• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ኢያዬ ደበርሳ” – ጩኸቴን አስተላልፍ፤ የሚመራው ህዝባዊ ዓመጽ

December 20, 2015 12:37 pm by Editor Leave a Comment

አሁን በተለይ በኦሮሚያ የተቀጣጠለው ዓመጽ ከጀርባው አቀጣጣይ ኃይላት እንዳሉበት ህወሃት እየሰበከ ነው። “ጥቂት ጸረ ሰላም ሃይሎች” በማለት ብዙ አካላትን እየከሰሰም ነው። የትኛውን ኦነግ ወይም ኦነጎችን እንደሆነ ባይታወቅም እንዲያው በደፈናው “ኦነግ”ን ይከስሳል። አርበኞች ግንቦት ፯ እና አገር ቤት ያሉ ሰላማዊ ተቀናቃኞችም የአመጹ አቀጣጣይ ተደርገው ተፈርጀዋል። በተገንጣይ ስም አገር የሚገዛው የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር ፍረጃውን ለሚያካሂደው ጭፍጨፋ ህጋዊ ሽፋን ሊያውለው ሆን ብሎ የሚያደርገው እንደሆነ ቢታመንም “እመኑኝ” ሲሉ ኦቦ ቃሉ Oboo Qaalluu የሚሉት ሌላ ነው።

ኦቦ ቃሉ ከ25 ዓመት በላይ ኦነግን ያገለገሉና አሁን በስደት አውስትራሊያ የሚኖሩ ናቸው። በቅርቡ ውህደቱን  ይፋ ያደርጋል ተብሎ የሚገመተው የኦሮሞ ነጻነት ግንባር [ዩናይትድ] አካል ሆነው እየሰሩ ነው። እርሳቸው እንደሚሉት ኦነግ ብዙ ነው። ብዙ አመራር አለው። ብዙ ቅርንጫፍ አለው። “ዩናይትድ” የሚል ቅጽል ስም ያለው ኦነግ ማን ነው?

በአቶ ቦንሳ ተባ የሚመራው የኦሮሞ ነጻነት ግንባር [ሸሌ]፣ በአቶ ድሪባ ሆርዶፋ የሚመራው ጊዜያዊ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ህብረት፣ በአቶ አብደታ ኢሸኬ የሚመራው የኦሮሞ ነጻነት ታጋዮች ጥምር፣ ከእነ ጀነራል ከማል ገልቹ የተገነጠለውና በአቶ ኑሮ ደደፎ የሚመራው የኦሮሞ ነጻነት ግንባር [ቼንጅ] የሚባሉት የተለያዩ የኦነግ አካሎች የፈጠሩት ህብረት ነው። ኦነግ ከሚለው መጠሪያው ጎን [ዩናይትድ] በሚል ተቀጽላ ራሱን የሚለየው ኦነግ ኦቦ ነጋ ጃራን ሊቀመንበር፣ ጄኔራል ኃይሉ ጎንፋን ምክትል ሊቀ መንበር አድርጎ ሰይሟል። ኦቦ ቃሉ እንደሚሉት ውህደቱ በቅርቡ ይፋ ይሆናል።

ሰሞኑን “ኦነግ” በሚለው ስያሜ ከየአቅጣጫው የሚወጣው መግለጫ እንደሚያሰረዳው ኦነግ ውስጥ ያለው መከፋፈል ፈርጁ ብዙ ነው። ሕዝባዊ አልኝታነት ግን ከመግለጫና ከቃላት በላይ ሊሆን ይገባል። ኦቦ ቃሉ እንደሚሉት “መግለጫ ማንም ማውጣት ይችላል። ፍርድን ለህዝብ በመተው እስከድል ድረስ እንኳን አንድ ለመሆን አለመቻል ያሳዝናል። ልዩነትን ወደ ጎን በመተው ከመስማማት ውጪ የሚደረገው የመግለጫ ጎርፍ የማስታወቂያ ስራም ይመስላል” በማለት ጊዜው የህብረት ሊሆን እንደሚገባ ያሳስባሉ። በርግጥም ሰሞኑንን ደብዛቸው የጠፋ በርካቶች ከመግለጫቸው ጋር ለትውስታ በቅተዋል። የጠፉት ብቅ የማለታቸው ጉዳይ በቻ ሳይሆን “ታጣቂ ሃይል አለን” የሚሉትስ?

ጦር ያላቸው ክፍሎች ካሉ ከዚህ የተሻለ አጋጣሚ ስለማያገኙ ህዝብን መቀላቀል ይገባቸው እንደነበር ያመለከቱት ኦቦ ቃሉ “ይህ የተቆጣ ህዝብ፣ ምሬት የፈነቀለው ህዝብ፣ በቃኝ ያለ ህዝብ፣ ትግሉን ከዱላ በዘለለ የሚያግዘው ቢያገኝ ውጤቱ ሊፈጥን በቻለ ነበር” ባይ ናቸው። አያይዘውም “ለመሆኑ መዋጮ ሲሰበሰብለት የኖረው ጦር የት አለ?” ሲሉ ይጠይቃሉ። ብሶትና ጭቆና ባዶ እጁን ደረቱን ለጥይት ሰጥቶ አደባባይ የወጣው ህዝብ በግዳጅ፣ በፈቃደኛነት ለገንዘብ ብሎ ለህወሃት ሰዎች መሳሪያውን በመሸጥ ባዶ እጁን የቀረ ሕዝብ፤ ከወረቀት መግለጫ የዘለለ ድጋፍ እንደሚያሻው ያመላክታሉ። ኢትዮጵያን ነጻ ሊያወጡ የተነሱ ኃይሎች  መቼ ነው አንድ ወረዳ የሚቆጣጠሩት? ጥያቄው የነበረ፣ ያለና የሚኖር ነው።

የህዝባዊ አመጹ ባለቤት ማን ነው?

የኦሮሚያ ሕዝብ እንደ ሌሎች ወገኖቹ ፩ – ፭ በሚባለው አደረጃጀት እስር ቤት ሳይገባ የታሰረ ሕዝብ ነው። መዋቀሩን የሚተገብረው ደግሞ ኦህዴድ ነው። ይህ ህዝብ ሳይፈታ ሊያምጽ አይችልም። የታሰሩትን የሚፈታቸው አሳሪያቸው ብቻ ነው። ስለዚህ የራሱን ሕዝብ ጠርንፎ የነበረው ሃይል ህዝቡን ለቀቀ። ህዝብ ሲፈታ መዋቅር ፈረሰ። ኦቦ ቃሉ ይህን ማብራሪያ ካነሱ በኋላ “አብረው  መስራት ያልተስማሙ ሃይሎች የተቀናጀ አመጽን ጸንሰው፣ አዋልደውና አሳድገው ሊመሩ ይቻላቸዋል?” በማለት ይጠይቃሉ። በዚህ መነሻ አመጹ የህዝብ የመንገፍገፍ ብዛት የወለደው እንደሆነ ይናገራሉ። ብሶት ትግራይ ብቻ ሳይሆን የተበደሉ ባሉበት ቦታ ሁሉ ቀን እየጠበቀ እንደሚነሳ ይጠቁማሉ።

አሁን ኦሮሚያ ላይ የተቀጣጠለውና ህወሃትን የናጠው የህዝብ አመጽ አስመልክቶ አቶ ጃዋር መሃመድ “የኦሮሞ ህዝብ እንደዚህ ሲያመር በታሪክ አይቼ አላውቅም። ከንግዲህ የሚቀረው ህይወቱ ብቻ ነው” በማለት እንደገለጹት ኦቦ ቃሉም “በህወሃትና በኦሮሞ ሕዝብ መካከል የነበረችው የሰለለች ክር ተበጥሳለች። መልሰው እንዳይቀጥሏት ቀድሞውንም የሰለለች ነበረች። ሂደት ነው የበጠሳት። አልቆላታል።” አቶ ጃዋር ለኢሳት እንዳሉት “ደም በፈሰሰ ቁጥር ደም ይግላል። የጋለ ደም አደገኛ ነው … ካሁን በኋላ በቀድሞው መልኩ አይቅጥልም። ሁላችንም ለመሞት ዝግጁ ነን”

የፈነዳው ኦህዴድ

አንዴ በቆረኪ፣ አንዴ በካርታ፣ አንዴ በኪራይ ሰብሳቢነት፣ ወዘተ እየተነረተ፤ በግምገማ ቁም ስቅሉን እያየ ለህወሃት ልእልና የኖረው ኦህዴድ “ፈንድቷል” የሚለው አገላለጽ ተስማሚው ሆኖ ተገኝቷል። ህወሃት ኦህዴድን “ከዳኝ” ይለዋል። ለዚህም ይመስላል የፈነዳው ኦህዴድ ኦሮምያ ላይ የነበረው ውሱን አቅም ተወስዶበታል። ቀድሞውንም ቢሆን ባለሙሉ ሥልጣን ስላልነበር የህወሃት ውሳኔ ገኖ አልወጣም እንጂ ኦሮሚያ ላይ ህወሃት ኩዴታ አካሂዷል። ኦህዴድን ከጨዋታው ውጪ አድርጎታል። ሊጠግኑት ቢሉ እንኳን የሚከብድ ነው።

በቀጣይ ተሃድሶ አካሂዶ ኦህዴድ ላይ ነፍስ መዝራትና እስከ ወረዳና ቀበሌ የተዘረጋውን መዋቀር በቀላሉ አድሶ ማስቀጠል የሚቻል አይሆንም። ኦቦ ቃሉ እንደሚሉት አሁን የተጀመረው የሕዝብ እምቢተኛነት ቢቀዘቅዝ እንኳን ኦህዴድ እንደ ቀድሞው የህወሃት ታማኝ ሆኖ እንዲቀጥል ወደሚያስችለው ደረጃ አይመለስም። ታምቆ የፈነዳና ፍንዳታው ከልሉን ያናወጠ በመሆኑ መዋቀሩ ሙሉ በሙሉ ወደ ህዝባዊ ትስስር ተቀይሯል። ህወሃት እድርና እቁብ የመሳሰሉት ማህበራዊ የመጠርነፊያ መገልገያዎቹን ከስሯል። በበርካታ መመዘኛዎች ኦህዴድ ዲቃላ ሆኖ የመቆም እድሉ ከህወሃት ፍላጎት አንጻር የጠወለገ ነው። እናም ቅድመ ዝግጅት ያስፈልጋል።

ሳይቃጠል በቅጠል

“ይህ ስርዓት አደገኛ ነው። ሲወድቅ ህዝብና አገር ይዞ ይሄዳል። ግንኙነት ያስፈለጋል” በማለት ሰዎች ያሉበት ሁኔታና አቋማቸው ሳይታወቅ አቋም መያዝ እንደማይገባ አቶ ጃዋር ያሳስባሉ። እንደ እሳቸው ገልጻ ሁሉ አሁን አገሪቱ ያለችበት ሁኔታ ያሳሰባቸው ከፍሎች ያገባናል የሚሉ ወገኖች ሁሉ የፖለቲካ መሪ የመፍጠር ስራና፣ አገሪቱ ላይ ህዝብ ያስነሳውን ተቃውሞ አቅጣጫ የማስያዝ ሥራ ሊሰራ እንደሚገባ ያስገነዝባሉ።

ኦሮሚያን አስመልክተው የሚሰሩ ሚዲያዎች ከግለሰብ ማንነትና ድጋፍ ያልተላቀቁ፣ ሚዛናቸው ግለሰብን መደገፍና ማስተዋወቅ እንደሆነ የተናገሩት ኦቦ ቃሉ “ነጻና ከግለሰብ ዝና አቀንቃኝነት የተላቀቀ ሚዲያ ቢኖር ህዝብ ስለ ፖለቲካ መሪዎቹ ጥሩ ስዕል ይኖረው ነበር” ብለዋል። ማናቸውም ሚዲያዎች ሰዎችን የመታደግና የመካብ ስራ ላይ ካተኮሩ ዋና ሚናቸውን ዘንግተዋልና ሊመለሱ ይገባል። አቶ መለስ ሞተውም በሺህ የሚቆጠር ሄክታር መሬት የሚመሩት ሚዲያው እንዲገነባላቸው በተደረገው የሌለ ስብዕናቸው ሳቢያም እንደሆን መረዳት ግድ እንደሚል ተናግረዋል።

“ስለዚህ” ይላሉ አሉ ኦቦ ቃሉ “ስለዚህ ህዝብ በቃኝ ብሎ በቀሰቀሰው ማእበል ውስጥ ገብቶ የማዕበሉ ፈጣሪ ለመሆንና የማስታወቂያ ይዘት ያላቸውን መግለጫዎች ከማተም በመቀራረብ አንድ ላይ መስራት ወደሚቻለበት መንገድ ባስቸኳይ ማምራቱ አንገብጋቢ ነው” ይላሉ፡፡

“አገሪቱ እየተቸበቸበች ነው። በዚህ መልኩ ፭ ዓመት ከቀጠልን ዋጋ የለንም” በማለት አቶ ጃዋር ለሰጡት አስተያየት ኦቦ ቃሉ “የኦሮሞ መሬት ፭ ዓመት የሚቆየ ዕድሜ የለውም” የሚል ማጠናከሪያ አስተያየት ሰጥተዋል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ፍፁም ብርሃኔና ታምራት የማነ በቁጥጥር ሥር ዋሉ April 16, 2021 10:06 am
  • “ለአንድ ፓርቲ የማደላ ከሆነ ሄጄ እዚያው ፓርቲ እገባለሁ” ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ April 16, 2021 08:45 am
  • “ተዋግተን አይደለም ስንተኛ ብንውል እንኳን መቀሌና አዲስ አበባ አይገቡም” ጄኔራል ባጫ April 14, 2021 09:06 am
  • የስኳር ፋብሪካዎች ተሽጠው ዕዳቸውን እንዲከፍሉ ተወሰነ April 14, 2021 08:53 am
  • “ኤርትራዊ ነን” በማለት የመኖሪያ ፈቃድ ሲቀበሉ የኖሩ የትግራይ ሰዎችን መለየት ተጀመረ April 1, 2021 02:01 am
  • ምርጫ ቦርድ የኦነግን ጥያቄ ውድቅ አደረገ April 1, 2021 01:15 am
  • “እርግጠኛ ሆኜ የምነግራችሁ መንግሥት ኮሮጆ አይሰርቅም” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ April 1, 2021 01:09 am
  • መንግሥት ካልደረሰልን አሁንም ግድያ ይኖራል – ነዋሪዎች April 1, 2021 01:04 am
  • በትግራይ ሊዘረፍ የነበረ የእርዳታ እህል ተያዘ April 1, 2021 12:39 am
  • “በኢትዮጵያ ክብርና ጥቅም ከመጣችሁ አንገቴ ይቀላል እንጂ አልደራደርም” March 24, 2021 01:22 am
  • “ከዚህ በኋላ ህወሓት ማለት በነፋስ የተበተነ ዱቄት ነው” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ March 23, 2021 11:28 pm
  • እነ ስብሃት ነጋ ጥያቄያቸው ውድቅ ሆነ March 23, 2021 10:23 pm
  • በርግጥ ኢትዮጵያ ዝናብ አዝንባለች? March 23, 2021 10:15 pm
  • አሜሪካ በሴናተሯ አማካይነት “ለቅሶ” ደረሰች March 21, 2021 08:57 pm
  • ቪኦኤ በወለጋ ሆሮ ጉድሩ ለተጨፈጨፉ ኦነግ ሸኔን ከደሙ ንጹህ አደረገ March 19, 2021 04:32 pm
  • ባልደራስና የአብን የትብብር ስምምነት ተፈራረሙ March 18, 2021 01:56 pm
  • ኤርሚያስ ለገሰ “የወያኔ የፕሮፖጋንዳ ሰራተኛ እያለ የለመደው የቁጥር ጫወታ አለቀቀውም” March 17, 2021 09:54 pm
  • በትግራይ ሰብዓዊ ድጋፍ በተቀላጠፈ ሁኔታ እየተካሄደ ነው – የተመድ የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት March 17, 2021 04:54 am
  • ምርጫ ቦርድ ከፈቀደለት ኦነግ በምርጫው እንደሚወዳደር አስታወቀ March 17, 2021 04:30 am
  • በዓለምአቀፍ ሚዲያ ዘጋቢዎች ላይ እርምጃ ሊወሰድ ነው March 15, 2021 11:25 am
  • በሲዳማ/ሀዋሳ 128 ቱርክ ሰራሽ ሽጉጥ፤ 2 መትረየስ ከ8,129 ጥይት ጋር ተያዘ March 15, 2021 10:13 am
  • የአክሱም ጅምላ ጭፍጨፋ ተብሎ የተሰራጨው ፎቶ የሐሰት ሆነ March 15, 2021 09:26 am
  • በትግራይ ትምህርት ቤቶች በቅርቡ ሥራ ይጀምራሉ March 15, 2021 09:04 am
  • በማይካድራ የጅምላ መቃብር ተገኘ፤ በህወሓት የተገደሉት ቁጥር ከ1300 እንደሚበልጥ ተነገረ March 15, 2021 08:54 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule