• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኦፌኮ ከለዘብተነት ወደ ነውጠኝነት

January 20, 2020 08:13 am by Editor Leave a Comment

ህግ ያልገዛውን ሀይል ይገዛዋል

ዛሬ ጦርነቱ ግልፅ ሆኗል። ኦፌኮ መንግሥትን ምንም አታመጣም እስኪ የምታደርገውን አይሃለሁ እያለው ነው። ኦቦ መረራ በስተርጅና ዋልታ ረገጥ ሆነው ፈንድተዋል። ሀይማኖት ውስጥ ያሸመቁ መናፍቃን ባደባባይ ፖለቲካውን ተቀላቅለዋል። ነውጠኛው ጃዋር ራሱን እንደ አሜባ አራብቷል። ጦርነቱ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ላይ ብቻ ላይ አይደለም ያጠነጠነው የሀገሪቱን መሰረት የመፈነቃቀል ስትራቴጂ ፊት ለፊት አንግቦ እንጂ።

ይህ ሀገር ላይ የተመዘዘ ሰይፍ የቱንም እምነት አይምርም። ሀገር ሳለች ነው እምነት፣ ክብርም፣ ራሱ መኖርም። ማንም ራሱን ካላሞኘ በስተቀር፣ ሁሉም በሰላም በማይኖርባት አገር ውስጥ የብቻዬን የሰላም ደሴት እፈጥራለሁ ሊል የሚቻለው አይደለም። እነሆ ዛሬ አንዳች ስውር፣ አንዳች ያልተገለጠ ምስጢር የለም። ዕቅዱ በገሀድ መተግበር ጀምሯል።

የባንዲራ መቃጠል፣ መረገጥና መዋረድ ሀገሪቱን ሊገጥማት ከሚችለው አደጋ አኳያ እየተስተዋለ ይሰጠው የነበረው አፀፋ እጅግ የለዘበ ነበር። ይህ አስተውሎና ሀላፊነት የተሞላው እሳቤ የነውጠኞችን ልብ ከማሳበጥና የአሸናፊነት ስነልቦናን እንዲጎናፀፉ ከማድረግ በቀር አንዳች ሲፈይድ አልታየም።

ዘለግ ብሎ ላሰበው ይቺ ሰንደቅ የተቀዳችው ከማርያም መቀነት ነው መባሉ የልዩነት ብሎም የመካረር ምክንያት ባልሆነ ነበር። እናታችን ማርያም በሁሉም ሀይማኖቶች ቅድስት ነችና። ቀስተዳመናም ቢሆን ለሁላችን አንድ በሆነው ሰማይ ላይ የሚዘረጋ፣ ላይናችን ትሩፋት፣ ለልባችን ትፍስህት የሆነ የፈጣሪ ድንቅ ጥበብ ነበር። አሁን ማ ይሙት ሰማዩ በቀስተዳመና ጥለት ሲጎናፀፍ ተመልክቶ ሀሴት የማያደርግ ሰብአዊ ፍጡር ለመሆኑ ማን ይሆን?

ጎበዝ ነገሩ ሁሉ እንዳይጥም እንዳይጥም እየሆነ ነው። እስኪ አሁን ይቺ መከረኛ ቤተክርስቲያን ማንን አሳልማ ነው ማንን የነፈገችው? እውን ለብርሀኑ የተዘረጋ መስቀል ለመረራ ታጠፈ? እስኪ አሁን መራራን የትኛው ካህን፣ የትኛው ደብር ነው መስቀል እንዳይሳለሙ ያቀባቸው?

ሰማእቱ አባታች ብፁእ አቡነ ጴጥሮስ “ምነው ኢትዮጵያን ጨከንሽባት፣ ምነው መቀነትሽን ታብቂባባት” አሉ እንጂ የት ጋር ነው ኦሮሚያ የሚል ቃል ካንደበታቸው የወጣው? ከነከሳት መርዝ ልቅመስ በፈጃት እቶን ልንደድላት ያሉት ለእምዬ ኢትዮጵያ እንጂ ለኦሮሚያ ነበርን?

አገር ከፈረሰ፣ እምነት ከተፋለሰ በኋላ ምን ላይ ተቆሞ ነው ዴሞክራሲውስ የሚገነባው፣ ፍትሁስ የሚበየነው? መንግስት ባለበት ሀገረመንግስት ባደባባይ የምፅአት ቀን ሲታወጅ ለማን አቤት ይሏል።

የኦሮሚያ ፖለቲካ የመናፍቃን ዋሻ ሆኗል። የአክራሪዎች ሰይፍ በቅድስት ቤተክርስቲያን ላይ ተመዟል። ሸዋ በራሱ ቤተክርስቲያን ላይ ጦር እንዲሰብቅ ክተት ተብሏል። ክርስቲያን በክርስቲያን ላይ እንዲነሳ ነጋሪት ተጎስሟል። የገብረጉራቻ ህዝብ አባት አያቱ በደም ሳይቀር፣ በነብስ ሳይቀር የተዋጁላትን እምነቱን እንድትዋረድ፣ እንድትመክን የጃዋር አበጋዝ የእርኩሰት መነባንቡን ሲያዝረበርብ ተስተውሏል። ደብረሊባኖስ በፅንፈኞች መዳፍ ስር እንድትወድቅ በፒኮሎው ጃዋር በኩል ቄሮና ቀሬ ክተቱ ተብለዋል። ይህ እየሆነ ያለው ኦፌኮ በሚዘውረው፣ ጃዋር በሚሾፍረው የአክራሪዎች ጎራ ነው።

እዚህ ከተደረሰ ቀጣዩን ለመተንበይ ጠንቋይ መሆን አያስፈልግም። ካህናትን እረዱ፣ ምእመናንን ጨፍጭፉ፣ አብያተ ክርስቲያናትን አቃጥሉ መባሉ ሳይታለም የተፈታ ነው።

እቺ ቤተክርስቲያን ጠላቶቿ ተበራክቷል። ከከፍታዋ ለማውረድ፣ ክብሯን ለመናድ፣ ህልውናዋን ለማጥፋት ረጅም፣ በጣም ረጅም መንገድ ተኬዷል።

መላው የእስልምናም፣ የፕሮቴስታንትም ሆነ የዋቄፌታ አማኞች ከዚች ግፉእ ቤተክርስቲያን ጎን ልትቆሙ ይገባል። የአንዱ መኖር ለሌላው ዋስትና እንጂ ጠር አይደለም። ካንዱ በደል ሌላው ቢያጎል እንጂ አይከስብም።

ቤተክርስቲያንም ብትሆን ምእመኑን ከአመፅ ማቀቧ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ ከአመፅ በመለስ ባሉ ማናቸውም ተቃውሞዎች ጎምዘዝ ኮምጨጭ ማለት አለባት። አባቶች የጀመሩትን እስኪጨርሱ ድረስ መዘናጋት የለባቸውም። ስሜት ሲንር ጠብቆ የሚፈነዳ፣ አንዴ ቦግ አንዴ እልም የሚል ሳይሆን ግብ ሳይደርስ የማይቆም ትግል ያስፈልጋል። ፅንፈኞች የሚዘሯቸው መርዞች በህግ አግባብ እየተነቀሱ በሰላማዊ መንገድ ለህግ አስፈፃሚ አካላት እንዲቀርቡ ሊደረግ ይገባል።

የፖለቲካ ድርጅቶችም ከትርምስ ለማትረፍ፣ ጠላትን ለመቀጥቀጥና ሌላ ፅንፍ ለማደራጀት ከመጠቀም ይልቅ መንግስት ላይ ጠንካራ ተፅእኖ በማሳረፍ፣ ለምርጫ ቦርድ የተሰነዱ መረጃዎችን በማቅረብ፣ ጠቅላይ አቃቤ ህግም በነዚህ ወንጀለኞች ላይ ክስ እንዲመሰረት ለማድረግ በዚህና በዚህ መሰል እውነቶች ላይ አንድነት ልትፈጥሩ ይገባል። ለምርጫ ቦርድም እንዲህ አይነት አካሄዶችን በዝምታ ማለፍ ሌሎች ተመሳሳይ ድርጊቶችን ማስከተሉ አይቀርምና፣ አሁን ያልተወሰደ እርምጃ ለወደፊቱ በሚደረጉ ተመሳሳይ ድርጊቶች ላይ ህጋዊ እርምጃ ለመውሰድ የሞራል ልእልናን ያሳጣልና፣ ጠንከር ያለ ህጋዊ እሮምጃ መውሰድ የጊዜው አይታለፍ ጥያቄ ነው።

መንግስት እንደመንግሥት መከበር፣ መታፈር አለበት። መንግሥት እንደ መንግሥት መከበርና መታፈር ካልቻለ የሚዋረደው ህዝብ ነው፣ የሚደፈረው ሀገር ነው። ስለዚህ ለህግ አንገዛም ላለ ሞገደኛ ሀይል ጉልበት አማራጭ ሆኖ ሊገራው ይገባል። ያለችን አንድ ሀገር ናት፣ ልንኮራባትና ልንታበይባት ሲገባን እስከመቼ ተሸማቀንና ተሸምቀን እንኑርባት። እስከመቼ ባበጡ ተረኞች አንገታችን ይሰበር፣ ልባችንስ እንክት ይበል። መረጥንህም አልመረጥንህም ሀገራችን በእጅህ ናትና ትጠብቃት ትታደጋት ዘንድ ግዴታም አደራም አለብህና ኢትዮጲያ ከነውጠኞች ከአክራሪዎች ፍላፃ ጠብቃት። ጉልበት ለጉልበተኞች ግድ ነው። ህግ ያልገዛውን ሀይል ይገዛዋል።

ፈጣሪ ኢትዮጵያን አብዝቶ ይባርክ

Wondemagegnehu Addis


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions, Social Tagged With: hailemichael, jawar massacre, ofc, Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule