• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ

June 7, 2022 01:11 am by Editor 1 Comment

* ገና ከጅምሩ የመፈረካከስ አዝማሚያ እየታየባቸው ነው

በኢትዮጵያ ውስጥ በነጻ አውጪነትና በብሕር ድርጅትነት የሚታወቁ ሙሉ በሙሉ የተካተቱበት አዲስ የፓርቲዎች የምክክር ቤት (caucus) መቋቋሙ ተገለጸ። በስም ከተዘረዘሩት የምክክር ቤት አባል ድርጅቶች ውስጥ ከአፋር ሁለት፣ ከኦሮሚያ ሁለት፣ ከትግራይ አረና፣ የወላይታና የዶንጋ ሕዝቦች ይገኙበታል። በርካታዎቹ በምርጫ ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው ሲሆኑ በፓርቲ ደረጃ መድረክ ሲገኝ፣ በቅርቡ በተካሄደው ምርጫ አዲስ አበባ ላይ አንድ ድምጽ ያገኘው ሕብርም አለበት። ስብስቡ ገና ከጅምሩ የመፈረካከስ ሁኔታ እየታየበት እንደሆነ ተገለጸ።

መንግሥት ከትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባር (ትህነግ) ጋር ሙሉ ውጊያ ገብቶ በነበረበት ወቅት ጡንቻ ያበቀሉ ያላቸውን እያጸዳና የሕግ ማስከበር እያካሄደ ነው በሚባልበት ወቅት ላይ፣ በተለይም በኦሮሚያና አማራ ክልል ይቀሰቀሳል የተባለው ውጊያ እንዳይነሳ ተደርጎ አከርካሪው እየተሰበረ ባለበት ወቅት ይህ ኅብረት መመስረቱ በርካቶችን ከጅምሩ አወያይቷል።

ትህነግ የፌደራል ኃይሎች ሲል መሥርቶት ከነበረው ጥምረት ጋር በግልጽና በኅቡዕ ግንኙነት እንዳላቸው በስም ሲጠቀሱ የነበሩ ፓርቲዎችን ያካተተው የምክክር ቤት ትህነግን በስም አላካተተውም። ከኦሮሚያ ኦፌኮን ኦነግ አባላት ናቸው። የኦፌኮ ሥራ አስፈጻሚ የሆነው ጃዋር መሐመድ ይህንን የምምክር ቤት ዜና “ሰበር” ብሎ ከዘገበው ኡቡንቱ ጋር የመጀመሪያ ውይይት ሲያደርግ “ከማንም ጋር ለሰላም እሠራለሁ” ማለቱ ይታወሳል። ኅብረቱም ይፋ የሆነው ጃዋር ለፖለቲካ ሥራ ወደ ጀርመን ማቅናቱን ተከትሎ መሆኑም “ግጥምጥም” ወይስ በዕቅድ የተሠራ አስብሎታል። ከዚህ በፊት በትግራይ ትህነግ የፌዴራሊስት ኃይሎች ብሎ በሰበሰባቸው ወቅት ጃዋር እነ በቀለ ገርባን ልኮ እርሱ አዲስ አበባ ነበር የሰነበተው።   

ብልጽግና የአገራዊ የምክክር መድረኩ ፓርቲው በተመረጠበት የኮንትራት ዘመኑን አስመልክቶ የሚነጋገረው ነገር እንደሌለ ማስታወቁ አይዘነጋም። የምክክር ቤት የተባለው የአስር ፓርቲዎች ስብስብ ገና ከጅምሩ ያስቀመጣቸው ሃሳቦች ቀደም ሲል እነ ልደቱ “የሽግግር መንግሥት” ከሚሉት አካሄድ ጋር መዛመድ እንደሚታይበት ዜናውን ተከትሎ የወጡ መረጃዎች ይጠቁማሉ። መድረኩ ነጻ አውጪ ድርጅቶችን ሙሉ በሙሉ ካካተተ ለምን ትህነግን እና ኦነግ ሸኔን እንደዘለለ ግልጽ አለመሆኑም ተመልክቶበታል። ሆኖም ትህነግ በአረና፤ ሸኔም በኦነግ ተወክሏል የሚሉም አሉ። (Ethio 12)

እንደ ዑቡንቱ ዘገባ በሀገራዊ የምክክር መድረክ አካሄድ ላይ መሠረታዊ ቅሬታ አለን ያሉ 10 የሚደርሱ የተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች “እውነተኛ የዴሞክራሲ ስርዓትን የሚያስገኝ ሀገራዊ ውይይት አማራጭን ለማቅረብ የሚያስችል የምክክር ቤት (Caucus) አቋቁመናል” ሲሉ በዛሬው ዕለት ባወጡት መግለጫ አሳውቀዋል።

የምክክር ቤቱን የመሠረቱት ፓርቲዎችም
1- መድረክ
2- ህብር ኢትዮጵያ
3- የአፋር ህዝብ ፓርቲ
4- የአፋር ፍትህ እና ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ
5- የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ)
6- የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ
7-የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃነት ግንባር
8- የዎላይታ ብሄራዊ ንቅናቄ
9- ዓረና ትግራይ
10- የዶንጋ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት መሆናቸው ተገልጾዋል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ እንደዚህ ዓይነት ጥምረት ሲመሠረት የሥልጣን ጥያቄን ተከትሎ የሚያስነሳው ውዝግብ ኅብረቱ ሩቅ ሳይሄድ እንዲፈርስ የሚያደርገው መሆኑ እየተገለጸ ይገኛል። ከዚህ ሌላ አመራር፣ የበጀት አመዳደብ፣ ውክልና፣ በአሸባሪነት የተመዘገቡ ወንጀለኛ ድርጅቶች የመካተታቸው ጉዳይ፣ የአማራ ውክልና አለመኖር፣ ወዘተ ገና ከጅምሩ ኅብረቱ ርቀት ሳይሄድ ባጭር የሚያስቀሩት አቀንጭራዎች ሆነው ብቅ እያሉ ነው። በዚህ ጉዳይ ላይ በቀጣይ ያሳባሰብነው ይዘን እንቀርባለን።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Law, Left Column, Politics

Reader Interactions

Comments

  1. gi says

    June 7, 2022 05:16 am at 5:16 am

    የኣሳ ግማቱ ከጭንቅላቱ ነው። የፓርቲ ብዛት ለስልጣን ካለ ፍላጎትና ጥማት የሚመነጭ እንጂ ሌላ አዲስ ነገር ለሕዝብ ስላላቸው አይደለም። ለሕዝብማ መልካም ነገር ቢኖራቸው ሕዝብ በደገፋቸው በመረጣቸው ነበር። እንደ ኣሜሪካ ለመሆን ሲዳክሩ ሕዝብ ያላወቃቸው ለም ኣለኝ በሰማይ ናቸው። ኣለን ለማለት ከሆነ ይሞክሩት።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule