• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ደጀኔ ጣፋ፥ ከ “ተጠርጣሪ” ወደ “ተከሳሽ”!

September 1, 2020 03:52 pm by Editor Leave a Comment

የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ (ኦፌኮ) ምክትል ዋና ጸሀፊ የሆኑት አቶ ደጀኔ ጣፋ በሕገ መንግስት እና ሕገ መንግስታዊ ስርዓት ላይ በሚፈጸም ወንጀል ተከሰሱ። አቶ ደጀኔ ክስ የቀረበባቸው ዛሬ ማክሰኞ ነሐሴ 26፤ 2012 ባስቻለው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ወንጀል ችሎት ነው።

የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ በአቶ ደጀኔ እና አቶ መስተዋርድ ተማም በተባሉ ተጠርጣሪዎች ላይ ባቀረበው ክስ፤ ተከሳሾቹ የወንጀል ድርጊቱን የፈጸሙት በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራባቸው ከሚገኙ እና ካልተያዙ ግብረ አበሮቻቸው ጋር በመሆን እንደነበር ጠቅሷል። ሁለቱ ተከሳሾች “በኃይል፣ በዛቻ፣ በአድማ ወይም ህገ ወጥ በማናቸውም መንገድ በሕገ መንግስቱ የተቋቋመውን ስርዓት ለማፍረስ በማሰብ ከሰኔ 2012 ዓ.ም. በኋላ መንግስት የስልጣን ዘመኑ የሚጠናቀቅ በመሆኑ መንግስት ሆኖ መቀጠል ስለማይችል የሽግግር መንግስት እንዲቋቋም ግፊት ሲያደርጉ ነበር” ሲል አቃቤ ህግ በክስ ቻርጁ ላይ አስፍሯል።

ተከሳሾቹ “ ‘የኦሮሞ ህዝብ በአመጽ በአንድ ላይ በመነሳት የሀገር ባለቤትነቱን ማረጋገጥ አለበት፣ በሀገሪቱ የሚገኙ የምኒልክ እና ሌሎች ተመሳሳይ ሀውልቶች መፍረስ አለባቸው፣ የኦሮሞ ቄሮዎች የሌሎች ብሔር ተወላጆችን ንብረት ማቃጠል አለባቸው፣ በቄሮ ደም ቤተመንግስት የገባውን ኃይል በቄሮ ትግል ማስወገድ አለብን’ በማለት ህዝብን ሲቀሰቅሱ ቆይተዋል” ሲል የክስ ሰነዱ አትቷል። ተከሳሾቹ የድምጻዊ ሃጫሉ ሁንዴሳን ግድያ ተከትሎ ያሰቡትን አላማ ለማሳካት መንቀሳቀሳቸውንም አቃቤ ህግ በክሱ ጠቅሷል።

የሃጫሉ የቀብር ስነ ስርዓት በአምቦ እንዲከናወን አስክሬኑ በመሸኘት ላይ እያለ በአንደኛ ተከሳሽነት በክስ መዝገቡ የሰፈሩት አቶ ደጀኔ፤ በተመሳሳይ የምርመራ መዝገብ ተጠርጣሪ ከሆኑት አቶ በቀለ ገርባ በስልክ ትዕዛዝ መቀበላቸውን የክስ ሰነዱ ያመለክታል። የኦፌኮ ምክትል ሊቀመንበር የሆኑት አቶ በቀለ ለሌላኛው የፓርቲያቸው አመራራ አቶ ደጀኔ ሰጡት የተባለው ትዕዛዝ “ወጣቶችን አደራጅተው የሃጫሉ አስክሬን ከኦሮሚያ ክልል ፊንፊኔ ልዩ ዞን፣ ቡራዩ ከተማ፣ ኬላ ተብሎ ከሚጠራው ስፍራ እንዳያልፍ እና ወደ አዲስ አበባ እንዲመለስ እንዲያደርጉ” የሚያሳስብ እንደሆነ የክስ ሰነዱ ያብራራል።

አቶ ደጀኔ የተሰጣቸውን ትዕዛዝ ተቀብለው በቡራዩ ኬላ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በርካታ ወጣቶችን በማስተባበር መንገድ በማዘጋት እና ከሟች ቤተሰብ ፍቃድ ውጪ የሃጫሉን አስክሬን በማስገደድ ወደ አዲስ አበባ እንዲመለስ ማድረጋቸውን በክስ ሰነዱ ላይ ተቀምጧል። ተከሳሾቹ ከአቶ በቀለ እና ከሌሎችም ግብረ አበሮቻቸው ጋር በመሆን ያስተባበሯቸው ወጣቶች ጉዳት ለማድረስ የሚያስችሉ የተለያዩ መሳሪያዎችን የያዙ እንደነበርም ክሱ አመልክቷል።

የኦፌኮ ምክትል ዋና ጸሀፊ ድምጻዊ ሃጫሉ በተገደለበት ሰኔ 22፤ 2012 ለሊት፤ አምስት ሰዓት ከ10 ደቂቃ ገደማ በስልክ ሰጡት የተባለው ትዕዛዝም በክስ ሰነዱ ተጠቅሶባቸዋል። አቶ ደጀኔ የስልክ ትዕዛዙን ያስተላለፉት በኦሮሚያ ክልል ባሌ ዞን ደምበል ተብሎ በሚጠራ አካባቢ ለነበረ ግብረአበራቸው መሆኑን አቃቤ ህግ በክሱ አስፍሯል።

እስካሁንም በቁጥጥር ስር አለመዋሉ በሰነዱ የተገለጸው ይህ ግለሰብ፤ የሃጫሉን ግድያ በመቃወም “ወደ መንገድ መውጣታቸውን እና መንግስትን ከስልጣን ለማስወገድ የመጨረሻ ትግል እንደሚያደርጉ” ለአንደኛ ተከሳሽ ነግሯቸዋል ተብሏል። በስልክ ልውውጡ ወቅት አቶ ደጀኔ ግለሰቡን “በርቱ” ማለታቸውን እና “ሀገሪቷ የቄሮ በመሆኗ እንደፈለጉ እንዲያደርጉ” ትዕዛዝ መስጠታቸውን አቃቤ ህግ በክሱ አትቷል።

ተከሳሹ ከድምጻዊ ሃጫሉ ግድያ ማግስት፤ ሰኔ 23፤ 2012፤ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞን ነጆ ወረዳ አካባቢ ለነበረ ግብረአበራቸውም ሌላ ትዕዛዝ ማስተላለፋቸውም በክስ ሰነዱ ላይ ተቀምጧል። ለጊዜው ስሙ አለመታወቁ በሰነዱ ለተጠቀሰው ግብረአበር የተሰጠው ትዕዛዝ “ወጣቶች ተቀናጅተው በየአካባቢው የመንግስትን መዋቅር እንዲቆጣጠሩ” የሚል እንደነበር አቃቤ ህግ በክሱ ገልጿል።

በተከሳሾቹ በተነሳሳው “ሕገ መንግስታዊ ስርዓቱን የመናድ ተግባር በኦሮሚያ ክልል ባሌ ዞን፣ በኦሮሚያ ልዩ ዞን ቡራዩ ከተማ የተለያዩ ንብረቶች መውደማቸውን የአቃቤ ህግ ክስ ዘርዝሯል። አቃቤ ህግ በዚህ የወንጀል ተግባር ምክንያት ተነሳ ባለው ግጭት፤ በቡራዩ ከተማ የ2 ሰዎች እና በአዲስ አበበ ከተማ በተለያዩ ቦታዎች የስድስት ሰዎች ህይወት ጠፍቷል ብሏል።

አቶ ደጀኔ እና አቶ መስተዋርድ በተከሰሱበት ወንጀል “በህዝብ ደህንነት ላይ ከፍተኛ ቀውስ የደረሰ በመሆኑ ተከሳሾቹ በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን በፈጸሙት በሕገ መንግስትና በሕገ መንግስት ስርዓት ላይ በሚደረግ ወንጀል ተከሰዋል” ሲል አቃቤ ህግ በክስ ሰነዱ አስፍሯል። ተከሳሾቹ በክስ ሰነዱ የተጠቀሰባቸው የወንጀል ህግ አንቀጽ 238 (2) “ወንጀሉ ሲፈጸም በሕዝብ ደህንነት ወይም ኑሮ ላይ ከፍተኛ ቀውስ ደርሶ እንደሆነ፤ አድራጊው በዕድሜ ልክ እስራት ወይም ሞት ይቀጣል” በማለት ይደነግጋል።

በዛሬው የችሎት ውሎ የቀረቡት ሁለቱ ተከሳሾች የክስ ቻርጁ እንደደረሳቸው ጠበቃቸው አቶ ቦሬሳ በየነ ገልጸዋል። “የክስ ቻርጁ የመጀመሪያ ቀን የደረሰን ስለሆነ ክሱን አይተን አስፈላጊውን ዝግጅት አድርገን ክርክር ለማድረግ ተለዋጭ ቀጠሮ ጠይቀናል” ሲሉ ጠበቃ ቦሬሳ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። በዛሬው ችሎት የተከሳሾች የዋስትና መብት በተመለከተም በችሎት የነበሩ ሶስት ጠበቆች ጥያቄ ማቅረባቸውንም አክለዋል።

የዋስትና መብት ጥያቄ የቀረበለት የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ወንጀል ችሎት ጥያቄውን መርምሮ ተገቢውን ብይን ለመስጠት ለከነገ በስቲያ ሐሙስ ነሐሴ 28፤ 2012 ቀጠሮ ሰጥቷል። በሐሙሱ ችሎት፤ በክሱ ላይ በጠበቆች በኩል ለሚቀርበው ምላሽ ተለዋጭ ቀጠሮ እንደሚሰጥም የተከሳሾቹ ጠበቃ ገልጸዋል። (በተስፋለም ወልደየስ፥ Ethiopia Insider)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Law, Right Column Tagged With: chilot, dejene taffa, jawar massacre, ችሎት

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዛሬ ‘ኃያል ነን’ የሚሉ ሀገራት ኢትዮጵያ ላይ በሚዲያ /በመረጃ/፣ በዲፕሎማሲ፣ በሳይበር እና በተልእኮ የተቀነባበረ ‘ግራጫ ጦርነት’ እያካሄዱባት ነው” ጠ/ሚ ዐቢይ July 7, 2022 10:03 am
  • የኦሮሞ ልሂቃንና ፖለቲከኞች በአማራ ተወላጆች ላይ እየደረሰ ያለውን “የዘር ማጥፋት” ወንጀል እንዲያወግዙት አብን ጠየቀ July 6, 2022 01:38 pm
  • “አማራን ኦሮሚያ ውስጥ የመግደል እና የመጨፍጨፍ እቅድ የኦነግ ሳይሆን የኦሮሚያ ብልጽግና ነው” አቶ ሃንጋሳ July 6, 2022 01:53 am
  • “በኢትዮጵያዊያን የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት ሀገሪቱን ማተራመስ አለብን” አይማን አብድልአዚዝ ግብጻዊው ፖለቲከኛ July 5, 2022 12:57 pm
  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule