• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሕወሃት ብጥብጥ እና ሽሽት- ከውስጥ አዋቂ ምንጭ

August 30, 2016 02:42 am by Editor 2 Comments

ሕዝባዊ አመጹ ያመጣውን ቀውስ ተከትሎ በህወሃት ከፍተኛ አመራር ውስጥ ከፍተኛ መበጣበጥ እና የርስ-በርስ ፍጥጫ መከሰቱን ከታመነ የውስጥ አዋቂ ምንጭ መረጃ  ደርሶናል። ­­­

“አመራሩ ክፉኛ ከመከፋፈሉ የተነሳም የርስበርሱ ችግራቸው ላይ ተወጥረዋል” ይላል መረጃው። ቀንደኞቹ የህወሃት አባላት ስርዓቱ እንዳበቃለት ስለተገነዘቡ ንብረት እና ልጆቻቸውን በማሸሽ ላይ ናቸው።

ሕዝቡ ሁሉ እንደተፋቸው በግልጽ እየነገራቸው ስለተገነዘቡ፤ የህወሃት የደህንነት አባላት ሕዝቡን ትተው የራሳቸውን ሰራዊት እና ፌደራል ፖሊስ አባላት እንዲሰልሉ ተነግሯቸዋል። “ተጠርጣሪ” የኦህዴድ እና ብአዴን አባላት በነዚህ ሰላዮች ስለተከበቡ በፍርሃት መወጠራቸውን ከራሳቸው አንደበት እየተሰማ ነው።

የርስበርስ ውጥረቱ የተከሰተው ወቅታዊ ችግሩን እንዴት እንፍታ በሚለው ሃሳብ ላይ ተቃዋሚ ፓርቲዎችን በሙሉ በመጥራት የአንድነት መንግስት እንመስርት በሚለው ሃሳብ ላይ ስምምነት ተወያይተው ውሳኔ ካስተላለፉ በኋላ በዚህ የተከፋው ቡድን  ባነሳው ተቃውሞ እንደሆነ መረጃው ጠቁሟል። ይህ ቡድን ችግሩን  በውይይት ሳይሆን በመሳሪያ ሃይል ለመፍታት ለብቻው መክሯል። ውይይታቸው ሁሉ ዛቻ እና ስድብ አዘል ንግግሮችም እንደነበሩበት ምንጫችን ጠቅሷል።

በውሳኔው መሰረት ተቃዋሚዎች በቤተመንግሥት ይጋበዛሉ ተብሏል። ለማዘናጋትም ተብሎ ይሁን ወይንም በፍርሃት የመጣው ይህ  ሃሳብ ግዜው አልፎበታል።

በሌላ በኩል ደግሞ ወታደራዊ ካምዮኖች የአጋዚ ወታደሮችን እና ከባድ መሳርያ ጭነው ከህወሃት ነጻ ወደ ወጡት ስፍራዎች እየጎረፉ ነው። ማብቅያ የሌላቸው እነዚህ የጭነት መኪናዎች እየተጓዙ ያሉት የውጭ ጠላትን ለመመከት ሳይሆን የገዛ ሕዝብን ለመደምሰስ ታቅዶ እና ታስቦ ነው። አለ የተባለው ሁሉ የህወሃት ሰራዊት ወደ አማራው ሕዝብ ተልኮ መንገድ ላይ ታግቷል። በአሁኑ ሰአት ሌላው አካባቢ ሰላማዊ ሰልፍ እንኳን ቢኖር ከአጋዚ ነጻ ይመስላል።

ሕዝባዊ አመጽ በተቀጣጠለባቸው ስፍራዎች (በተለይ በጎንደር እና ጎጃም) ያሉ የሰራዊት አባላት በሕዝቡ ላይ እንዲተኩሱ ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል ትእዛዝ አስተላልፎ ነበር። ችግር ግን አለ። ይህ ትዕዛዝ ከአካባቢው የሰራዊቱ አባላት ተቀባይነት አላገኘም። ልዩ ፖሊስ በመባል የሚታወቁት የአካባቢው ፖሊሶች እና  ወታደሮች ከህዝብ ጎን መቆምን መርጠዋል። በአካባቢው ያሉ የሰራዊቱ አባላት በህዝብ ላይ አንተኩስም ብለዋል። ይልቁንም ልዩ-ፖሊሶች ህዝብን ከአጋዚ ገዳዮች በመከላከል ላይ እንዳሉ ነው የሚሰማው።

በተለይ በጎንደር እና ጎጃም ሕዝቡ አስቀድሞ መንገዶችን በሙሉ ዘግቶ የአጋዚ ገዳዮች ወደ ስፍራው እንዳይገቡ አድርጓቸዋል። ይህ ባለመሳካቱም የኢትዮጵያ አየር መንገድ የውስጥ በረራውን አቁሞ የአጋዚ ሠራዊትን ወደ ባህርዳር እንዲያመላልስ ታዝዟል። በበርካታ ስፍራዎችም ሕዝቡ ራሱን ለመከላከል በመፋለም ላይ ይገኛል።

ሃይለማርያም ደሳለኝ በጠቅላይ ሚኒስትርነት ስልጣን ላይ ቁጭ ብሎ፤ በምክትሉ ነው የሚመራው። ለእያንዳንዱ የሚፈስ ደም፣ ለእያንዳንዱ የጦር ወንጀል፣ ለእያንዳንዱ በሰብአዊነት ላይ የሚፈጸም ወንጀል … የመጀመሪያ ጠያቂው እሱ መሆኑን ዘንግቶት ግን አይደለም።

ላለፉት 25 ዓመታት በጥቂቶች የተረገጠ ህዝብ ብሶቱ ከመብዛቱ የተነሳ ገንፍሎ ወጥቷል። (አብዛኛዎቹ) የጎንደር እና ጎጃም ክፍለ ሃገራት ከዘረኛው የህወሃት አገዛዝ ነጻ ወጥተዋል። በአንዳንድ ስፍራዎች ከፍተኛ የተኩስ ልውውጥ እየተካሄደ ቢሆንም ሁኔታው ለህወሃት እጅግ አስቸጋሪ እንደሆነበት ከስፍራው የሚደርሱን መረጃዎች ይጠቁማሉ።

በአዲስ አበባ እና በሌሎች ከተሞች ውጥረት እንደሰፈነ ነው። በሃገሪቱ የሚያስፈራ ድባብ ሰፍኗል። የኢኮኖሚው እንቅስቃሴ በእጅጉ እየተዳከመ ነው። የውሃ፣ የመብራት፣ የስልክ እና ኢንተርኔት መቋረጥ ህዝቡን እጅግ አስመርሮታል። አንድ ሊፈነዳ ያለ ነገር እንዳለ ይሰማል። ሕዝባዊ አመጽ በቀጠሮ አይመጣም። ብሶቱ መጨረሻ ደረጃ ላይ ሲደርስ ይፈነዳል።

የአዲስ አበባ ሕዝብ ለሰዓታት ከቤቱ ወጥቶ በሩ ላይ ብቻ ቢቆም፣  አሁን የሚደነፉበት ዘራፊዎች  ሁሉ ሃገር ለቀው ይጠፋሉ።


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. rasdejen says

    August 31, 2016 10:26 am at 10:26 am

    ጀግናዉ ዎሎ፤ጀግናዉ ሸዋ ሆይ፥፡

    የህወሃት ገዳይ ዎታደር አና ኣጋዜ ባንተ በኩል ኣድርጎ በጎጃምና በጎንድር ዎገኖችህን ሊጨፈጭፍ አየጎረፈ ነዉ። በምታዉቀዉ ጋራ፣ሸንተረር፣ሸለቆና መሿለኪያ አያጠመድክ መንገድ ላይ አንድታስቀረዉ በሰፊዉ ዎገንህ ስም ይህን ጥሪ ኣቀርብልሃለሁ። ተነስ የጀግንነትና ሰዉ ኣድን ታሪክ ኣሁን ስራ!!!! ተ….ነ…………ስ………….!!!!!!!!!!!!!!

    ጀግናዉ ጋየንት አና ጀግናዉ የፋርጣም ህዝብ ሾልኮ የሚሄደዉን ወገን ኣራጅ ሃይል እንድታስቀረዉ ጥብቅ ወገናዊ ጥሪ በወገን ስም ከአክብሮት ጋር ኣቀርባለሁ!!!!!!!!!!!!!

    እንዴ፤አትነሳም… እንዴ? https://www.youtube.com/watch?v=KmLwEgwBey8

    ለወገን ደራሽ ወገን ነዉ
    ይህ ጥሪ ከፍተኛ እድልም ነዉ፤ ኣጥብቀዉ እየተመኙ ያላገኙት በዙወች ነን
    እድልም ነዉና ኣይለፍችዉ፤ ኣይለፍሽ፤ኣይለፍህ!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!

    Reply
  2. Lusif says

    August 31, 2016 05:22 pm at 5:22 pm

    Obviously. Tyrany just doesn’t’t go away without futile and desperate last attempt. That is what we are seeing right now. The ruling party is on life support—– the military and security tube. Most staff members of the military are to busy with moving, hiding and transferring there looted wealth and properties. A lot of them do not seem fully engaged in defending the status quo, rather they seem looking a way out.
    Those who are financially well off are arguing for a peaceful transition and transfer of power so that the can enjoy the wealth they have already accumulated without raising any alarm.
    What I am trying to show is the ruling party is currently disorganized and in disarray. The situation is very fertile. The conditions are favorable for total change. What everybody needs to do is to come together, keep the momentum and increase the pressure stronger and stronger.
    I live in the country. I have lots of friends and business acquaintances. Every individual I know have become desperate. Each seems seeking information and help to know where all these end up, what the future would look like. And most of all most are worried how society would react towards them. Everybody is running to save the self and immediate family members.
    In general the ruling party is in its weakest links and shape. Time is precious. Let everybody utilize it wisely.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule