• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከመስከረም 25 በኋላ “መንግሥት የለም” በሚል ትርምስ ለመፍጠር በሚሰሩ አካላት ላይ እርምጃ እወስዳለሁ – የፌዴራል ፖሊስ

September 25, 2020 02:43 pm by Editor 2 Comments

የፌዴራል ፖሊስ ጥብቅ ፍተሻ እያደረገ ያለው ከአማራ ክልል በሚመጡ መንገደኞች ብቻ ሳይሆን ወደ መዲናዋ በሚያስገቡ በሁሉም በሮች ላይ ተመሳሳይ የቁጥጥር ስራ እየሰራ መሆኑን አስታወቀ።

የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል እንደሻው ጣሰው ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ የመስቀል ደመራ እና የኢሬቻ በአልን ምክኒያት በማድረግ በአዲስ አበባ የሽብር ድርጊት ለመፈጸም እና ይህንኑ ተከትሎ ሁከት እና ግጭት እንዲፈጠር በዝግጅት ላይ የሚገኙ አካላት እንዳሉ ደርሰንበታል ያሉት ኮሚሽነር ጄኔራሉ መረጃውን መሰረት በማድረግ ወደ አዲስ አበባ በሚያስገቡ በሁሉም በሮች ላይ ጥብቅ ፍተሻ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል ።

የበዓሉን እንቅስቃሴ ለማደፍረስ ዕቅድ ያላቸው ሀይሎች እንዳሉ ፖሊስ በምርመራ እንደደረሰበት ጠቁመው፤ እነዚህ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቀቆጠቡ አሳስበዋል።

ከመስከረም 25 በኋላ መንግስት አይኖርም በሚል የተለያዩ እንስቃሴዎች የሚያደርጉ አካላት እንዳሉ ገልጸው የህዝቡን ሰላም እና ደህንነት ለማስጠበቅ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁ መሆኑን አስታውቀዋል።

በዓሉ በሰላም ተከብሮ እንዲጠናቀቅ ወደ አዲስ አበባ መግቢያ በሮች በሱልልታ፣ ለገጣፎ፣ ቡራዩ፣ ገላንና ሰበታ ፍተሻ እየተደረገ እንደሆነም ኮሚሽነር እንዳሻው ጣሰው ተናግረዋል።

አላስፈላጊ እንቅስቃሴዎችን ለመግታት ፖሊስ አስፈላጊውን ዝግጅት ማድረጉን ገልጸው፤ በበዓሉ ለመታደም የሚመጡ ምዕምናንና እንግዶችም ትክክልኛውን የይለፍ ባጅ ማድርጋቸውን ማረጋገጥ እንዳለባቸው ተናግረዋል። ይህን ተላልፎ በሚገኝ ማንኛውንም አካል አይታገስም ፤ ፖሊስ እርምጃ ይወስዳልም ብለዋል።

ፖሊስ ከኅብረተሰብ ጋር በትብብር እየሰራ ነው ያሉት ሀላፊው፤ ህብረተሰቡ ለየት ያለ እንቅስቃሴ ሲመለከት የተለመደ ትብብርንና ጥቆማውን ለፖሊስ እንዲሰጥ ጥሪ ማቅረባቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column Tagged With: Ethiopia, federal police, take action

Reader Interactions

Comments

  1. ዘረ-ያዕቖብ says

    September 26, 2020 05:54 am at 5:54 am

    under no intention- z-habesha:

    ኢትዮጵያ ያለባት ሃላፊነት

    1. ለዜጎችዋ
    2. ለምድሪቱ የሰው ልጆች በሙሉ
    3. በዚሁም መሰረት ኢትዮጵያ ዜግዎችዋ የሚያስፈልጋቸውን በሙሉ ለማሳካት የተቻላትን ጥረት ታደርጋለች:: ግብፅ የአባይን ውሃ ሸጣ ገቢ ከማግኘቷ በፊት ኢትዮጵያ በኢትዮጵያ ተራራዎች ላይ ዘንቦ በኢትዮጵያ ወንዞች ውስጥ የሚፈሰውን ውሃና አፈርን ለህዝቦችዋ ጥቅም ታውላለች:: የሰው ልጆች እንደመሆናችን መጠን በሌሎች ህዝቦች ላይ ሌሎች ሃያላን ሃገራት በጎረቤቶቻቸው ላይ እንደሚያካሂዱት አይነት የማድረቅ barbaric ተግባራትን በጎረቤት ሃገራት ላይ አናካሂድም:: ስለሆነም እኛ የግብፆች ጉሮሮ እንዲደርቅ ፍላጎታችን ሊሆን አይችልም:: ከዚህን በላይ እነ የግብፅ አሽቀርቃሪዎች የሚመኙትን ስግብግብነት የሟሟላት ግን አንዳችም ግዴታም ሆነ ሃላፊነት የለብንም:: ኢትዮጵያ በዚህ መልኩ አለም አቀፋዊ ሃላፊነቷን ስለምትወጣ ግድቦቻችንንና ውሃ አፈሮቻችንን አስመልክቶ አማላጅ ምንቲሴም አስፈላጊነት የለውም:: ግን ምናልባት የGlobal አዲስ ሁናቴ ተፈጥሮ አሜሪካና ሜክሲኮ ከአሜሪካ ወደ ሜክሲኮ በሚወርዱት ወንዞችን አስመልክቶ በአማላጅ ጣልቃ ገብነት ከተደራደሩ፣ እኛም የአዲሱ የድርድር ህጎች ተገዢዎች ልንሆን ነው ማለት ነው፣ እስከዚያን ጊዜ ድረስ ነጋ ጠባ መደነቛቆሩ ቢቆም ይመረጣል::
    4. ለኢትዮጵያውያን በሙሉ፣ unity in diversity፣ ዋናው የመከላከያ ሃይል አንድነት ነውና!

    Reply
  2. ዘረ-ያዕቖብ says

    September 26, 2020 05:30 pm at 5:30 pm

    the manipulation form of z-habesha
    sagt:
    26. September 2020 um 5:50 Uhr

    ሃላፊነት ያለባት ሃላፊነት
    1. ለዜጎችዋ
    2. ለምድሪቱ የሰው ልጆች በሙሉ
    3. በዚሁም መሰረት ኢትዮጵያ ዜግዎችዋ የሚያስፈልጋቸውን በሙሉ ለማሳካት ታደርጋለች :: :: ልጆች እንደመሆናችን መጠን በሌሎች ህዝቦች ላይ ሌሎች ሃያላን ሃገራት በጎረቤቶቻቸው ላይ እንደሚያካሂዱት bar barbarisch ተግባራትን በጎረቤት ሃገራት አናካሂድም :: ስለሆነም እኛ የግብፆች ጉሮሮ እንዲደርቅ አይችልም አይችልም :: ከዚህን በላይ እነ የግብፅ አሽቀርቃሪዎች የሚመኙትን ስግብግብነት የሟሟላት ግን አንዳችም ግዴታም የለብንም የለብንም :: የለብንም የለብንም የ አለም አቀፋዊ ሃላፊነቷን ስለምትወጣ ግድቦቻችንንና ውሃ አፈሮቻችንን አስመልክቶ አማላጅ የለውም የለውም :: ግን የ የ Global አዲስ ሁናቴ ተፈጥሮ አሜሪካና ሜክሲኮ ከአሜሪካ የ በሚወርዱት በሚወርዱት አስመልክቶ በአማላጅ ጣልቃ ገብነት ፣ እኛም እኛም የድርድር ህጎች ተገዢዎች ልንሆን ነው መደነቛቆሩ መደነቛቆሩ ፣ ፣ እስከዚያን ቢቆም ይመረጣል ::
    4. ለኢትዮጵያውያን በሙሉ ፣ Einheit in Vielfalt ፣ ዋናው የመከላከያ ሃይል ሃይል ነውና!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule