• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የፌዴራል መንግሥት ከትግራይ ክልል ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት እንዳያደርግ ተወሰነ

October 7, 2020 12:56 am by Editor Leave a Comment

የፌዴሬሽን ምክር ቤት ማክሰኞ ባካሄደው መደበኛ ጉባዔ የፌደራል መንግሥት ከትግራይ ክልል መስተዳድር ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት እንዳያደርግ ውሳኔ አሳለፈ።

ይህ ውሳኔ ሊተላለፍ የቻለው ባለፈው ነሃሴ 30 2012 ዓ.ም የፌዴሬሽን ምክር ቤት አድርጎት በነበረው አስቸኳይ ጉባዔ በትግራይ ክልል የሚካሄደው ምርጫ እንዳልተደረገ፣ እንዳልተፈጸመ እና እንደማይጸና ውሳኔ ማስተላለፉን ተከትሎ ነው።

ውሳኔውን የሚከታተል የህገ መንግስት ጉዳዮች እና የማንነት ጉዳዮች አጣሪ ቋሚ ኮሚቴ ጉዳዩን ሲከታተል ቆይቶ ውሳኔው ባለመፈጸሙ ባዛሬው ዕለት ባደረገው መደበኛ ስብሰባ ነው ይህንን ወሳኔ ሊያሳልፍ ያቻለው።

ምክር ቤቱ በትግራይ ክልል መንግስት ላይ ሶስት ውሳኔዎችን ማሳለፉን ገልጿል።

የመጀመሪያው የትግራይ ክልል ያካሄደውን ኢ-ህገ መንስታዊ ምርጫ ተከትሎ ከተመሰረቱ የትግራይ ክልል ምክር ቤትና ከፍተኛ የህግ አስፈጻሚ አካል ጋር የፌዴራል መንግስት ምንም አይነት ግንኙነት እንደማያደርግ ወስኗል።

ሁለተኛው የፌደራል መንግስት የትግራይ ህዝብን የልማትና መሰረታዊ አገልግሎቶች ፍላጎት ማዕከል በማድረግ የከተማ እና የቀበሌ አስተዳደርን ጨምሮ በክልሉ ከሚገኙ ህጋዊ ተቋማት ብቻ የስራ ግንኙነት ያደርጋል።

ሶስተኛ የውሳኔውን አፈጻጸም በፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔ እና ጉዳዩ በሚመለከታቸው ቋሚ ኮሚቴ ክትትል መደረግ እንዳለበት ውሳኔ ተላልፏል። (ሰለሞን ጸጋዬ፤ ኢቢሲ)

ከዚሁ ጋር በተያያዘ “ወደ ትግራይ ተመለሱ” ተብለው በህወሓት የተጠሩት አባላት “አንሄድም” ማለታቸው ተሰምቷል።

ህወሃት የፌዴራል መንግስቱ ሕገ መንግስቱን እንደጣሰ ገልጾ በፌደራል ደረጃ ምርጫን በማሸነፍ በሚያዙ ኃላፊነቶችና ውክልና የነበራቸው የህወሃት አመራሮችና የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ኃላፊነታቸውን በመተው ወደ ድርጅታችሁ ህወሓት ጽ/ቤት ሪፖርት እንዲያደርጉ ነው ውሳኔ ያስተላለፈው።

በዚህም መሰረት የጠቅላይ ሚኒስትሩን ልዩ አማካሪ አርከበ ዕቁባይ (ዶ/ር)፣ የሕዳሴው ግድብ ሕዝባዊ ተሳትፊ ማስተባበሪያ ምክር ቤት ጽ/ቤት ዋና ዳይሬክተር ሮማን ገ/ሥላሴ ፣ የሰላም ሚኒስትር ዴኤታ አልማዝ መኮንን ፣ የትራንስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ ሙሉ ገ/እግዚአብሔር ፣ ዓባይ ወልዱን እና አዲስ ዓለም ባሌማን ጨምሮ 13 አመራሮች ለህወሃት ጽ/ቤት ሪፖርት እንዲያደርጉ ተጠይቀዋል። ከዚህ በተጨማሪም የህወሃት አባል የሆኑ 27 የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላትም ጥሪ ተላልፎላቸዋል።

በዚህ ጉዳይ ላይ አል ዐይን አስተያየት የጠየቃቸው የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ሕዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ምክር ቤት ጽ/ቤት ዋና ዳይሬክተር ሮማን ገ/ሥላሴ ጉዳዩን እንዳልሰሙት ተናግረዋል። ህወሃት ይህንኑ ውሳኔ በይፋዊ የፌስቡክ ገጹ ላይ ሪፖርት እንዲያደርጉ ከጠቀሳቸው አመራሮች መካከል ወ/ሮ ሮማን ገ/ስላሴ አምስተኛ ተራ ቁጥር ላይ የጠቀሳቸው እርሳቸው ግን ጥሪውን እንዳላዩትና እንዳላነበቡት ተናግረዋል።

በመጨረሻም “እኔ የምሰራው ሕዳሴው ግድብ ላይ ነው፣ግድቡ ደግሞ የሁሉም ብሔር ፣ የሁሉም ሕዝብ ሀብት ነው” ሲሉ ለአል ዐይን ምላሽ ሰጥተዋል። ጥሪውን በተመለከተ አስተያየት እንዲሰጡን የጠየቅናቸው ወ/ሮ ሮማን ምላሽ ከመስጠት ተቆጥበዋል።

ትናንትና በሁለቱ ምክር ቤቶች መክፈቻ ላይ የተገኙት ብቸኛዋ የትግራይ ሕዝብ ተወካይ ወ/ሮ ያየሽ ተስፋሁነኝም ህወሃት ከአባልነታቸው ተነስተው ሪፖርት እንዲያደርጉ ከጻፈላቸው የፓርቲው አባላት መካከል ቢሆኑም የህዝብ ድምፅ በማክበር ወደ ስብሰባው መምጣታቸውን ለኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ተናግረዋል።

ወ/ሮ ያየሽ

“የተለያየ ፓርቲ ወክለን ወደ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ብንገባም ምክር ቤት ስንገባ ግን የኢትዮጵያ ሕዝብ ወኪል ነን” ያሉት ወ/ሮ ያየሽ አንድ የምክር ቤት አባል ከአባልነቱ የሚነሳው የወከለው ህዝብ አይወክሉኝም ሲል አሊያም የስራ ዘመን ሲያበቃ መሆኑን ገልጸዋል። ዓለም አቀፍ በሆነው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ምርጫ እንዲራዘም መደረጉ የሕግ ልዕልና የታየበት መሆኑን ተናግረው በመክፈቻው ስብሰባ መገኘታቸው ትክክለኛ እና የሚጠበቅ ስለመሆኑ ገልጸዋል።

የሰላም ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ አልማዝ መኮንንም ሪፖርት እንዲያደርጉ ከተጠቀሱት መካከል ሲሆኑ ስለጉዳዩ እንዳልሰሙ ገልጸዋል።

ጥሪ የተደረገው ለምክር ቤት አባላት መሆኑን ነው የማውቀው ያሉት ወ/ሮ አልማዝ ትናንትና እስከምሽት ሥራ ላይ እንደነበሩና ስለእርሳቸውም ሆነ ስለሌሎች አመራሮች የሰሙት እንደሌለ ለአል ዐይን ተናግረዋል። (አል ዐይን አማርኛ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News, Politics

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule