• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ደጀኔ ጣፋ፥ ከ “ተጠርጣሪ” ወደ “ተከሳሽ”!

September 1, 2020 03:52 pm by Editor Leave a Comment

የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ (ኦፌኮ) ምክትል ዋና ጸሀፊ የሆኑት አቶ ደጀኔ ጣፋ በሕገ መንግስት እና ሕገ መንግስታዊ ስርዓት ላይ በሚፈጸም ወንጀል ተከሰሱ። አቶ ደጀኔ ክስ የቀረበባቸው ዛሬ ማክሰኞ ነሐሴ 26፤ 2012 ባስቻለው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ወንጀል ችሎት ነው።

የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ በአቶ ደጀኔ እና አቶ መስተዋርድ ተማም በተባሉ ተጠርጣሪዎች ላይ ባቀረበው ክስ፤ ተከሳሾቹ የወንጀል ድርጊቱን የፈጸሙት በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራባቸው ከሚገኙ እና ካልተያዙ ግብረ አበሮቻቸው ጋር በመሆን እንደነበር ጠቅሷል። ሁለቱ ተከሳሾች “በኃይል፣ በዛቻ፣ በአድማ ወይም ህገ ወጥ በማናቸውም መንገድ በሕገ መንግስቱ የተቋቋመውን ስርዓት ለማፍረስ በማሰብ ከሰኔ 2012 ዓ.ም. በኋላ መንግስት የስልጣን ዘመኑ የሚጠናቀቅ በመሆኑ መንግስት ሆኖ መቀጠል ስለማይችል የሽግግር መንግስት እንዲቋቋም ግፊት ሲያደርጉ ነበር” ሲል አቃቤ ህግ በክስ ቻርጁ ላይ አስፍሯል።

ተከሳሾቹ “ ‘የኦሮሞ ህዝብ በአመጽ በአንድ ላይ በመነሳት የሀገር ባለቤትነቱን ማረጋገጥ አለበት፣ በሀገሪቱ የሚገኙ የምኒልክ እና ሌሎች ተመሳሳይ ሀውልቶች መፍረስ አለባቸው፣ የኦሮሞ ቄሮዎች የሌሎች ብሔር ተወላጆችን ንብረት ማቃጠል አለባቸው፣ በቄሮ ደም ቤተመንግስት የገባውን ኃይል በቄሮ ትግል ማስወገድ አለብን’ በማለት ህዝብን ሲቀሰቅሱ ቆይተዋል” ሲል የክስ ሰነዱ አትቷል። ተከሳሾቹ የድምጻዊ ሃጫሉ ሁንዴሳን ግድያ ተከትሎ ያሰቡትን አላማ ለማሳካት መንቀሳቀሳቸውንም አቃቤ ህግ በክሱ ጠቅሷል።

የሃጫሉ የቀብር ስነ ስርዓት በአምቦ እንዲከናወን አስክሬኑ በመሸኘት ላይ እያለ በአንደኛ ተከሳሽነት በክስ መዝገቡ የሰፈሩት አቶ ደጀኔ፤ በተመሳሳይ የምርመራ መዝገብ ተጠርጣሪ ከሆኑት አቶ በቀለ ገርባ በስልክ ትዕዛዝ መቀበላቸውን የክስ ሰነዱ ያመለክታል። የኦፌኮ ምክትል ሊቀመንበር የሆኑት አቶ በቀለ ለሌላኛው የፓርቲያቸው አመራራ አቶ ደጀኔ ሰጡት የተባለው ትዕዛዝ “ወጣቶችን አደራጅተው የሃጫሉ አስክሬን ከኦሮሚያ ክልል ፊንፊኔ ልዩ ዞን፣ ቡራዩ ከተማ፣ ኬላ ተብሎ ከሚጠራው ስፍራ እንዳያልፍ እና ወደ አዲስ አበባ እንዲመለስ እንዲያደርጉ” የሚያሳስብ እንደሆነ የክስ ሰነዱ ያብራራል።

አቶ ደጀኔ የተሰጣቸውን ትዕዛዝ ተቀብለው በቡራዩ ኬላ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በርካታ ወጣቶችን በማስተባበር መንገድ በማዘጋት እና ከሟች ቤተሰብ ፍቃድ ውጪ የሃጫሉን አስክሬን በማስገደድ ወደ አዲስ አበባ እንዲመለስ ማድረጋቸውን በክስ ሰነዱ ላይ ተቀምጧል። ተከሳሾቹ ከአቶ በቀለ እና ከሌሎችም ግብረ አበሮቻቸው ጋር በመሆን ያስተባበሯቸው ወጣቶች ጉዳት ለማድረስ የሚያስችሉ የተለያዩ መሳሪያዎችን የያዙ እንደነበርም ክሱ አመልክቷል።

የኦፌኮ ምክትል ዋና ጸሀፊ ድምጻዊ ሃጫሉ በተገደለበት ሰኔ 22፤ 2012 ለሊት፤ አምስት ሰዓት ከ10 ደቂቃ ገደማ በስልክ ሰጡት የተባለው ትዕዛዝም በክስ ሰነዱ ተጠቅሶባቸዋል። አቶ ደጀኔ የስልክ ትዕዛዙን ያስተላለፉት በኦሮሚያ ክልል ባሌ ዞን ደምበል ተብሎ በሚጠራ አካባቢ ለነበረ ግብረአበራቸው መሆኑን አቃቤ ህግ በክሱ አስፍሯል።

እስካሁንም በቁጥጥር ስር አለመዋሉ በሰነዱ የተገለጸው ይህ ግለሰብ፤ የሃጫሉን ግድያ በመቃወም “ወደ መንገድ መውጣታቸውን እና መንግስትን ከስልጣን ለማስወገድ የመጨረሻ ትግል እንደሚያደርጉ” ለአንደኛ ተከሳሽ ነግሯቸዋል ተብሏል። በስልክ ልውውጡ ወቅት አቶ ደጀኔ ግለሰቡን “በርቱ” ማለታቸውን እና “ሀገሪቷ የቄሮ በመሆኗ እንደፈለጉ እንዲያደርጉ” ትዕዛዝ መስጠታቸውን አቃቤ ህግ በክሱ አትቷል።

ተከሳሹ ከድምጻዊ ሃጫሉ ግድያ ማግስት፤ ሰኔ 23፤ 2012፤ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞን ነጆ ወረዳ አካባቢ ለነበረ ግብረአበራቸውም ሌላ ትዕዛዝ ማስተላለፋቸውም በክስ ሰነዱ ላይ ተቀምጧል። ለጊዜው ስሙ አለመታወቁ በሰነዱ ለተጠቀሰው ግብረአበር የተሰጠው ትዕዛዝ “ወጣቶች ተቀናጅተው በየአካባቢው የመንግስትን መዋቅር እንዲቆጣጠሩ” የሚል እንደነበር አቃቤ ህግ በክሱ ገልጿል።

በተከሳሾቹ በተነሳሳው “ሕገ መንግስታዊ ስርዓቱን የመናድ ተግባር በኦሮሚያ ክልል ባሌ ዞን፣ በኦሮሚያ ልዩ ዞን ቡራዩ ከተማ የተለያዩ ንብረቶች መውደማቸውን የአቃቤ ህግ ክስ ዘርዝሯል። አቃቤ ህግ በዚህ የወንጀል ተግባር ምክንያት ተነሳ ባለው ግጭት፤ በቡራዩ ከተማ የ2 ሰዎች እና በአዲስ አበበ ከተማ በተለያዩ ቦታዎች የስድስት ሰዎች ህይወት ጠፍቷል ብሏል።

አቶ ደጀኔ እና አቶ መስተዋርድ በተከሰሱበት ወንጀል “በህዝብ ደህንነት ላይ ከፍተኛ ቀውስ የደረሰ በመሆኑ ተከሳሾቹ በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን በፈጸሙት በሕገ መንግስትና በሕገ መንግስት ስርዓት ላይ በሚደረግ ወንጀል ተከሰዋል” ሲል አቃቤ ህግ በክስ ሰነዱ አስፍሯል። ተከሳሾቹ በክስ ሰነዱ የተጠቀሰባቸው የወንጀል ህግ አንቀጽ 238 (2) “ወንጀሉ ሲፈጸም በሕዝብ ደህንነት ወይም ኑሮ ላይ ከፍተኛ ቀውስ ደርሶ እንደሆነ፤ አድራጊው በዕድሜ ልክ እስራት ወይም ሞት ይቀጣል” በማለት ይደነግጋል።

በዛሬው የችሎት ውሎ የቀረቡት ሁለቱ ተከሳሾች የክስ ቻርጁ እንደደረሳቸው ጠበቃቸው አቶ ቦሬሳ በየነ ገልጸዋል። “የክስ ቻርጁ የመጀመሪያ ቀን የደረሰን ስለሆነ ክሱን አይተን አስፈላጊውን ዝግጅት አድርገን ክርክር ለማድረግ ተለዋጭ ቀጠሮ ጠይቀናል” ሲሉ ጠበቃ ቦሬሳ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። በዛሬው ችሎት የተከሳሾች የዋስትና መብት በተመለከተም በችሎት የነበሩ ሶስት ጠበቆች ጥያቄ ማቅረባቸውንም አክለዋል።

የዋስትና መብት ጥያቄ የቀረበለት የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ወንጀል ችሎት ጥያቄውን መርምሮ ተገቢውን ብይን ለመስጠት ለከነገ በስቲያ ሐሙስ ነሐሴ 28፤ 2012 ቀጠሮ ሰጥቷል። በሐሙሱ ችሎት፤ በክሱ ላይ በጠበቆች በኩል ለሚቀርበው ምላሽ ተለዋጭ ቀጠሮ እንደሚሰጥም የተከሳሾቹ ጠበቃ ገልጸዋል። (በተስፋለም ወልደየስ፥ Ethiopia Insider)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Law, Right Column Tagged With: chilot, dejene taffa, jawar massacre, ችሎት

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “የገቡበት ገብተን አንድ ሰው አናስቀርም – በተለይ አመራሩን” ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ February 15, 2021 11:46 pm
  • የትግራይ ገበሬና የከተማ ነዋሪ በሠራዊታችን ላይ አንድ ጥይት አልተኮሰም – ሪር አድሚራል ክንዱ February 4, 2021 01:51 pm
  • ኢንተርፖል፤ የህወሃት ሳምሪዎች የማይካድራ ጭፍጭፋ ከቦኮሃራም የከፋ ነው February 4, 2021 11:10 am
  • ጄኔራሎች “ተገድለዋል” በሚል የሀሰት መረጃ ሲያሰራጭ የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ February 4, 2021 08:48 am
  • በትግራይ ክልል በሴቶች ላይ ተፈጸመ የተባለውን ጥቃት የሚያጣራ ግብረ ኃይል መቀሌ ገባ February 3, 2021 12:06 pm
  • ፓርቲዎች የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቶቻቸውን ወሰዱ February 3, 2021 10:29 am
  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule