• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሃጫሉ፤ ሙዚቃ እና አብዮት

July 2, 2020 04:54 am by Editor Leave a Comment

“ሐጫሉ የሚሰራቸውን አዳዲስ ሙዚቃዎች አንሰማ ይሆናል። ግን ዘላለማዊ ነው። ከትውልድ ትውልድ የሚሸጋገሩ፤ ትውልድን ለትግል የሚያነሳሱ፤ ሐጫሉ የቆመለትን ዓላማ ከግብ የሚያደርሱ ሥራዎችን ሰርቶ አልፏል። መሞቱን እያወቀ፤ መስዋዕትነት እንደሚከፍል እያወቀ የኖረ እና የተሰዋ ሰው ነው። ሙዚቃዎቹን ለዘልዓለም እንሰማቸዋለን” አቶ በፍቃዱ ሞረዳ

በልጅነቱ የሙዚቃ ተሰጥዖውን ከሞረደባቸው መካከል የዳዊት መኮንን ሥራዎች ቀዳሚ እንደሆኑ ይናገር ነበር። ጊታር፣ ኪቦርድ እና ክራር ይሞካክር የነበረው ሐጫሉ በአንድ ወቅት እንደተናገረው ሰኚ ሞቲ የተባለው የመጀመሪያ የአልበም ሥራ አብዛኛው የተፃፈው በእስር በቆየባቸው አምስት አመታት ነው።

የፍቅር ሙዚቃዎችም አቀንቅኗል። ፖለቲካዊ ይዘት ያላቸው ሙዚቃዎቹ ግን የዛሬ ስብዕናውን ገንብተዋል። ከእነዚህ መካከል “ምኑን አለሁት” ያለበት ሙዚቃ ተጠቃሽ ነው። የቀድሞው ጋዜጠኛ በፍቃዱ ሞረዳ “ማለን ጂራ” የሚል ርዕስ የተሰጠውን እና ከአምስት አመታት በፊት ለአድማጭ የቀረበውን ሙዚቃ “በሕይወት እስካለሁ ድረስ እንጉርጉሮዬ ይሆናል” የሚሉት ነው። አቶ በፍቃዱ እንደሚሉት ይኸ ሙዚቃ የኦሮሞን ሕዝብ ባሕል፤ የኦሮሞን ሕዝብ ስሜት እና የልብ ትርታ የገለጸበት ነው።  

ይኸ ሙዚቃ ብርቱ ፖለቲካዊ መልዕክት ያዘለ ነው። “ሰባብረው ጨርሰውኛል። ምኑን ነው ያለሁት? በመካከላችን አጥር ሰርተው፤ ድንበር ሰርተው እንድንለያይ ያደረጉን እነሱ ናቸው። እነሱ ማን እንደሆኑ እኔ አላውቅም፤ እሱ ያውቃል፤ ጣት ይቀስርባቸዋል። እንዋደድ ነበረ፤ እንፋቀር ነበረ ግን እንዳንገናኝ አደረጉን። ይላል። እዚያ ውስጥ የሚያነሳቸው ታሪካዊ፣ ባሕላዊ የሆኑ ነገሮች አሉ” ሲሉ አቶ በፍቃዱ ይዘቱን ለዶይቼ ቬለ አስረድተዋል።

ሐጫሉ በሥራዎቹ ጠንካራ ፖለቲካዊ መልዕክት ማስተላለፍ የጀመረው ግን ቀደም ብሎ ነው። አቶ በፍቃዱ እንዲያውም አብዮተኛ ይሉታል። ቱሉ ጃላ የሚለው ሙዚቃው ሌላ ጠንከር ያለ ይዘት ያለው ነው። “ቱላ ጃላ [ወደ አማርኛ ሲተረጎም በተራራው ግርጌ] በሚለው ዘፈኑ ዐቢይ ሆኖ ይቀነቀን የነበረው ነገር እንደዋዛ ለምትጠፋው ሕይወታችን ሮሮን መሸከም ምንድነው? የሚል ነው። ሕይወታችን የትም እንደ ዋዛ ይጠፋል ግን ሮሮን መሸከም የለብንም። ተሸናፊነትን መቀበል የለብንም የሚል መልዕክት ነው የሚያስተላልፈው” ይላሉ አቶ በፍቃዱ።

አለን!

ሐጫሉ “ጂራ” ከማለቱ በፊት በሚሊኒየም አዳራሽ የኢትዮጵያ መንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት በተገኙበት ያሰማው ሽለላ የአገሪቱን ፖለቲካ የነቀነቀ ነበር። በወቅቱ ባለሥልጣናቱ በኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትወርክ የቀጥታ ሥርጭት በተላለፈው መሰናዶ በቀረበው የሐጫሉ ሽለላ ተበሳጭተው እስከመገሰጥ ደርሰዋል። አቶ በፍቃዱ ያ ሽለላ “በራሱ መጽሐፍ ሊሆን የሚችል ነው። ልብ ኖሮት ቁጭ ብሎ የሚጽፍ ደራሲ ካለ” ብለዋል።

በዚያ መድረክ ሐጫሉ

“ሸልል ሸልል ትሉኛላችሁ፤ ተነስቼ ልሸልል ወይ?

ጥፋ ጥፋ ትሉኛላችሁ ተነስቼ ልጥፋ ወይ?

እኔስ ምኑን ሸለልኩኝ በሀሳብ ተይዣለሁ፤

ሸልሎ ያልጠገበ ወንድ ቃሊቲ እስር ቤት ነው ያለው፤

ሸልሎ ያልጠገበ ወንድ ቂሊንጦ እስር ቤት ነው ያለው፤

ሸልሎ ያልጠገበ ወንድ ከርቸሌ ታስሮ ነው ያለው፤ አምቦ ከርቸሌ ነው ያለው፤

እኔስ ምኑን ሸለልኩኝ ሀሳብ እያናወዘኝ?”

ነበር ያለው።

“ሐጫሉ ዋናው ሞቱ የተደገሰለት ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ነው በእኔ እይታ” ብለዋል አቶ በፍቃዱ ሞረዳ። ከዚያ ጂራ የተሰኘው ሙዚቃ በሌላ ፖለቲካዊ መልዕክት ቀረበ። ይኸን ሙዚቃ “ተስፋን የፈነጠቀበት” እንደሆነ አቶ በፍቃዱ ያምናሉ።

“አለን፣ አለን፣ አለን፣ አለን ውለን ንጋት ልናይ

ሆድ አስፍቶልን አይ እኛ!

አይ እኛ! አወይ ነገር መርሳት

አወይ ነገር መርሳት፤ የእኛ ነገር

ለቁንጫ ዝላይ፣ ለትኋንም ሽሽት፣ ለአሞራም ክንፏን፤ ለአሞራም ክንፏን ለኤሊም ድንጋይ፣ እና ማን እምቢ ይላል? አለን ሁሉን ችለን አለን ሁሉን ችለን”  ሲል ጂራ የሚል ርዕስ በሰጠው ሙዚቃው ሐጫሉ ሁንዴሳ አቀንቅኗል። አቶ በፍቃዱ በ36 አመቱ እስካሁን ማንነታቸው ባልታወቀ ሰዎች የተገደለው ሐጫሉ ሁንዴሳ ስኬታማ ሥራዎች አበርክቷል ሲሉ ይናገራሉ።

“ሐጫሉ የሚሰራቸውን አዳዲስ ሙዚቃዎች አንሰማ ይሆናል። ግን ዘላለማዊ ነው። የሰራቸው ከበቂ በላይ ናቸው። ከትውልድ ትውልድ የሚሸጋገሩ፤ አሁንም ትውልድን ለትግል የሚያነሳሱ፤ ሐጫሉ የቆመለትን ዓላማ ከግብ የሚያደርሱ ሥራዎችን ሰርቶ አልፏል። መሞቱን እያወቀ፤ ዋጋ እንደሚከፍል፤ መስዋዕትነት እንደሚከፍል እያወቀ የኖረ እና የተሰዋ ሰው ነው። ሙዚቃዎቹን ለዘልዓለም እንሰማቸዋለን፤ እስካሁን የሰራቸው በቂ ናቸው” ብለዋል። 

አምቦ ተወልዶ ያደገው የ36 አመቱ ሐጫሉ ሁንዴሳ ሞት የቀሰቀሰው ተቃውሞ ቀድሞም በቅጡ መርጋት የተሳነውን የኢትዮጵያ ፖለቲካ እንደ አዲስ ይንጠው ይዟል። ሐጫሉ ሰኔ 22 ቀን 2012 ዓ.ም. ማንነታቸው ባልታወቀ ሰዎች በአዲስ አበባ ከተማ መገደሉ ከተሰማ በኋላ በመላው ኦሮሚያ በተቀሰቀሰው ተቃውሞ እስካሁን በትንሹ 81 ሰዎች መገደላቸውን የክልሉ መንግሥት አረጋግጧል።

አቶ በፍቃዱ “ሐጫሉ በሰው ልብ ውስጥ ሐውልት ሆኗል፤ ከዚህ በኋላ የሚዘፍነውም ዘፈን ላይኖር ይችላል፤ መዝፈን የሚገባውን፤ ማስተላለፍ የሚገባውን መልዕክት አስተላልፏል። እነዚህ ሥራዎቹ በትውልድ ልብ ውስጥ ለመኖር በቂ ሐውልቶች ናቸው ብዬ አስባለሁ” ሲሉ ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል። (ምንጭ DW Amharic)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column, Slider

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule