• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ደጀኔ ጣፋ፥ ከ “ተጠርጣሪ” ወደ “ተከሳሽ”!

September 1, 2020 03:52 pm by Editor Leave a Comment

የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ (ኦፌኮ) ምክትል ዋና ጸሀፊ የሆኑት አቶ ደጀኔ ጣፋ በሕገ መንግስት እና ሕገ መንግስታዊ ስርዓት ላይ በሚፈጸም ወንጀል ተከሰሱ። አቶ ደጀኔ ክስ የቀረበባቸው ዛሬ ማክሰኞ ነሐሴ 26፤ 2012 ባስቻለው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ወንጀል ችሎት ነው።

የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ በአቶ ደጀኔ እና አቶ መስተዋርድ ተማም በተባሉ ተጠርጣሪዎች ላይ ባቀረበው ክስ፤ ተከሳሾቹ የወንጀል ድርጊቱን የፈጸሙት በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራባቸው ከሚገኙ እና ካልተያዙ ግብረ አበሮቻቸው ጋር በመሆን እንደነበር ጠቅሷል። ሁለቱ ተከሳሾች “በኃይል፣ በዛቻ፣ በአድማ ወይም ህገ ወጥ በማናቸውም መንገድ በሕገ መንግስቱ የተቋቋመውን ስርዓት ለማፍረስ በማሰብ ከሰኔ 2012 ዓ.ም. በኋላ መንግስት የስልጣን ዘመኑ የሚጠናቀቅ በመሆኑ መንግስት ሆኖ መቀጠል ስለማይችል የሽግግር መንግስት እንዲቋቋም ግፊት ሲያደርጉ ነበር” ሲል አቃቤ ህግ በክስ ቻርጁ ላይ አስፍሯል።

ተከሳሾቹ “ ‘የኦሮሞ ህዝብ በአመጽ በአንድ ላይ በመነሳት የሀገር ባለቤትነቱን ማረጋገጥ አለበት፣ በሀገሪቱ የሚገኙ የምኒልክ እና ሌሎች ተመሳሳይ ሀውልቶች መፍረስ አለባቸው፣ የኦሮሞ ቄሮዎች የሌሎች ብሔር ተወላጆችን ንብረት ማቃጠል አለባቸው፣ በቄሮ ደም ቤተመንግስት የገባውን ኃይል በቄሮ ትግል ማስወገድ አለብን’ በማለት ህዝብን ሲቀሰቅሱ ቆይተዋል” ሲል የክስ ሰነዱ አትቷል። ተከሳሾቹ የድምጻዊ ሃጫሉ ሁንዴሳን ግድያ ተከትሎ ያሰቡትን አላማ ለማሳካት መንቀሳቀሳቸውንም አቃቤ ህግ በክሱ ጠቅሷል።

የሃጫሉ የቀብር ስነ ስርዓት በአምቦ እንዲከናወን አስክሬኑ በመሸኘት ላይ እያለ በአንደኛ ተከሳሽነት በክስ መዝገቡ የሰፈሩት አቶ ደጀኔ፤ በተመሳሳይ የምርመራ መዝገብ ተጠርጣሪ ከሆኑት አቶ በቀለ ገርባ በስልክ ትዕዛዝ መቀበላቸውን የክስ ሰነዱ ያመለክታል። የኦፌኮ ምክትል ሊቀመንበር የሆኑት አቶ በቀለ ለሌላኛው የፓርቲያቸው አመራራ አቶ ደጀኔ ሰጡት የተባለው ትዕዛዝ “ወጣቶችን አደራጅተው የሃጫሉ አስክሬን ከኦሮሚያ ክልል ፊንፊኔ ልዩ ዞን፣ ቡራዩ ከተማ፣ ኬላ ተብሎ ከሚጠራው ስፍራ እንዳያልፍ እና ወደ አዲስ አበባ እንዲመለስ እንዲያደርጉ” የሚያሳስብ እንደሆነ የክስ ሰነዱ ያብራራል።

አቶ ደጀኔ የተሰጣቸውን ትዕዛዝ ተቀብለው በቡራዩ ኬላ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በርካታ ወጣቶችን በማስተባበር መንገድ በማዘጋት እና ከሟች ቤተሰብ ፍቃድ ውጪ የሃጫሉን አስክሬን በማስገደድ ወደ አዲስ አበባ እንዲመለስ ማድረጋቸውን በክስ ሰነዱ ላይ ተቀምጧል። ተከሳሾቹ ከአቶ በቀለ እና ከሌሎችም ግብረ አበሮቻቸው ጋር በመሆን ያስተባበሯቸው ወጣቶች ጉዳት ለማድረስ የሚያስችሉ የተለያዩ መሳሪያዎችን የያዙ እንደነበርም ክሱ አመልክቷል።

የኦፌኮ ምክትል ዋና ጸሀፊ ድምጻዊ ሃጫሉ በተገደለበት ሰኔ 22፤ 2012 ለሊት፤ አምስት ሰዓት ከ10 ደቂቃ ገደማ በስልክ ሰጡት የተባለው ትዕዛዝም በክስ ሰነዱ ተጠቅሶባቸዋል። አቶ ደጀኔ የስልክ ትዕዛዙን ያስተላለፉት በኦሮሚያ ክልል ባሌ ዞን ደምበል ተብሎ በሚጠራ አካባቢ ለነበረ ግብረአበራቸው መሆኑን አቃቤ ህግ በክሱ አስፍሯል።

እስካሁንም በቁጥጥር ስር አለመዋሉ በሰነዱ የተገለጸው ይህ ግለሰብ፤ የሃጫሉን ግድያ በመቃወም “ወደ መንገድ መውጣታቸውን እና መንግስትን ከስልጣን ለማስወገድ የመጨረሻ ትግል እንደሚያደርጉ” ለአንደኛ ተከሳሽ ነግሯቸዋል ተብሏል። በስልክ ልውውጡ ወቅት አቶ ደጀኔ ግለሰቡን “በርቱ” ማለታቸውን እና “ሀገሪቷ የቄሮ በመሆኗ እንደፈለጉ እንዲያደርጉ” ትዕዛዝ መስጠታቸውን አቃቤ ህግ በክሱ አትቷል።

ተከሳሹ ከድምጻዊ ሃጫሉ ግድያ ማግስት፤ ሰኔ 23፤ 2012፤ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞን ነጆ ወረዳ አካባቢ ለነበረ ግብረአበራቸውም ሌላ ትዕዛዝ ማስተላለፋቸውም በክስ ሰነዱ ላይ ተቀምጧል። ለጊዜው ስሙ አለመታወቁ በሰነዱ ለተጠቀሰው ግብረአበር የተሰጠው ትዕዛዝ “ወጣቶች ተቀናጅተው በየአካባቢው የመንግስትን መዋቅር እንዲቆጣጠሩ” የሚል እንደነበር አቃቤ ህግ በክሱ ገልጿል።

በተከሳሾቹ በተነሳሳው “ሕገ መንግስታዊ ስርዓቱን የመናድ ተግባር በኦሮሚያ ክልል ባሌ ዞን፣ በኦሮሚያ ልዩ ዞን ቡራዩ ከተማ የተለያዩ ንብረቶች መውደማቸውን የአቃቤ ህግ ክስ ዘርዝሯል። አቃቤ ህግ በዚህ የወንጀል ተግባር ምክንያት ተነሳ ባለው ግጭት፤ በቡራዩ ከተማ የ2 ሰዎች እና በአዲስ አበበ ከተማ በተለያዩ ቦታዎች የስድስት ሰዎች ህይወት ጠፍቷል ብሏል።

አቶ ደጀኔ እና አቶ መስተዋርድ በተከሰሱበት ወንጀል “በህዝብ ደህንነት ላይ ከፍተኛ ቀውስ የደረሰ በመሆኑ ተከሳሾቹ በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን በፈጸሙት በሕገ መንግስትና በሕገ መንግስት ስርዓት ላይ በሚደረግ ወንጀል ተከሰዋል” ሲል አቃቤ ህግ በክስ ሰነዱ አስፍሯል። ተከሳሾቹ በክስ ሰነዱ የተጠቀሰባቸው የወንጀል ህግ አንቀጽ 238 (2) “ወንጀሉ ሲፈጸም በሕዝብ ደህንነት ወይም ኑሮ ላይ ከፍተኛ ቀውስ ደርሶ እንደሆነ፤ አድራጊው በዕድሜ ልክ እስራት ወይም ሞት ይቀጣል” በማለት ይደነግጋል።

በዛሬው የችሎት ውሎ የቀረቡት ሁለቱ ተከሳሾች የክስ ቻርጁ እንደደረሳቸው ጠበቃቸው አቶ ቦሬሳ በየነ ገልጸዋል። “የክስ ቻርጁ የመጀመሪያ ቀን የደረሰን ስለሆነ ክሱን አይተን አስፈላጊውን ዝግጅት አድርገን ክርክር ለማድረግ ተለዋጭ ቀጠሮ ጠይቀናል” ሲሉ ጠበቃ ቦሬሳ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። በዛሬው ችሎት የተከሳሾች የዋስትና መብት በተመለከተም በችሎት የነበሩ ሶስት ጠበቆች ጥያቄ ማቅረባቸውንም አክለዋል።

የዋስትና መብት ጥያቄ የቀረበለት የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ወንጀል ችሎት ጥያቄውን መርምሮ ተገቢውን ብይን ለመስጠት ለከነገ በስቲያ ሐሙስ ነሐሴ 28፤ 2012 ቀጠሮ ሰጥቷል። በሐሙሱ ችሎት፤ በክሱ ላይ በጠበቆች በኩል ለሚቀርበው ምላሽ ተለዋጭ ቀጠሮ እንደሚሰጥም የተከሳሾቹ ጠበቃ ገልጸዋል። (በተስፋለም ወልደየስ፥ Ethiopia Insider)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Law, Right Column Tagged With: chilot, dejene taffa, jawar massacre, ችሎት

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule