• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ህወሃት “ተቃዋሚዎችን” በዓመት ሦስቴ ደጄን ከረገጣችሁ ይበቃችኋል አላቸው

December 12, 2016 06:58 pm by Editor 1 Comment

በጥልቅ እየታደስኩ ነው የሚለው ህወሃት/ኢህአዴግ በየቀኑ በጥልቅ መበስበሱን እና ለመታደስ ፈጽሞ የማይችል መሆኑን የሚመለክቱ ተግባራትን ሲፈጽም እየታየ ነው፡፡ የትግራይ ተወላጆችን ወደኋላ በማድረግ ከመድረኩ በማውጣት የፊት ገጾች እንዲሆኑ ከትግራ ውጭ ያሉ ግለሰቦችን በማስቀመጥ ሥራውን በምክትሎቻቸው የትግራይ ተወላጆች እንዲሠራ እደረገ ነው፡፡ የፖለቲካ ምህዳሩን አሰፋለሁ፣ አሳታፊ እሆናለሁ፣ … እያለ የፖለቲካ አመራሮችን፣ ጋዜጠኞችን፣ የተቃዋሚ ኃይላትን ያስራል፤ ሕዝቡን ያሰቃያል፣ ይገድላል፡፡

አዲስ አድማስ ተቃዋሚ ፓርቲዎች በዓመት ሦስት ጊዜ ፓርላማ ገብተው በውይይት እንዲሳተፉ ለማድረግ ማኑዋል እየተዘጋጀ መሆኑን በመጥቀስ “ተቃዋሚዎች፤ ሳንመረጥ ፓርላማ አንገባም አሉ” በሚል ርዕስ የዘገበው እንዲህ ይነበባል፤

tigistu-so-called-oppositionመንግስት ተቃዋሚ ፓርቲዎች በዓመት ሦስት ጊዜ ፓርላማ ገብተው በውይይት እንዲሳተፉ ለማድረግ ማኑዋል እየተዘጋጀ መሆኑን የገለፀ ሲሆን ተቃዋሚዎች በበኩላቸው፣ ሳይወከሉ በፓርላማ ውይይት ህገ መንግስታዊ አይደለም ሲሉ ተችተዋል።

ተቃዋሚዎች ለምን አላማ ከመንግስት ጋር በዚህ መንገድ እንዲወያዩ እንደተፈለገ አይገባንም ያሉት የአረና ም/ሊቀመንበር አቶ ጎይቶም ፀጋዬ፤ ውይይቱ በፓርላማ መደረጉ ምናልባት ኢህአዴግ ብቻውን ተቆጣጥሮታል የሚለውን ሃሜት ለማስቀረት ካልሆነ በቀር ሌላ ፋይዳ አይኖረውም ብለዋል። “የተቃዋሚዎች የመወሰን ሚና ጨርሶ በሌለበት ሁኔታ የሚደረጉ ውይይቶች ጥቅማቸው እምብዛም ነው” ይላሉ አቶ ጎይቶም፡፡

የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) ም/ሊቀመንበር አቶ ሙላቱ ገመቹ በበኩላቸው፤ ተቃዋሚዎች የህዝብ ውክልና ሳይኖራቸው በፓርላማ መገኘታቸው በምን አግባብ ነው? ሲሉ ይጠይቃሉ፡፡ “ፓርላማው ላይ መገኘት የሚቻለው በህዝብ ሲወከሉ ብቻ ነው” ያሉት አቶ ሙላቱ፤ ተቃዋሚዎች የመወሰን ሚና ሳይኖራቸው የሚያደርጉት ውይይት ምንም ፋይዳ አይኖረውም ብለዋል፡፡

“መንግስት ከተቃዋሚዎች ምክር የሚፈልግ ከሆነ፣ በፓርላማው መሆን የለበትም” ያሉት አቶ ሙላቱ፤ ሌሎች ልዩ መድረኮች መዘጋጀት አለባቸው ይላሉ፡፡ ተግባራዊ ይደረጋል ብለው እንደማያምኑ የተናገሩት ም/ሊቀመንበሩ፤ ከዚህ በፊት መሰል የውይይት መድረኮች ይዘጋጃሉ ተብሎ መቅረቱን ያስታውሳሉ፡፡ አሁን መንግስት ማድረግ ያለበት ለህዝብ ጥያቄ መልስ መስጠት ነው ብለዋል – አቶ ሙላቱ፡፡

የፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አባል የሆነው የኢትዮጵያ ራዕይ ፓርቲ (ኢራፓ) ፕሬዚዳንት አቶ ተሻለ ሰብሮ በበኩላቸው፤ “መንግስት ከተቃዋሚዎች ጋር ይወያያል የተባለው ከ2002 ምርጫ ማግስት ጀምሮ ነው፤ ሆኖም ተፈፅሞ አያውቅም፤ የአሁኑም የፓርላማው ውይይት የተስፋ ቃል ነው” ይላሉ፡፡

የመንግስትና የተቃዋሚዎች ውይይት እስካሁን ተግባራዊ ሲሆን አለማየታቸውን የገለፁት አቶ ተሻለ፤ “በእውን የሚደረግ ከሆነም፣ “በምን አግባብ ይከናወናል? መቼ ነው የሚጀምረው? እንዴት ነው ተቃዋሚዎች የሚሳተፉት? የሚሉትን ጥያቄዎችን መመለስ አለበት” ብለዋል፡፡ “የውይይት መድረኩ እውን ይሆናል ብለን እንድናምንና ምልክቶች መታየት አለባቸው ብለዋል” – ሲሉ አክለዋል፡፡

“የተቃዋሚዎች በፓርላማ መሳተፍ ምንን መርህ አድርጎ ነው? ህገ መንግስታዊ ነው? በአዋጅ የሚያሳትፍ ነው? የፖሊሲ አቅጣጫ አለው?” ሲሉ የጠየቁት የኢዴፓ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ጫኔ ከበደ በበኩላቸው፤ “ተቃዋሚዎች በምን መንገድ፣ የትኛውን የህብረተሰብ ክፍል ወክለው  ነው በፓርላማ ሊሣተፉ የሚችሉት” ብለዋል፡፡

“መንግስት ቅድሚያ መስጠት ያለበት ለህዝቡ ቀጥተኛ ጥያቄዎች መልስ መስጠት ላይ ነው” ያሉት ዶ/ር ጫኔ፤ “በአሁኑ ሰዓት ህዝብ ለተቃዋሚዎችም ለመንግስትም ፍላጎት ባላሳየበት ሁኔታ ተቃዋሚዎች በምን አግባብ ነው ፓርላማ ገብተው ሊነጋገሩ የሚችሉት” ሲሉ ጠይቀዋል፡፡  ኢዴፓ ተቃዋሚዎችን ፓርላማ አስገብቶ በመወያየት ብቻ ችግሮች ይቀረፋሉ የሚል እምነት እንደሌለው የጠቆሙት ፕሬዚዳንቱ፤ ፓርቲያቸው የፖሊሲ አቅጣጫዎች እንዲሻሻሉና ህግ ሙሉ ለሙሉ እንዲከበር እንደሚፈልግ ገልፀዋል፡፡

አቶ ናሁሠናይ በላይ
አቶ ናሁሠናይ በላይ

በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካ ሳይንስና የፌደራሊዝም መምህር አቶ ናሁሠናይ በላይ የፓርላማውን ውይይት በተመለከተ ተጠይቀው ሲመልሱ፤ በፓርላማው ለየት ያለ ሃሳብ እንዲንፀባረቅ መፈለጉ መልካምና ጠቃሚ መሆኑን ገልፀው፤ የተቃዋሚዎች ሚና የሚለካው ከገዥው ፓርቲ ጋር በመገናኘታቸው ብቻ አይደለም፤ ገዥው ፓርቲ በተቃዋሚዎች ሚና የሚያምን ከሆነ፣ እንደ ፖለቲካ ፓርቲ የሚንቀሣቀሱበትን የመጫወቻ ሜዳ ምቹ ማድረግ አለበት ብለዋል፡፡

“ኢህአዴግ የፖለቲካ ፓርቲዎች ገንቢ ሚና አላቸው ብሎ ማመን መጀመሩን ለማሳየት ከፈለገ፣ በፖለቲካ እንቅስቃሴያቸው ላይ እንቅፋት ከመሆን መቆጠብ ይኖርበታል፤ በአመት ሶስት ጊዜ ተቃዋሚዎችን በፓርላማ አሳትፋለሁ ማለት ብቻውን በቂ አይደለም፤ የተለያዩ መድረኮች መዘጋጀት አለባቸው” ያሉት ምሁሩ፤ “አሁን የሃገሪቱ ሁኔታ እንደ ቀድሞ የኔ ሃሳብ ብቻ  ይሰማ የሚባልበት ባለመሆኑ፣ ኢህአዴግ ከልቡ ተምሮ ከሆነ፣ ይህን ውጥኑን ተግባራዊ ሊያደርግ ይችላል” ሲሉ እምነታቸውን ገልፀዋል፡፡ (አዲስ አድማስ) (ፎቶ: DW እና Dassenech Tsemai)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Lusif says

    December 13, 2016 11:08 pm at 11:08 pm

    I guess the ruling party lacks sophistication. Who, in his right mind suggest such outright child’s game. Is that what Machivlae suggests when he said ” make you adversaries closer, so that you look benevolent and caring”. Has that been the intention, the ruling party need to understand it does not belong to the current century time frame. Safe exit the right strategy — durable peace and less costly.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule