• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሃጫሉ፤ ሙዚቃ እና አብዮት

July 2, 2020 04:54 am by Editor Leave a Comment

“ሐጫሉ የሚሰራቸውን አዳዲስ ሙዚቃዎች አንሰማ ይሆናል። ግን ዘላለማዊ ነው። ከትውልድ ትውልድ የሚሸጋገሩ፤ ትውልድን ለትግል የሚያነሳሱ፤ ሐጫሉ የቆመለትን ዓላማ ከግብ የሚያደርሱ ሥራዎችን ሰርቶ አልፏል። መሞቱን እያወቀ፤ መስዋዕትነት እንደሚከፍል እያወቀ የኖረ እና የተሰዋ ሰው ነው። ሙዚቃዎቹን ለዘልዓለም እንሰማቸዋለን” አቶ በፍቃዱ ሞረዳ

በልጅነቱ የሙዚቃ ተሰጥዖውን ከሞረደባቸው መካከል የዳዊት መኮንን ሥራዎች ቀዳሚ እንደሆኑ ይናገር ነበር። ጊታር፣ ኪቦርድ እና ክራር ይሞካክር የነበረው ሐጫሉ በአንድ ወቅት እንደተናገረው ሰኚ ሞቲ የተባለው የመጀመሪያ የአልበም ሥራ አብዛኛው የተፃፈው በእስር በቆየባቸው አምስት አመታት ነው።

የፍቅር ሙዚቃዎችም አቀንቅኗል። ፖለቲካዊ ይዘት ያላቸው ሙዚቃዎቹ ግን የዛሬ ስብዕናውን ገንብተዋል። ከእነዚህ መካከል “ምኑን አለሁት” ያለበት ሙዚቃ ተጠቃሽ ነው። የቀድሞው ጋዜጠኛ በፍቃዱ ሞረዳ “ማለን ጂራ” የሚል ርዕስ የተሰጠውን እና ከአምስት አመታት በፊት ለአድማጭ የቀረበውን ሙዚቃ “በሕይወት እስካለሁ ድረስ እንጉርጉሮዬ ይሆናል” የሚሉት ነው። አቶ በፍቃዱ እንደሚሉት ይኸ ሙዚቃ የኦሮሞን ሕዝብ ባሕል፤ የኦሮሞን ሕዝብ ስሜት እና የልብ ትርታ የገለጸበት ነው።  

ይኸ ሙዚቃ ብርቱ ፖለቲካዊ መልዕክት ያዘለ ነው። “ሰባብረው ጨርሰውኛል። ምኑን ነው ያለሁት? በመካከላችን አጥር ሰርተው፤ ድንበር ሰርተው እንድንለያይ ያደረጉን እነሱ ናቸው። እነሱ ማን እንደሆኑ እኔ አላውቅም፤ እሱ ያውቃል፤ ጣት ይቀስርባቸዋል። እንዋደድ ነበረ፤ እንፋቀር ነበረ ግን እንዳንገናኝ አደረጉን። ይላል። እዚያ ውስጥ የሚያነሳቸው ታሪካዊ፣ ባሕላዊ የሆኑ ነገሮች አሉ” ሲሉ አቶ በፍቃዱ ይዘቱን ለዶይቼ ቬለ አስረድተዋል።

ሐጫሉ በሥራዎቹ ጠንካራ ፖለቲካዊ መልዕክት ማስተላለፍ የጀመረው ግን ቀደም ብሎ ነው። አቶ በፍቃዱ እንዲያውም አብዮተኛ ይሉታል። ቱሉ ጃላ የሚለው ሙዚቃው ሌላ ጠንከር ያለ ይዘት ያለው ነው። “ቱላ ጃላ [ወደ አማርኛ ሲተረጎም በተራራው ግርጌ] በሚለው ዘፈኑ ዐቢይ ሆኖ ይቀነቀን የነበረው ነገር እንደዋዛ ለምትጠፋው ሕይወታችን ሮሮን መሸከም ምንድነው? የሚል ነው። ሕይወታችን የትም እንደ ዋዛ ይጠፋል ግን ሮሮን መሸከም የለብንም። ተሸናፊነትን መቀበል የለብንም የሚል መልዕክት ነው የሚያስተላልፈው” ይላሉ አቶ በፍቃዱ።

አለን!

ሐጫሉ “ጂራ” ከማለቱ በፊት በሚሊኒየም አዳራሽ የኢትዮጵያ መንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት በተገኙበት ያሰማው ሽለላ የአገሪቱን ፖለቲካ የነቀነቀ ነበር። በወቅቱ ባለሥልጣናቱ በኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትወርክ የቀጥታ ሥርጭት በተላለፈው መሰናዶ በቀረበው የሐጫሉ ሽለላ ተበሳጭተው እስከመገሰጥ ደርሰዋል። አቶ በፍቃዱ ያ ሽለላ “በራሱ መጽሐፍ ሊሆን የሚችል ነው። ልብ ኖሮት ቁጭ ብሎ የሚጽፍ ደራሲ ካለ” ብለዋል።

በዚያ መድረክ ሐጫሉ

“ሸልል ሸልል ትሉኛላችሁ፤ ተነስቼ ልሸልል ወይ?

ጥፋ ጥፋ ትሉኛላችሁ ተነስቼ ልጥፋ ወይ?

እኔስ ምኑን ሸለልኩኝ በሀሳብ ተይዣለሁ፤

ሸልሎ ያልጠገበ ወንድ ቃሊቲ እስር ቤት ነው ያለው፤

ሸልሎ ያልጠገበ ወንድ ቂሊንጦ እስር ቤት ነው ያለው፤

ሸልሎ ያልጠገበ ወንድ ከርቸሌ ታስሮ ነው ያለው፤ አምቦ ከርቸሌ ነው ያለው፤

እኔስ ምኑን ሸለልኩኝ ሀሳብ እያናወዘኝ?”

ነበር ያለው።

“ሐጫሉ ዋናው ሞቱ የተደገሰለት ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ነው በእኔ እይታ” ብለዋል አቶ በፍቃዱ ሞረዳ። ከዚያ ጂራ የተሰኘው ሙዚቃ በሌላ ፖለቲካዊ መልዕክት ቀረበ። ይኸን ሙዚቃ “ተስፋን የፈነጠቀበት” እንደሆነ አቶ በፍቃዱ ያምናሉ።

“አለን፣ አለን፣ አለን፣ አለን ውለን ንጋት ልናይ

ሆድ አስፍቶልን አይ እኛ!

አይ እኛ! አወይ ነገር መርሳት

አወይ ነገር መርሳት፤ የእኛ ነገር

ለቁንጫ ዝላይ፣ ለትኋንም ሽሽት፣ ለአሞራም ክንፏን፤ ለአሞራም ክንፏን ለኤሊም ድንጋይ፣ እና ማን እምቢ ይላል? አለን ሁሉን ችለን አለን ሁሉን ችለን”  ሲል ጂራ የሚል ርዕስ በሰጠው ሙዚቃው ሐጫሉ ሁንዴሳ አቀንቅኗል። አቶ በፍቃዱ በ36 አመቱ እስካሁን ማንነታቸው ባልታወቀ ሰዎች የተገደለው ሐጫሉ ሁንዴሳ ስኬታማ ሥራዎች አበርክቷል ሲሉ ይናገራሉ።

“ሐጫሉ የሚሰራቸውን አዳዲስ ሙዚቃዎች አንሰማ ይሆናል። ግን ዘላለማዊ ነው። የሰራቸው ከበቂ በላይ ናቸው። ከትውልድ ትውልድ የሚሸጋገሩ፤ አሁንም ትውልድን ለትግል የሚያነሳሱ፤ ሐጫሉ የቆመለትን ዓላማ ከግብ የሚያደርሱ ሥራዎችን ሰርቶ አልፏል። መሞቱን እያወቀ፤ ዋጋ እንደሚከፍል፤ መስዋዕትነት እንደሚከፍል እያወቀ የኖረ እና የተሰዋ ሰው ነው። ሙዚቃዎቹን ለዘልዓለም እንሰማቸዋለን፤ እስካሁን የሰራቸው በቂ ናቸው” ብለዋል። 

አምቦ ተወልዶ ያደገው የ36 አመቱ ሐጫሉ ሁንዴሳ ሞት የቀሰቀሰው ተቃውሞ ቀድሞም በቅጡ መርጋት የተሳነውን የኢትዮጵያ ፖለቲካ እንደ አዲስ ይንጠው ይዟል። ሐጫሉ ሰኔ 22 ቀን 2012 ዓ.ም. ማንነታቸው ባልታወቀ ሰዎች በአዲስ አበባ ከተማ መገደሉ ከተሰማ በኋላ በመላው ኦሮሚያ በተቀሰቀሰው ተቃውሞ እስካሁን በትንሹ 81 ሰዎች መገደላቸውን የክልሉ መንግሥት አረጋግጧል።

አቶ በፍቃዱ “ሐጫሉ በሰው ልብ ውስጥ ሐውልት ሆኗል፤ ከዚህ በኋላ የሚዘፍነውም ዘፈን ላይኖር ይችላል፤ መዝፈን የሚገባውን፤ ማስተላለፍ የሚገባውን መልዕክት አስተላልፏል። እነዚህ ሥራዎቹ በትውልድ ልብ ውስጥ ለመኖር በቂ ሐውልቶች ናቸው ብዬ አስባለሁ” ሲሉ ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል። (ምንጭ DW Amharic)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column, Slider

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule