• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ

June 7, 2022 01:11 am by Editor 1 Comment

* ገና ከጅምሩ የመፈረካከስ አዝማሚያ እየታየባቸው ነው

በኢትዮጵያ ውስጥ በነጻ አውጪነትና በብሕር ድርጅትነት የሚታወቁ ሙሉ በሙሉ የተካተቱበት አዲስ የፓርቲዎች የምክክር ቤት (caucus) መቋቋሙ ተገለጸ። በስም ከተዘረዘሩት የምክክር ቤት አባል ድርጅቶች ውስጥ ከአፋር ሁለት፣ ከኦሮሚያ ሁለት፣ ከትግራይ አረና፣ የወላይታና የዶንጋ ሕዝቦች ይገኙበታል። በርካታዎቹ በምርጫ ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው ሲሆኑ በፓርቲ ደረጃ መድረክ ሲገኝ፣ በቅርቡ በተካሄደው ምርጫ አዲስ አበባ ላይ አንድ ድምጽ ያገኘው ሕብርም አለበት። ስብስቡ ገና ከጅምሩ የመፈረካከስ ሁኔታ እየታየበት እንደሆነ ተገለጸ።

መንግሥት ከትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባር (ትህነግ) ጋር ሙሉ ውጊያ ገብቶ በነበረበት ወቅት ጡንቻ ያበቀሉ ያላቸውን እያጸዳና የሕግ ማስከበር እያካሄደ ነው በሚባልበት ወቅት ላይ፣ በተለይም በኦሮሚያና አማራ ክልል ይቀሰቀሳል የተባለው ውጊያ እንዳይነሳ ተደርጎ አከርካሪው እየተሰበረ ባለበት ወቅት ይህ ኅብረት መመስረቱ በርካቶችን ከጅምሩ አወያይቷል።

ትህነግ የፌደራል ኃይሎች ሲል መሥርቶት ከነበረው ጥምረት ጋር በግልጽና በኅቡዕ ግንኙነት እንዳላቸው በስም ሲጠቀሱ የነበሩ ፓርቲዎችን ያካተተው የምክክር ቤት ትህነግን በስም አላካተተውም። ከኦሮሚያ ኦፌኮን ኦነግ አባላት ናቸው። የኦፌኮ ሥራ አስፈጻሚ የሆነው ጃዋር መሐመድ ይህንን የምምክር ቤት ዜና “ሰበር” ብሎ ከዘገበው ኡቡንቱ ጋር የመጀመሪያ ውይይት ሲያደርግ “ከማንም ጋር ለሰላም እሠራለሁ” ማለቱ ይታወሳል። ኅብረቱም ይፋ የሆነው ጃዋር ለፖለቲካ ሥራ ወደ ጀርመን ማቅናቱን ተከትሎ መሆኑም “ግጥምጥም” ወይስ በዕቅድ የተሠራ አስብሎታል። ከዚህ በፊት በትግራይ ትህነግ የፌዴራሊስት ኃይሎች ብሎ በሰበሰባቸው ወቅት ጃዋር እነ በቀለ ገርባን ልኮ እርሱ አዲስ አበባ ነበር የሰነበተው።   

ብልጽግና የአገራዊ የምክክር መድረኩ ፓርቲው በተመረጠበት የኮንትራት ዘመኑን አስመልክቶ የሚነጋገረው ነገር እንደሌለ ማስታወቁ አይዘነጋም። የምክክር ቤት የተባለው የአስር ፓርቲዎች ስብስብ ገና ከጅምሩ ያስቀመጣቸው ሃሳቦች ቀደም ሲል እነ ልደቱ “የሽግግር መንግሥት” ከሚሉት አካሄድ ጋር መዛመድ እንደሚታይበት ዜናውን ተከትሎ የወጡ መረጃዎች ይጠቁማሉ። መድረኩ ነጻ አውጪ ድርጅቶችን ሙሉ በሙሉ ካካተተ ለምን ትህነግን እና ኦነግ ሸኔን እንደዘለለ ግልጽ አለመሆኑም ተመልክቶበታል። ሆኖም ትህነግ በአረና፤ ሸኔም በኦነግ ተወክሏል የሚሉም አሉ። (Ethio 12)

እንደ ዑቡንቱ ዘገባ በሀገራዊ የምክክር መድረክ አካሄድ ላይ መሠረታዊ ቅሬታ አለን ያሉ 10 የሚደርሱ የተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች “እውነተኛ የዴሞክራሲ ስርዓትን የሚያስገኝ ሀገራዊ ውይይት አማራጭን ለማቅረብ የሚያስችል የምክክር ቤት (Caucus) አቋቁመናል” ሲሉ በዛሬው ዕለት ባወጡት መግለጫ አሳውቀዋል።

የምክክር ቤቱን የመሠረቱት ፓርቲዎችም
1- መድረክ
2- ህብር ኢትዮጵያ
3- የአፋር ህዝብ ፓርቲ
4- የአፋር ፍትህ እና ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ
5- የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ)
6- የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ
7-የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃነት ግንባር
8- የዎላይታ ብሄራዊ ንቅናቄ
9- ዓረና ትግራይ
10- የዶንጋ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት መሆናቸው ተገልጾዋል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ እንደዚህ ዓይነት ጥምረት ሲመሠረት የሥልጣን ጥያቄን ተከትሎ የሚያስነሳው ውዝግብ ኅብረቱ ሩቅ ሳይሄድ እንዲፈርስ የሚያደርገው መሆኑ እየተገለጸ ይገኛል። ከዚህ ሌላ አመራር፣ የበጀት አመዳደብ፣ ውክልና፣ በአሸባሪነት የተመዘገቡ ወንጀለኛ ድርጅቶች የመካተታቸው ጉዳይ፣ የአማራ ውክልና አለመኖር፣ ወዘተ ገና ከጅምሩ ኅብረቱ ርቀት ሳይሄድ ባጭር የሚያስቀሩት አቀንጭራዎች ሆነው ብቅ እያሉ ነው። በዚህ ጉዳይ ላይ በቀጣይ ያሳባሰብነው ይዘን እንቀርባለን።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Law, Left Column, Politics

Reader Interactions

Comments

  1. gi says

    June 7, 2022 05:16 am at 5:16 am

    የኣሳ ግማቱ ከጭንቅላቱ ነው። የፓርቲ ብዛት ለስልጣን ካለ ፍላጎትና ጥማት የሚመነጭ እንጂ ሌላ አዲስ ነገር ለሕዝብ ስላላቸው አይደለም። ለሕዝብማ መልካም ነገር ቢኖራቸው ሕዝብ በደገፋቸው በመረጣቸው ነበር። እንደ ኣሜሪካ ለመሆን ሲዳክሩ ሕዝብ ያላወቃቸው ለም ኣለኝ በሰማይ ናቸው። ኣለን ለማለት ከሆነ ይሞክሩት።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule