• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በኢትዮጵያ የሚኒስትሮች ም/ቤት የህወሓት ኅልውና እየከሰመ ነው

January 22, 2020 12:10 am by Editor 1 Comment

እጅግ መረን በለቀቀ ሁኔታ የኢትዮጵያን የመንግሥት ሥልጣን ተቆጣጥሮ የነበረው የተገንጣይ ወንበዴዎች ቡድን እና በዚሁ የተገንጣይ ቡድን ስም አገር ሲገዛ የኖረው ትህነግ/ህወሓት በአሁኑ ወቅት በሚኒስትሮች ም/ቤት ያለው ኅልውና ሊከሰም ጥቂት ነው የቀረው።

የጠ/ሚ/ር፣ የውጭ ጉዳይ፣ የመከላከያ (ኤታ ማዦር ሹም)፣ የማስታወቂያ (በኋላ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን የተባለው) ወዘተ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶችን በብቸኝነትና በማንአለብኝነት ለበርካታ ዓመታት ሲቆጣጠር የነበረውን የተገንጣይ ቡድን በሚኒስትሮች ም/ቤት ትወክለው ነበረችው ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሔር ከሥልጣኗ ተወግዳለች። የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት የላከውን መረጃ የኦሮሚያ ብልጽግና ፓርቲ አማርኛ ልሳን በፌስቡክ አረጋግጧል።

የህወሓት የፖሊትቢሮ አባልና የደብረጽዮን ምክትል የሆነችው ፈትለወርቅ (ሳሞራ የኑስ ባወጣላት የበረሃ ስሟ “ሞንጆሪኖ” ተብላ የምትጠራው) በሚኒስትሮች ም/ቤት የህወሓት ሥራ አስፈጻሚ ብቸኛ ተወካይ ነበረች።

ሌላኛዋ የህወሓት አባል ያለም ጸጋዬ የትህነግ የሥራ አስፈጻሚ አባል ባትሆንም ህወሓትን በሚኒስትሮች ም/ቤት የምትወክል ብቸኛዋ ሆና ቀጥላለች።

ህወሓት ጠፍጥፋ በሠራቻቸው ፓርቲዎች የመሠረተው ኢህአዴግ የተባለው ድርጅት ወደከርሰ መቃብር ከወረደ በኋላ አባልና አጋር የተባሉት ፓርቲዎች በሙሉ በመዋሃድ ብልጽግና ፓርቲን ሲመሠርቱ ትህነግ/ህወሓት ብቻዋን አልቀላቀልም በማለት እንደስሟ ተገንጥላ ቆይታ ነበር። በመጨረሻም ብልጽግናን አልቀላቀልም፣ ንብረቴን መልሱልኝ በማለት መግለጫ ማውጣቷ ይታወሳል።

የፌዴራሉንና በአጠቃላይ የኢትዮጵያን ከፍተኛ የሥልጣን ቦታዎችን ያለገደብ እና ያለበቂ ዕውቀትና የትምህርት ዝግጅት (አለ ተብሎ የተመዘገበውም በግዢ ከዲግሪ ወፍጮቤቶች የተመረተ ነው) በግፍ ሲገዛ የነበረው የተገንጣይ ወንበዴዎች ቡድን ከምኒልክ ቤተመንግሥት ከተወገደ በኋላ የትግራይን ሕዝብ አግቶ በአፈና እየገዛ ይገኛል። ሰሞኑን የተነሳበት ሕዝባዊ ተቃውሞም የትግራይ ሕዝብ ይህንን የጥቂቶች ቡድን ከላዩ ለመጣል ፈር የሚቀድ ሊሆን ይችላል የሚል ግምት ተሰጥቶታል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፤ ፈትለወርቅን በሦስት መሥመር ደብዳቤ ካባረሯት በኋላ በምትኳ የቀድሞው የንግድ ሚ/ር የነበሩትን መላኩ አለበልን በሚኒስትርነት ሾመዋል። ህወሓትን አልፈልግም ብለው የወጡትና አገርበቀል መፍትሔዎችን በማመንጨት የ3.5 ሚሊዮን ብር ተሸላሚ የሆኑት አብርሃም በላይ (ዶ/ር)፤ ጌታሁን መኩሪያን (ዶ/ር) በመተካት የኢኖቬሽን እና የቴክኖሎጂ ሚኒስትር ሆነው ተሾመዋል። ጌታሁን የትምህርት ሚ/ር ሆነዋል።

በፈትለወርቅ መነሳት ከፍተኛ ክስረት የደረሰባት ትህነግ/ህወሓት ጉዳዩን ከሕዝብ ጋር ጠብ የመጫሪያ ስልት አድርጋ ለመጠቀም የሞከረችው የተሳካ ባይሆንም ከምርጫው በኋላ ብልጽግና እንደ ፓርቲ የመንግሥትን ሥልጣን የሚይዝ ከሆነ የህወሓት ኅልውና ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ከፌዴራል መንግሥት ተወግዶ እንደ ፈጣሪዋ መለስ የሙት ዓመቷን ራሷ እየዘከረች የምትኖር ትሆናለች በማለት በፌስቡክ ገጻችን ለጎልጉል አስተያየታቸውን የላኩ ተሳልቀዋል።

ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: fetlework, Full Width Top, Middle Column, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. GET BOG says

    January 24, 2020 04:49 pm at 4:49 pm

    MINM MADREG AYCHALEM AMNO MEKEBEL NEW YEGIZE GUDAY NEW HULGEZE SILTAN LAY AYNORIM BELULEGN

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am
  • የኦነግ ሸኔ አባላትን ዕድሜ ለማሳጠር የጂፒኤስ ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ እየዋለ ነው December 7, 2020 12:38 am
  • የቆሰሉ ወታደሮች በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተጎበኙ December 6, 2020 11:41 pm
  • “ከዚህ በኋላ ይዘን እንታገላለን እንጂ ሠጥተን አንጠይቅም” ኮሎኔል ደመቀ December 2, 2020 12:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule