• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በኢትዮጵያ የሚኒስትሮች ም/ቤት የህወሓት ኅልውና እየከሰመ ነው

January 22, 2020 12:10 am by Editor 1 Comment

እጅግ መረን በለቀቀ ሁኔታ የኢትዮጵያን የመንግሥት ሥልጣን ተቆጣጥሮ የነበረው የተገንጣይ ወንበዴዎች ቡድን እና በዚሁ የተገንጣይ ቡድን ስም አገር ሲገዛ የኖረው ትህነግ/ህወሓት በአሁኑ ወቅት በሚኒስትሮች ም/ቤት ያለው ኅልውና ሊከሰም ጥቂት ነው የቀረው።

የጠ/ሚ/ር፣ የውጭ ጉዳይ፣ የመከላከያ (ኤታ ማዦር ሹም)፣ የማስታወቂያ (በኋላ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን የተባለው) ወዘተ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶችን በብቸኝነትና በማንአለብኝነት ለበርካታ ዓመታት ሲቆጣጠር የነበረውን የተገንጣይ ቡድን በሚኒስትሮች ም/ቤት ትወክለው ነበረችው ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሔር ከሥልጣኗ ተወግዳለች። የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት የላከውን መረጃ የኦሮሚያ ብልጽግና ፓርቲ አማርኛ ልሳን በፌስቡክ አረጋግጧል።

የህወሓት የፖሊትቢሮ አባልና የደብረጽዮን ምክትል የሆነችው ፈትለወርቅ (ሳሞራ የኑስ ባወጣላት የበረሃ ስሟ “ሞንጆሪኖ” ተብላ የምትጠራው) በሚኒስትሮች ም/ቤት የህወሓት ሥራ አስፈጻሚ ብቸኛ ተወካይ ነበረች።

ሌላኛዋ የህወሓት አባል ያለም ጸጋዬ የትህነግ የሥራ አስፈጻሚ አባል ባትሆንም ህወሓትን በሚኒስትሮች ም/ቤት የምትወክል ብቸኛዋ ሆና ቀጥላለች።

ህወሓት ጠፍጥፋ በሠራቻቸው ፓርቲዎች የመሠረተው ኢህአዴግ የተባለው ድርጅት ወደከርሰ መቃብር ከወረደ በኋላ አባልና አጋር የተባሉት ፓርቲዎች በሙሉ በመዋሃድ ብልጽግና ፓርቲን ሲመሠርቱ ትህነግ/ህወሓት ብቻዋን አልቀላቀልም በማለት እንደስሟ ተገንጥላ ቆይታ ነበር። በመጨረሻም ብልጽግናን አልቀላቀልም፣ ንብረቴን መልሱልኝ በማለት መግለጫ ማውጣቷ ይታወሳል።

የፌዴራሉንና በአጠቃላይ የኢትዮጵያን ከፍተኛ የሥልጣን ቦታዎችን ያለገደብ እና ያለበቂ ዕውቀትና የትምህርት ዝግጅት (አለ ተብሎ የተመዘገበውም በግዢ ከዲግሪ ወፍጮቤቶች የተመረተ ነው) በግፍ ሲገዛ የነበረው የተገንጣይ ወንበዴዎች ቡድን ከምኒልክ ቤተመንግሥት ከተወገደ በኋላ የትግራይን ሕዝብ አግቶ በአፈና እየገዛ ይገኛል። ሰሞኑን የተነሳበት ሕዝባዊ ተቃውሞም የትግራይ ሕዝብ ይህንን የጥቂቶች ቡድን ከላዩ ለመጣል ፈር የሚቀድ ሊሆን ይችላል የሚል ግምት ተሰጥቶታል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፤ ፈትለወርቅን በሦስት መሥመር ደብዳቤ ካባረሯት በኋላ በምትኳ የቀድሞው የንግድ ሚ/ር የነበሩትን መላኩ አለበልን በሚኒስትርነት ሾመዋል። ህወሓትን አልፈልግም ብለው የወጡትና አገርበቀል መፍትሔዎችን በማመንጨት የ3.5 ሚሊዮን ብር ተሸላሚ የሆኑት አብርሃም በላይ (ዶ/ር)፤ ጌታሁን መኩሪያን (ዶ/ር) በመተካት የኢኖቬሽን እና የቴክኖሎጂ ሚኒስትር ሆነው ተሾመዋል። ጌታሁን የትምህርት ሚ/ር ሆነዋል።

በፈትለወርቅ መነሳት ከፍተኛ ክስረት የደረሰባት ትህነግ/ህወሓት ጉዳዩን ከሕዝብ ጋር ጠብ የመጫሪያ ስልት አድርጋ ለመጠቀም የሞከረችው የተሳካ ባይሆንም ከምርጫው በኋላ ብልጽግና እንደ ፓርቲ የመንግሥትን ሥልጣን የሚይዝ ከሆነ የህወሓት ኅልውና ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ከፌዴራል መንግሥት ተወግዶ እንደ ፈጣሪዋ መለስ የሙት ዓመቷን ራሷ እየዘከረች የምትኖር ትሆናለች በማለት በፌስቡክ ገጻችን ለጎልጉል አስተያየታቸውን የላኩ ተሳልቀዋል።

ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: fetlework, Full Width Top, Middle Column, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. GET BOG says

    January 24, 2020 04:49 pm at 4:49 pm

    MINM MADREG AYCHALEM AMNO MEKEBEL NEW YEGIZE GUDAY NEW HULGEZE SILTAN LAY AYNORIM BELULEGN

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule