• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኦህዴድ ሳያገግም፤ ብአዴን ሊደገም?

March 7, 2016 07:03 am by Editor 3 Comments

ኢትዮጵያን በተገንጣይ ስም የሚመራው የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግምባር – ህወሃት፣ የገጠመው ቀውስ እየተለጠጠበት ነው። ኦህዴድ አደረጃጀቱ ሊጠገን በማይችልበት ሁኔታ ተናግቶበታል። ይኽው ወረርሽኝ ወደ ሌሎች ገባር ድርጅቶች መስፋፋቱ የማይቀር ቢሆንም ብአዴን ውስጥ ቀውስ ስለመነሳቱ መረጃዎች ከቀድሞው በላይ ጎልተው እየወጡ ነው።

በ1997 ምርጫ ኢህአዴግን ከውድቀት ጉድጓድ ያወጣው ኦህዴድ፣ ህወሃት በአንጃ ተቧድኖ ሲባላ የመለስን ወገኖች የታደገው ብአዴን አሁን ለህወሃት መከራ ሆነውበታል። አጋር የሚባሉት ድርጅቶችም ውስጥ ተመሳሳይ ችግሮች እንዳሉ የራሱ የህወሃት መገናኛዎች እየመሰከሩ ነው።

የችግሩ አሳሳቢነት ቀላል ባለመሆኑ ኦሮሚያና ጋምቤላ ተሸንሽነው “በጊዚያዊ ወታደራዊ አስተዳደር” ሥር ወድቀዋል። ይህንኑ እውነት አሁንም የራሱ የህወሃት ልሳኖች አምነው ይፋ አድርገውታል። አንድ ወጥ አገር በነጻ አውጪ ቡድን፣ በፌዴራል መዋቅር፣ በጊዜያዊ ወታደራዊ አስተዳደር፣ በሱዳን ሚሊሺያ፣ ወዘተ የተዘበራረቀ አመራር ላይ መውደቋ የወደፊቱን የመለስ “ራዕይ” አመላካች ስለመሆኑ አስተያየት እየተሰጠ ነው።

ነገሮች እንደዚህ በጦዙበት ወቅት “የታላቋ ትግራይ” ድንበር ሙሉ የሁመራን ለም ምድር የሚያጠቃልል፣ ጠገዴንና ወልቃይትን የሚውጥ፣ እንዲሁም ኤርትራ ግዛት ጠልቆ የሚገባ መሆኑ ቦታና ስም ተዘርዝሮ ይፋ መሆን ጀምሯል። በሌላ ጎኑ ኦህዴድ ውስጥ “ህዝብ ለምን አመጸ፣ የጸጥታ ሃይሉ እንዴት ከጃችን ወጣ? የታች መዋቅሩ እንዴት ፈረሰ? ድርጅታዊ ሠንሰለቱ እንዴት ተበጠሰ? ታማኝነትና ጠባብነት …” ማለቂያ የሌለው ግምገማ  እየተካሄደ ነው። ከዚሁ ጋር በተያያዘ  የኢህአዴግ ሥራ አስፈጻሚና የኦህዴድ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዳባ ደበሌ፣ የኦሕዴድ ሥራ አስፈጻሚና የኦሮሚያ ክልል አስተዳደርና ፀጥታ ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ ሰለሞን ኩቹ ለጊዜው ከተመደቡበት ያገለጋይነት ሹመት ተነስትው ቀለበት ውስጥ እንዳሉ ተሰምቷል። ሹም ሸሩ ቀጣይ እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል።

በህወሃት አደረጃጀት “ጸጥታ” የሚለው ሹመት የስለላው ምሶሶ ዘርፍ ነው። የኦህዴድ የፀጥታ ሃላፊ ተነሱ ማለት ስለላው ተናግቷል ወይም እንደ ቀድሞ መረጃ አያገኝም ማለት ነው። ይህ የሚሆነው ደግሞ አንድ ለአምስት የሚባለው የስለላ መዋቅር ውሃ በለቶታል ማለት ነው። አሁን እንደ አዲስ ቢደራጅ የሚተገበረው ቀድሞ ታች ባሉት አመራሮችና ካድሬዎች ላይ በመሆኑ ተግባራዊ ሊሆን አይችልም በማለት ስለ አደረጃጀቱና ስለ ወቅቱ ግለት የሚያውቁ እየገለጹ ነው።

በየቀበሌው ድምጻቸውን ያሰሙ ወገኖች ተገልለዋል፤ በሺህ የሚቆጠሩ ታስረዋል። የተሰደዱ፣ ቀያቸውን ጥለው የኮበለሉ፣ ዱር ያሉ፣ ከዚህም በላይ ሃዘን ያደቀቃቸውና የሚጠዘጥዛቸው ቤተሰቦች፣ ዘመዶች፣ የወንዝ ልጆች፣ ኦሮሞዎች፣ ኢትዮጵያውያን አዝነዋል። የቂም ቋጠሯቸው ጠብቋል። የፈሰሰው ደም ከሚያንዘፈዝፋቸው  ክፍሎች መካከል የታችኛው ካድሬና አመራር በግንባር ቀደምትነት የሚሰለፍ ነው። በዚህ መነሻ ህወሃት እነዚሁ ዜጎች ላይ ታዛዥ ሃላፊ ቀይሮ እንደ ቀድሞው ልፈንጭ፣ ለጋልብ፣ ልፍለጥ፣ ልቁረጥ ቢል አይሳካለትም ሲሉ እነዚሁ ክፍሎች ያብራራሉ።

ምሳሌ ሲያነሱ አርሲ የሆነውን ይጠቀሳሉ። የኦሮምያ ፈጥኖ ደራሽ አባል ወገኖቹን ሊገድል የመጣውን የአጋዚ ቅጥረኞችን መሳሪያ አዙሮ ረሸነ። አስራ አንዱን ሲገድል አንዱን አንገቱ ላይ ቆሞ ነው እያቀራራ ጥይት ያዘነበበት። ተቺዎች እንደሚሉት የዚህ ፖሊስ ተግባር መጪውን የሚያመላክት ነው። ህወሃት ብቻ ሳይሆን ሌሎችም በብሄራቸው ላይ የሚፈጸም ግፍ ያማቸዋል። በዝርፊያ የበሰበሱትን ሳይጨምር።

የበታቹ ካድሬ የዝርፊያ ጉዳይ አያሳስበውም። አብዛኛው ደግሞ ይህ የህብረተሰብ ከፍል ነው። ባንድ ግምገማ ላይ አንድ የህወሃት ሰው ስለ ሙስና አንስተው ሲገመግሙ አንድ ከንቲባ ተነስተው “እርስዎ ቤተሰቦችዎን እየላኩ መሬት ይወስዱ አልነበረም” ሲል ሞግተዋቸው እንደነበር የሚያስታውሱ “አሁን የበላዩ የበታቹን ሲገመግም አዳራሹ በሽሙጥ ይሞላል፤ ሌላውን ለመወንጀል ንጹህ ጀርባ ያላቸው ስለሌሉ የሚታየው ሁሉ ከበሰበሰ እንቁላል ጫጩት የመከጀል ያህል ነው” በሚል ህወሃት ብስባሽ ላይ ሆኖ እንደሚወራጭ ያስረዳሉ።

በኦሮሚያ መዋቅር ፈርሶ ሽማግሌዎች መሬት ለተወሰደባቸው ሲያከፋፈሉ ነበር። አጋርፋ አካባቢ ይህ ተፈጽሟል። ይህንን ህዝብ መልሶ ማደራጀት ጅልነት እንደሆነ የሚጠቁሙ ክፍሎች ህወሃት በቅጡ አስቦና መክሮ ወደ ትክክለኛው መፍትሄ ሊመጣ እንደሚገባው ይመክራሉ። አያይዘውም በሌሎች የህብረተሰብ ከፍሎች ላይ የሚፈጸመው ግፍ አድሮም ቢሆን ዋጋ ስለሚያስከፍል በስማቸው የሚፈጸመው ወንጀል ይቆም ዘንድ የትግራይ ንጹሃን ድምጻቸውን ሊያሰሙ እንደሚገባ ጠቁመዋል።

አማራ ክልልም ቢሆን የተሳከረ ችግር ስለ መኖሩ ህወሃት የማይክድበት ደረጃ ላይ ነው። ባለፈው ሳምንት የትግራይ ክልል ፐሬዚዳንት የአማራ ክልል አስተዳዳሪን ውይይት ላይ “አማራን ትጥቅ አስፈታ” የሚል ትዕዛዝ አዘል ንግግር ሲናግሩ “የምን ትጥቅ ነው የማስፈታው? አንተ ግምጃ ቤት ከፍትህ ለትግራይ ህዝብ መሳሪያ እያደልክ” የሚል መልስ እንደሰጡ በተለይ ለጎልጉል መረጃ የላኩ አስረድተዋል።

የወልቃይትን ጉዳይ ከህወሃት ፍላጎት አንጻር የብአዴን ስራ አስፈጻሚ እንዲቀበልን አቋም እንዲይዝ ትዕዛዝ ቢሰጥም “በቀጥታ ከህዝብ ጋር የምንገናኘው እኛ ነን፤ ይህንን አንቀበልም፤ ልታስፈጁን ነው?” የሚል ምላሽ ከበታች ካድሬዎች ተሰንዝሯል። እንደ ዜናው አቀባዮች ከሆነ ብአዴን ውስጥ ኦህዴድ ላይ የደረሰው የበታች አመራር መንሸራተት እየታየ ነው።

የብአዴን ማዕከላዊ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርጓል፡፡ በመልካም አስተዳደር ችግሮች ላይ፣ ከቅማንት ማኅበረሰብ ማንነት ጋር በተያያዘ የተከሰተውን ችግርና የግጭት አፈታት ተግባራትን፣ በአማራና በትግራይ ክልሎች በፀገዴ ወረዳዎች የተከሰተውን ችግርና በሁለቱ ክልሎች የተደረገውን ምክክር፣ በክልሉ በድርቅ የተጠቁ 2.3 ሚሊዮን ዜጎችን በተመለከተና በሌሎች ጉዳዮች ላይ ለሦስት ቀናት መክሯል ሲል ሪፖርተር ዛሬ ዘግቧዋል።

ሰሞኑን በሁለት የኦህዴድ ከፍተኛ አመራሮች ላይ በተወሰደው እርምጃ የተጀመረው ኦህዴድን የማጽዳት ተግባር በርካታ የአመራሮች ላይ ሰይፉን እንደሚያሳርፍ ከወዲሁ የሚያመላክቱ በርካታ መረጃዎች አሉ፡፡ ከሁለት ወር ተኩል በፊት ጎልጉል የኦህዴድ ህወሃት/ኢህአዴግን መክዳት አስመልክቶ በጻፈው የዜና ዘገባ ላይ እስካሁን የተሠራው ጥርነፋም ሆነ የህወሃት የበላይነት የተፈለገውን ውጤት ሳያመጣ ቀርቶ ኦሮሚያን ለከፋ ችግር እንደዳረጋት ተጠቅሶ ነበር፡፡

ይህ የኦህዴድ ችግር ገና መስመር ሳይዝ አሁን ደግሞ ህወሃት ወደ ብአዴን ላይ ለመዞር ማሰቡና “ትጥቅ” ለማስፈታት የሚያደርገው እንቅስቃሴ ጉዞውን ከድጡ ወደ ማጡ ያደርገዋል የሚለው አስተያየት የበረከተ ነው፡፡ ከሁሉ በላይ ኦህዴድና ብአዴን አብረው ህወሃትን ብቻውን ቢያስቀሩት የፖለቲካውን አሰላለፍም ሆነ የአገሪቱን የወደፊት አቅጣጫ ባልታሰበ መልኩ ይቀይረዋል ተብሎ ይታመናል፡፡ (ፎቶ: addisfortune)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Aman says

    March 7, 2016 12:03 pm at 12:03 pm

    የናንተው የብዕር ጥቃት በ25 ዓመታት ውስጥ ምንም ሊሰራ ኣልቻለም። እናንተ እንደምትፎኩሩት ከሆነ ወያነ ከኣስርቱ ዓመታት በፊት ሞቶዋል።

    Reply
  2. gud says

    March 7, 2016 04:01 pm at 4:01 pm

    Speculation and wishful thinking

    Reply
  3. geresu says

    March 10, 2016 10:35 am at 10:35 am

    ወያኔ ብአዲኖችንና ኦህዲድዶችን ንፍጣቸዉን እያናፈጣቸዉ ነዉ::

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule