• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ኢያዬ ደበርሳ” – ጩኸቴን አስተላልፍ፤ የሚመራው ህዝባዊ ዓመጽ

December 20, 2015 12:37 pm by Editor Leave a Comment

አሁን በተለይ በኦሮሚያ የተቀጣጠለው ዓመጽ ከጀርባው አቀጣጣይ ኃይላት እንዳሉበት ህወሃት እየሰበከ ነው። “ጥቂት ጸረ ሰላም ሃይሎች” በማለት ብዙ አካላትን እየከሰሰም ነው። የትኛውን ኦነግ ወይም ኦነጎችን እንደሆነ ባይታወቅም እንዲያው በደፈናው “ኦነግ”ን ይከስሳል። አርበኞች ግንቦት ፯ እና አገር ቤት ያሉ ሰላማዊ ተቀናቃኞችም የአመጹ አቀጣጣይ ተደርገው ተፈርጀዋል። በተገንጣይ ስም አገር የሚገዛው የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር ፍረጃውን ለሚያካሂደው ጭፍጨፋ ህጋዊ ሽፋን ሊያውለው ሆን ብሎ የሚያደርገው እንደሆነ ቢታመንም “እመኑኝ” ሲሉ ኦቦ ቃሉ Oboo Qaalluu የሚሉት ሌላ ነው።

ኦቦ ቃሉ ከ25 ዓመት በላይ ኦነግን ያገለገሉና አሁን በስደት አውስትራሊያ የሚኖሩ ናቸው። በቅርቡ ውህደቱን  ይፋ ያደርጋል ተብሎ የሚገመተው የኦሮሞ ነጻነት ግንባር [ዩናይትድ] አካል ሆነው እየሰሩ ነው። እርሳቸው እንደሚሉት ኦነግ ብዙ ነው። ብዙ አመራር አለው። ብዙ ቅርንጫፍ አለው። “ዩናይትድ” የሚል ቅጽል ስም ያለው ኦነግ ማን ነው?

በአቶ ቦንሳ ተባ የሚመራው የኦሮሞ ነጻነት ግንባር [ሸሌ]፣ በአቶ ድሪባ ሆርዶፋ የሚመራው ጊዜያዊ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ህብረት፣ በአቶ አብደታ ኢሸኬ የሚመራው የኦሮሞ ነጻነት ታጋዮች ጥምር፣ ከእነ ጀነራል ከማል ገልቹ የተገነጠለውና በአቶ ኑሮ ደደፎ የሚመራው የኦሮሞ ነጻነት ግንባር [ቼንጅ] የሚባሉት የተለያዩ የኦነግ አካሎች የፈጠሩት ህብረት ነው። ኦነግ ከሚለው መጠሪያው ጎን [ዩናይትድ] በሚል ተቀጽላ ራሱን የሚለየው ኦነግ ኦቦ ነጋ ጃራን ሊቀመንበር፣ ጄኔራል ኃይሉ ጎንፋን ምክትል ሊቀ መንበር አድርጎ ሰይሟል። ኦቦ ቃሉ እንደሚሉት ውህደቱ በቅርቡ ይፋ ይሆናል።

ሰሞኑን “ኦነግ” በሚለው ስያሜ ከየአቅጣጫው የሚወጣው መግለጫ እንደሚያሰረዳው ኦነግ ውስጥ ያለው መከፋፈል ፈርጁ ብዙ ነው። ሕዝባዊ አልኝታነት ግን ከመግለጫና ከቃላት በላይ ሊሆን ይገባል። ኦቦ ቃሉ እንደሚሉት “መግለጫ ማንም ማውጣት ይችላል። ፍርድን ለህዝብ በመተው እስከድል ድረስ እንኳን አንድ ለመሆን አለመቻል ያሳዝናል። ልዩነትን ወደ ጎን በመተው ከመስማማት ውጪ የሚደረገው የመግለጫ ጎርፍ የማስታወቂያ ስራም ይመስላል” በማለት ጊዜው የህብረት ሊሆን እንደሚገባ ያሳስባሉ። በርግጥም ሰሞኑንን ደብዛቸው የጠፋ በርካቶች ከመግለጫቸው ጋር ለትውስታ በቅተዋል። የጠፉት ብቅ የማለታቸው ጉዳይ በቻ ሳይሆን “ታጣቂ ሃይል አለን” የሚሉትስ?

ጦር ያላቸው ክፍሎች ካሉ ከዚህ የተሻለ አጋጣሚ ስለማያገኙ ህዝብን መቀላቀል ይገባቸው እንደነበር ያመለከቱት ኦቦ ቃሉ “ይህ የተቆጣ ህዝብ፣ ምሬት የፈነቀለው ህዝብ፣ በቃኝ ያለ ህዝብ፣ ትግሉን ከዱላ በዘለለ የሚያግዘው ቢያገኝ ውጤቱ ሊፈጥን በቻለ ነበር” ባይ ናቸው። አያይዘውም “ለመሆኑ መዋጮ ሲሰበሰብለት የኖረው ጦር የት አለ?” ሲሉ ይጠይቃሉ። ብሶትና ጭቆና ባዶ እጁን ደረቱን ለጥይት ሰጥቶ አደባባይ የወጣው ህዝብ በግዳጅ፣ በፈቃደኛነት ለገንዘብ ብሎ ለህወሃት ሰዎች መሳሪያውን በመሸጥ ባዶ እጁን የቀረ ሕዝብ፤ ከወረቀት መግለጫ የዘለለ ድጋፍ እንደሚያሻው ያመላክታሉ። ኢትዮጵያን ነጻ ሊያወጡ የተነሱ ኃይሎች  መቼ ነው አንድ ወረዳ የሚቆጣጠሩት? ጥያቄው የነበረ፣ ያለና የሚኖር ነው።

የህዝባዊ አመጹ ባለቤት ማን ነው?

የኦሮሚያ ሕዝብ እንደ ሌሎች ወገኖቹ ፩ – ፭ በሚባለው አደረጃጀት እስር ቤት ሳይገባ የታሰረ ሕዝብ ነው። መዋቀሩን የሚተገብረው ደግሞ ኦህዴድ ነው። ይህ ህዝብ ሳይፈታ ሊያምጽ አይችልም። የታሰሩትን የሚፈታቸው አሳሪያቸው ብቻ ነው። ስለዚህ የራሱን ሕዝብ ጠርንፎ የነበረው ሃይል ህዝቡን ለቀቀ። ህዝብ ሲፈታ መዋቅር ፈረሰ። ኦቦ ቃሉ ይህን ማብራሪያ ካነሱ በኋላ “አብረው  መስራት ያልተስማሙ ሃይሎች የተቀናጀ አመጽን ጸንሰው፣ አዋልደውና አሳድገው ሊመሩ ይቻላቸዋል?” በማለት ይጠይቃሉ። በዚህ መነሻ አመጹ የህዝብ የመንገፍገፍ ብዛት የወለደው እንደሆነ ይናገራሉ። ብሶት ትግራይ ብቻ ሳይሆን የተበደሉ ባሉበት ቦታ ሁሉ ቀን እየጠበቀ እንደሚነሳ ይጠቁማሉ።

አሁን ኦሮሚያ ላይ የተቀጣጠለውና ህወሃትን የናጠው የህዝብ አመጽ አስመልክቶ አቶ ጃዋር መሃመድ “የኦሮሞ ህዝብ እንደዚህ ሲያመር በታሪክ አይቼ አላውቅም። ከንግዲህ የሚቀረው ህይወቱ ብቻ ነው” በማለት እንደገለጹት ኦቦ ቃሉም “በህወሃትና በኦሮሞ ሕዝብ መካከል የነበረችው የሰለለች ክር ተበጥሳለች። መልሰው እንዳይቀጥሏት ቀድሞውንም የሰለለች ነበረች። ሂደት ነው የበጠሳት። አልቆላታል።” አቶ ጃዋር ለኢሳት እንዳሉት “ደም በፈሰሰ ቁጥር ደም ይግላል። የጋለ ደም አደገኛ ነው … ካሁን በኋላ በቀድሞው መልኩ አይቅጥልም። ሁላችንም ለመሞት ዝግጁ ነን”

የፈነዳው ኦህዴድ

አንዴ በቆረኪ፣ አንዴ በካርታ፣ አንዴ በኪራይ ሰብሳቢነት፣ ወዘተ እየተነረተ፤ በግምገማ ቁም ስቅሉን እያየ ለህወሃት ልእልና የኖረው ኦህዴድ “ፈንድቷል” የሚለው አገላለጽ ተስማሚው ሆኖ ተገኝቷል። ህወሃት ኦህዴድን “ከዳኝ” ይለዋል። ለዚህም ይመስላል የፈነዳው ኦህዴድ ኦሮምያ ላይ የነበረው ውሱን አቅም ተወስዶበታል። ቀድሞውንም ቢሆን ባለሙሉ ሥልጣን ስላልነበር የህወሃት ውሳኔ ገኖ አልወጣም እንጂ ኦሮሚያ ላይ ህወሃት ኩዴታ አካሂዷል። ኦህዴድን ከጨዋታው ውጪ አድርጎታል። ሊጠግኑት ቢሉ እንኳን የሚከብድ ነው።

በቀጣይ ተሃድሶ አካሂዶ ኦህዴድ ላይ ነፍስ መዝራትና እስከ ወረዳና ቀበሌ የተዘረጋውን መዋቀር በቀላሉ አድሶ ማስቀጠል የሚቻል አይሆንም። ኦቦ ቃሉ እንደሚሉት አሁን የተጀመረው የሕዝብ እምቢተኛነት ቢቀዘቅዝ እንኳን ኦህዴድ እንደ ቀድሞው የህወሃት ታማኝ ሆኖ እንዲቀጥል ወደሚያስችለው ደረጃ አይመለስም። ታምቆ የፈነዳና ፍንዳታው ከልሉን ያናወጠ በመሆኑ መዋቀሩ ሙሉ በሙሉ ወደ ህዝባዊ ትስስር ተቀይሯል። ህወሃት እድርና እቁብ የመሳሰሉት ማህበራዊ የመጠርነፊያ መገልገያዎቹን ከስሯል። በበርካታ መመዘኛዎች ኦህዴድ ዲቃላ ሆኖ የመቆም እድሉ ከህወሃት ፍላጎት አንጻር የጠወለገ ነው። እናም ቅድመ ዝግጅት ያስፈልጋል።

ሳይቃጠል በቅጠል

“ይህ ስርዓት አደገኛ ነው። ሲወድቅ ህዝብና አገር ይዞ ይሄዳል። ግንኙነት ያስፈለጋል” በማለት ሰዎች ያሉበት ሁኔታና አቋማቸው ሳይታወቅ አቋም መያዝ እንደማይገባ አቶ ጃዋር ያሳስባሉ። እንደ እሳቸው ገልጻ ሁሉ አሁን አገሪቱ ያለችበት ሁኔታ ያሳሰባቸው ከፍሎች ያገባናል የሚሉ ወገኖች ሁሉ የፖለቲካ መሪ የመፍጠር ስራና፣ አገሪቱ ላይ ህዝብ ያስነሳውን ተቃውሞ አቅጣጫ የማስያዝ ሥራ ሊሰራ እንደሚገባ ያስገነዝባሉ።

ኦሮሚያን አስመልክተው የሚሰሩ ሚዲያዎች ከግለሰብ ማንነትና ድጋፍ ያልተላቀቁ፣ ሚዛናቸው ግለሰብን መደገፍና ማስተዋወቅ እንደሆነ የተናገሩት ኦቦ ቃሉ “ነጻና ከግለሰብ ዝና አቀንቃኝነት የተላቀቀ ሚዲያ ቢኖር ህዝብ ስለ ፖለቲካ መሪዎቹ ጥሩ ስዕል ይኖረው ነበር” ብለዋል። ማናቸውም ሚዲያዎች ሰዎችን የመታደግና የመካብ ስራ ላይ ካተኮሩ ዋና ሚናቸውን ዘንግተዋልና ሊመለሱ ይገባል። አቶ መለስ ሞተውም በሺህ የሚቆጠር ሄክታር መሬት የሚመሩት ሚዲያው እንዲገነባላቸው በተደረገው የሌለ ስብዕናቸው ሳቢያም እንደሆን መረዳት ግድ እንደሚል ተናግረዋል።

“ስለዚህ” ይላሉ አሉ ኦቦ ቃሉ “ስለዚህ ህዝብ በቃኝ ብሎ በቀሰቀሰው ማእበል ውስጥ ገብቶ የማዕበሉ ፈጣሪ ለመሆንና የማስታወቂያ ይዘት ያላቸውን መግለጫዎች ከማተም በመቀራረብ አንድ ላይ መስራት ወደሚቻለበት መንገድ ባስቸኳይ ማምራቱ አንገብጋቢ ነው” ይላሉ፡፡

“አገሪቱ እየተቸበቸበች ነው። በዚህ መልኩ ፭ ዓመት ከቀጠልን ዋጋ የለንም” በማለት አቶ ጃዋር ለሰጡት አስተያየት ኦቦ ቃሉ “የኦሮሞ መሬት ፭ ዓመት የሚቆየ ዕድሜ የለውም” የሚል ማጠናከሪያ አስተያየት ሰጥተዋል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule