
ይህ የምትመለከቱትን ፎት ያነሳሁት በጅዳው አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ውስጥ በሚገኝ የጸጥታ አስከባሪ ፖሊሶች አንድ ጽህፈት ቤት ውስጥ ነው፡፡ ይህች የምታይዋት እህትም ምን እዚያ አመጣት እንዳትሉ ! ከአንድ ወር ከሳምንት በፊት በኮንትራት ስራ ከሀገር ቤት የመጣች መሆኗን ሳውዲው የእድሜ ባለጸጋ አሰሪዋ ተነገረውኛል፡፡ እኔም ሆንኩ ይህንን ጉድ አብረውኝ የሚመከቱ እህቶቸ ሁላችንም ወደ ሃገር ቤት የሚሸኙ ዘመዶቻችንና ወዳጆቻችን አጅበን ነና የመጣነው የዚህች እህት ወደ አየር መንገዱ ለምን እንዳመጣች መጠየቅ አላስፈለገኝም ፡፡ በሰውነቷ ላይ ባረፈውን እስራትና ድብደባ ከመገለ እጇና ገላዋ ላይ ሰንበር የመሰለ የጉዳት ምልክት ይታያል፡፡ (ሙሉው ታሪክ እዚህ ላይ ይገኛል)
በጣም የሚያሳዝን ነገር ነው ጃል እንዴት ዝም ይባላል በተለያየ ጊዜ የነቢዩን ጽሁፎች አይቻለሁ ሁልጌዜ ይጮሃል ግን ማን እንደሰማው እንጃ እኛ ግን በጣም ቀልድ ላይ ነን ጎበዝ ይህ የህልውና ጉዳይ ነው ዝምታችን እጅግ ከፍቷል ይቺ ልጅ የሁላችን እህት ናት ስለዚህ ለምን ባፋጣኝ አንድ ነገር ለማድረግ አንነሳም ከዚ በፊት የሆነ ፔቲሽን ኦን ላይን ላይ አይቼ ሞላሁ ለዩኤን አፒል የሚደረግ ከዚያ በኋላ ግን ማንም ሲያነሳው እንሱም ድጋሚ የሆነ ፕሮግራስ ያለው ነገር ሲሰሩ አላየሁም እና ምን እያደረግን እንደሆነ ግራ ግባኝ ጎበዝ፡ እዚያ የሰይጣን ቁራጭ የሆኑ ፍጥረቶች መቼም በወገኖቻችንን ላይ ሲቀልዱ አይኖሩም ከላይም ቢሆን አንድ ቀን ዋጋቸውን ይቀበላሉ እኛ ግን ልንሰራው የሚገባንን ብንሰራ ጥሩ ነው ቢያንስ እኔ ምለው ምናለ እንዚህን ጽሁፎች ከጥሩ ሪፈረንስ ጋር ለኢንተርናሽናል ፍርድ ቤት አይጻፍም አቅሙ ያላችሁ ፕሊስ ስሩበት ስለ ኢትዮጵያ አምላክ ብላችሁ ። ምን ዋጋ አለው ሃገር ሃገር ብንል ራሳችን ካልተረዳዳን ከ እኛ መንግሥት ጋ ይምንቀራረብ ይህንን ያነበብንም ቢሆን አንድ ነገር እንዲደረግ ሥራዎች አይጀመሩም? እኛ ይህንን የምናነብ ሁላችን ለምን አስተያየት አንሰጥበትም ከተወሰነ ደቂቃ በፊት በርካት ጽሁፎችን በዚህ ገጽ ሳነብ በርካታ አስተያየቶችን አይቻለሁ እዚህ ላይ ግን አንድ ሃሳብ ሳጣ በጣም አዘንኩ ከማንም ምንም ሳንጠብቅ ባንድ ላይ ለመጮህ እንነሳ ባካችሁ ወገኖቼ የድረ ገጹ አዘጋጆች ይህን በተመክለከተ አንድ ወጥ የሆነ ነገር ብትሰሩ ጥሩ ነው እባካችሁ አሊያ ወገኔ ሃገር ሃገር ማለቱ ኮ ከራስ በላይ ነፋስ እንዳይሆንብን ባካችሁ……
አቡጊዳ.
hello the children of Ethiopia
it is terrible news for Ethiopians any way we have to struggle to destroy the woyane elit
IF WE UNITE WE STAND TOGETHER and IF WE DIVIDE we FALL DAWN
i