሪዎች ፍላፃ ጠብቃት። ጉልበት ለጉልበተኞች ግድ ነው። ህግ ያልገዛውን ሀይል ይገዛዋል።

ፈጣሪ ኢትዮጵያን አብዝቶ ይባርክ

Wondemagegnehu Addis


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions, Social Tagged With: hailemichael, jawar massacre, ofc, Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule