• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ

June 7, 2022 01:11 am by Editor 1 Comment

* ገና ከጅምሩ የመፈረካከስ አዝማሚያ እየታየባቸው ነው

በኢትዮጵያ ውስጥ በነጻ አውጪነትና በብሕር ድርጅትነት የሚታወቁ ሙሉ በሙሉ የተካተቱበት አዲስ የፓርቲዎች የምክክር ቤት (caucus) መቋቋሙ ተገለጸ። በስም ከተዘረዘሩት የምክክር ቤት አባል ድርጅቶች ውስጥ ከአፋር ሁለት፣ ከኦሮሚያ ሁለት፣ ከትግራይ አረና፣ የወላይታና የዶንጋ ሕዝቦች ይገኙበታል። በርካታዎቹ በምርጫ ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው ሲሆኑ በፓርቲ ደረጃ መድረክ ሲገኝ፣ በቅርቡ በተካሄደው ምርጫ አዲስ አበባ ላይ አንድ ድምጽ ያገኘው ሕብርም አለበት። ስብስቡ ገና ከጅምሩ የመፈረካከስ ሁኔታ እየታየበት እንደሆነ ተገለጸ።

መንግሥት ከትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባር (ትህነግ) ጋር ሙሉ ውጊያ ገብቶ በነበረበት ወቅት ጡንቻ ያበቀሉ ያላቸውን እያጸዳና የሕግ ማስከበር እያካሄደ ነው በሚባልበት ወቅት ላይ፣ በተለይም በኦሮሚያና አማራ ክልል ይቀሰቀሳል የተባለው ውጊያ እንዳይነሳ ተደርጎ አከርካሪው እየተሰበረ ባለበት ወቅት ይህ ኅብረት መመስረቱ በርካቶችን ከጅምሩ አወያይቷል።

ትህነግ የፌደራል ኃይሎች ሲል መሥርቶት ከነበረው ጥምረት ጋር በግልጽና በኅቡዕ ግንኙነት እንዳላቸው በስም ሲጠቀሱ የነበሩ ፓርቲዎችን ያካተተው የምክክር ቤት ትህነግን በስም አላካተተውም። ከኦሮሚያ ኦፌኮን ኦነግ አባላት ናቸው። የኦፌኮ ሥራ አስፈጻሚ የሆነው ጃዋር መሐመድ ይህንን የምምክር ቤት ዜና “ሰበር” ብሎ ከዘገበው ኡቡንቱ ጋር የመጀመሪያ ውይይት ሲያደርግ “ከማንም ጋር ለሰላም እሠራለሁ” ማለቱ ይታወሳል። ኅብረቱም ይፋ የሆነው ጃዋር ለፖለቲካ ሥራ ወደ ጀርመን ማቅናቱን ተከትሎ መሆኑም “ግጥምጥም” ወይስ በዕቅድ የተሠራ አስብሎታል። ከዚህ በፊት በትግራይ ትህነግ የፌዴራሊስት ኃይሎች ብሎ በሰበሰባቸው ወቅት ጃዋር እነ በቀለ ገርባን ልኮ እርሱ አዲስ አበባ ነበር የሰነበተው።   

ብልጽግና የአገራዊ የምክክር መድረኩ ፓርቲው በተመረጠበት የኮንትራት ዘመኑን አስመልክቶ የሚነጋገረው ነገር እንደሌለ ማስታወቁ አይዘነጋም። የምክክር ቤት የተባለው የአስር ፓርቲዎች ስብስብ ገና ከጅምሩ ያስቀመጣቸው ሃሳቦች ቀደም ሲል እነ ልደቱ “የሽግግር መንግሥት” ከሚሉት አካሄድ ጋር መዛመድ እንደሚታይበት ዜናውን ተከትሎ የወጡ መረጃዎች ይጠቁማሉ። መድረኩ ነጻ አውጪ ድርጅቶችን ሙሉ በሙሉ ካካተተ ለምን ትህነግን እና ኦነግ ሸኔን እንደዘለለ ግልጽ አለመሆኑም ተመልክቶበታል። ሆኖም ትህነግ በአረና፤ ሸኔም በኦነግ ተወክሏል የሚሉም አሉ። (Ethio 12)

እንደ ዑቡንቱ ዘገባ በሀገራዊ የምክክር መድረክ አካሄድ ላይ መሠረታዊ ቅሬታ አለን ያሉ 10 የሚደርሱ የተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች “እውነተኛ የዴሞክራሲ ስርዓትን የሚያስገኝ ሀገራዊ ውይይት አማራጭን ለማቅረብ የሚያስችል የምክክር ቤት (Caucus) አቋቁመናል” ሲሉ በዛሬው ዕለት ባወጡት መግለጫ አሳውቀዋል።

የምክክር ቤቱን የመሠረቱት ፓርቲዎችም
1- መድረክ
2- ህብር ኢትዮጵያ
3- የአፋር ህዝብ ፓርቲ
4- የአፋር ፍትህ እና ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ
5- የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ)
6- የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ
7-የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃነት ግንባር
8- የዎላይታ ብሄራዊ ንቅናቄ
9- ዓረና ትግራይ
10- የዶንጋ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት መሆናቸው ተገልጾዋል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ እንደዚህ ዓይነት ጥምረት ሲመሠረት የሥልጣን ጥያቄን ተከትሎ የሚያስነሳው ውዝግብ ኅብረቱ ሩቅ ሳይሄድ እንዲፈርስ የሚያደርገው መሆኑ እየተገለጸ ይገኛል። ከዚህ ሌላ አመራር፣ የበጀት አመዳደብ፣ ውክልና፣ በአሸባሪነት የተመዘገቡ ወንጀለኛ ድርጅቶች የመካተታቸው ጉዳይ፣ የአማራ ውክልና አለመኖር፣ ወዘተ ገና ከጅምሩ ኅብረቱ ርቀት ሳይሄድ ባጭር የሚያስቀሩት አቀንጭራዎች ሆነው ብቅ እያሉ ነው። በዚህ ጉዳይ ላይ በቀጣይ ያሳባሰብነው ይዘን እንቀርባለን።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Law, Left Column, Politics

Reader Interactions

Comments

  1. gi says

    June 7, 2022 05:16 am at 5:16 am

    የኣሳ ግማቱ ከጭንቅላቱ ነው። የፓርቲ ብዛት ለስልጣን ካለ ፍላጎትና ጥማት የሚመነጭ እንጂ ሌላ አዲስ ነገር ለሕዝብ ስላላቸው አይደለም። ለሕዝብማ መልካም ነገር ቢኖራቸው ሕዝብ በደገፋቸው በመረጣቸው ነበር። እንደ ኣሜሪካ ለመሆን ሲዳክሩ ሕዝብ ያላወቃቸው ለም ኣለኝ በሰማይ ናቸው። ኣለን ለማለት ከሆነ ይሞክሩት።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule