• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሃጫሉ፤ ሙዚቃ እና አብዮት

July 2, 2020 04:54 am by Editor Leave a Comment

“ሐጫሉ የሚሰራቸውን አዳዲስ ሙዚቃዎች አንሰማ ይሆናል። ግን ዘላለማዊ ነው። ከትውልድ ትውልድ የሚሸጋገሩ፤ ትውልድን ለትግል የሚያነሳሱ፤ ሐጫሉ የቆመለትን ዓላማ ከግብ የሚያደርሱ ሥራዎችን ሰርቶ አልፏል። መሞቱን እያወቀ፤ መስዋዕትነት እንደሚከፍል እያወቀ የኖረ እና የተሰዋ ሰው ነው። ሙዚቃዎቹን ለዘልዓለም እንሰማቸዋለን” አቶ በፍቃዱ ሞረዳ

በልጅነቱ የሙዚቃ ተሰጥዖውን ከሞረደባቸው መካከል የዳዊት መኮንን ሥራዎች ቀዳሚ እንደሆኑ ይናገር ነበር። ጊታር፣ ኪቦርድ እና ክራር ይሞካክር የነበረው ሐጫሉ በአንድ ወቅት እንደተናገረው ሰኚ ሞቲ የተባለው የመጀመሪያ የአልበም ሥራ አብዛኛው የተፃፈው በእስር በቆየባቸው አምስት አመታት ነው።

የፍቅር ሙዚቃዎችም አቀንቅኗል። ፖለቲካዊ ይዘት ያላቸው ሙዚቃዎቹ ግን የዛሬ ስብዕናውን ገንብተዋል። ከእነዚህ መካከል “ምኑን አለሁት” ያለበት ሙዚቃ ተጠቃሽ ነው። የቀድሞው ጋዜጠኛ በፍቃዱ ሞረዳ “ማለን ጂራ” የሚል ርዕስ የተሰጠውን እና ከአምስት አመታት በፊት ለአድማጭ የቀረበውን ሙዚቃ “በሕይወት እስካለሁ ድረስ እንጉርጉሮዬ ይሆናል” የሚሉት ነው። አቶ በፍቃዱ እንደሚሉት ይኸ ሙዚቃ የኦሮሞን ሕዝብ ባሕል፤ የኦሮሞን ሕዝብ ስሜት እና የልብ ትርታ የገለጸበት ነው።  

ይኸ ሙዚቃ ብርቱ ፖለቲካዊ መልዕክት ያዘለ ነው። “ሰባብረው ጨርሰውኛል። ምኑን ነው ያለሁት? በመካከላችን አጥር ሰርተው፤ ድንበር ሰርተው እንድንለያይ ያደረጉን እነሱ ናቸው። እነሱ ማን እንደሆኑ እኔ አላውቅም፤ እሱ ያውቃል፤ ጣት ይቀስርባቸዋል። እንዋደድ ነበረ፤ እንፋቀር ነበረ ግን እንዳንገናኝ አደረጉን። ይላል። እዚያ ውስጥ የሚያነሳቸው ታሪካዊ፣ ባሕላዊ የሆኑ ነገሮች አሉ” ሲሉ አቶ በፍቃዱ ይዘቱን ለዶይቼ ቬለ አስረድተዋል።

ሐጫሉ በሥራዎቹ ጠንካራ ፖለቲካዊ መልዕክት ማስተላለፍ የጀመረው ግን ቀደም ብሎ ነው። አቶ በፍቃዱ እንዲያውም አብዮተኛ ይሉታል። ቱሉ ጃላ የሚለው ሙዚቃው ሌላ ጠንከር ያለ ይዘት ያለው ነው። “ቱላ ጃላ [ወደ አማርኛ ሲተረጎም በተራራው ግርጌ] በሚለው ዘፈኑ ዐቢይ ሆኖ ይቀነቀን የነበረው ነገር እንደዋዛ ለምትጠፋው ሕይወታችን ሮሮን መሸከም ምንድነው? የሚል ነው። ሕይወታችን የትም እንደ ዋዛ ይጠፋል ግን ሮሮን መሸከም የለብንም። ተሸናፊነትን መቀበል የለብንም የሚል መልዕክት ነው የሚያስተላልፈው” ይላሉ አቶ በፍቃዱ።

አለን!

ሐጫሉ “ጂራ” ከማለቱ በፊት በሚሊኒየም አዳራሽ የኢትዮጵያ መንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት በተገኙበት ያሰማው ሽለላ የአገሪቱን ፖለቲካ የነቀነቀ ነበር። በወቅቱ ባለሥልጣናቱ በኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትወርክ የቀጥታ ሥርጭት በተላለፈው መሰናዶ በቀረበው የሐጫሉ ሽለላ ተበሳጭተው እስከመገሰጥ ደርሰዋል። አቶ በፍቃዱ ያ ሽለላ “በራሱ መጽሐፍ ሊሆን የሚችል ነው። ልብ ኖሮት ቁጭ ብሎ የሚጽፍ ደራሲ ካለ” ብለዋል።

በዚያ መድረክ ሐጫሉ

“ሸልል ሸልል ትሉኛላችሁ፤ ተነስቼ ልሸልል ወይ?

ጥፋ ጥፋ ትሉኛላችሁ ተነስቼ ልጥፋ ወይ?

እኔስ ምኑን ሸለልኩኝ በሀሳብ ተይዣለሁ፤

ሸልሎ ያልጠገበ ወንድ ቃሊቲ እስር ቤት ነው ያለው፤

ሸልሎ ያልጠገበ ወንድ ቂሊንጦ እስር ቤት ነው ያለው፤

ሸልሎ ያልጠገበ ወንድ ከርቸሌ ታስሮ ነው ያለው፤ አምቦ ከርቸሌ ነው ያለው፤

እኔስ ምኑን ሸለልኩኝ ሀሳብ እያናወዘኝ?”

ነበር ያለው።

“ሐጫሉ ዋናው ሞቱ የተደገሰለት ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ነው በእኔ እይታ” ብለዋል አቶ በፍቃዱ ሞረዳ። ከዚያ ጂራ የተሰኘው ሙዚቃ በሌላ ፖለቲካዊ መልዕክት ቀረበ። ይኸን ሙዚቃ “ተስፋን የፈነጠቀበት” እንደሆነ አቶ በፍቃዱ ያምናሉ።

“አለን፣ አለን፣ አለን፣ አለን ውለን ንጋት ልናይ

ሆድ አስፍቶልን አይ እኛ!

አይ እኛ! አወይ ነገር መርሳት

አወይ ነገር መርሳት፤ የእኛ ነገር

ለቁንጫ ዝላይ፣ ለትኋንም ሽሽት፣ ለአሞራም ክንፏን፤ ለአሞራም ክንፏን ለኤሊም ድንጋይ፣ እና ማን እምቢ ይላል? አለን ሁሉን ችለን አለን ሁሉን ችለን”  ሲል ጂራ የሚል ርዕስ በሰጠው ሙዚቃው ሐጫሉ ሁንዴሳ አቀንቅኗል። አቶ በፍቃዱ በ36 አመቱ እስካሁን ማንነታቸው ባልታወቀ ሰዎች የተገደለው ሐጫሉ ሁንዴሳ ስኬታማ ሥራዎች አበርክቷል ሲሉ ይናገራሉ።

“ሐጫሉ የሚሰራቸውን አዳዲስ ሙዚቃዎች አንሰማ ይሆናል። ግን ዘላለማዊ ነው። የሰራቸው ከበቂ በላይ ናቸው። ከትውልድ ትውልድ የሚሸጋገሩ፤ አሁንም ትውልድን ለትግል የሚያነሳሱ፤ ሐጫሉ የቆመለትን ዓላማ ከግብ የሚያደርሱ ሥራዎችን ሰርቶ አልፏል። መሞቱን እያወቀ፤ ዋጋ እንደሚከፍል፤ መስዋዕትነት እንደሚከፍል እያወቀ የኖረ እና የተሰዋ ሰው ነው። ሙዚቃዎቹን ለዘልዓለም እንሰማቸዋለን፤ እስካሁን የሰራቸው በቂ ናቸው” ብለዋል። 

አምቦ ተወልዶ ያደገው የ36 አመቱ ሐጫሉ ሁንዴሳ ሞት የቀሰቀሰው ተቃውሞ ቀድሞም በቅጡ መርጋት የተሳነውን የኢትዮጵያ ፖለቲካ እንደ አዲስ ይንጠው ይዟል። ሐጫሉ ሰኔ 22 ቀን 2012 ዓ.ም. ማንነታቸው ባልታወቀ ሰዎች በአዲስ አበባ ከተማ መገደሉ ከተሰማ በኋላ በመላው ኦሮሚያ በተቀሰቀሰው ተቃውሞ እስካሁን በትንሹ 81 ሰዎች መገደላቸውን የክልሉ መንግሥት አረጋግጧል።

አቶ በፍቃዱ “ሐጫሉ በሰው ልብ ውስጥ ሐውልት ሆኗል፤ ከዚህ በኋላ የሚዘፍነውም ዘፈን ላይኖር ይችላል፤ መዝፈን የሚገባውን፤ ማስተላለፍ የሚገባውን መልዕክት አስተላልፏል። እነዚህ ሥራዎቹ በትውልድ ልብ ውስጥ ለመኖር በቂ ሐውልቶች ናቸው ብዬ አስባለሁ” ሲሉ ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል። (ምንጭ DW Amharic)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News, Right Column, Slider

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “የገቡበት ገብተን አንድ ሰው አናስቀርም – በተለይ አመራሩን” ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ February 15, 2021 11:46 pm
  • የትግራይ ገበሬና የከተማ ነዋሪ በሠራዊታችን ላይ አንድ ጥይት አልተኮሰም – ሪር አድሚራል ክንዱ February 4, 2021 01:51 pm
  • ኢንተርፖል፤ የህወሃት ሳምሪዎች የማይካድራ ጭፍጭፋ ከቦኮሃራም የከፋ ነው February 4, 2021 11:10 am
  • ጄኔራሎች “ተገድለዋል” በሚል የሀሰት መረጃ ሲያሰራጭ የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ February 4, 2021 08:48 am
  • በትግራይ ክልል በሴቶች ላይ ተፈጸመ የተባለውን ጥቃት የሚያጣራ ግብረ ኃይል መቀሌ ገባ February 3, 2021 12:06 pm
  • ፓርቲዎች የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቶቻቸውን ወሰዱ February 3, 2021 10:29 am
  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule