• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የእነ ለማ ጉዳይ ወደ ሕግ ሊያመራ ይችላል ተባለ

August 13, 2020 08:05 am by Editor Leave a Comment

ሰሞኑን ከኃላፊነታቸው መታገዳቸው የተሰማው የኦሮሚያ ከፍተኛ አመራሮች አቶ ለማ መገርሣ፥ ወ/ሮ ጠይባና ሜልኬሣ ሚደጋ ከፌዴሬሽን ምክርቤት አባልነታቸውም ተነስተዋል ተብሎ በሥፋት ሲናፈስ ነበር። ሆኖም ዜናው ሐሰት ነው ተብሎ ማስተባበያም ተሰጥቶበታል።

ጎልጉል ከወደ አዲስ አበባ ያሰባሰበው መረጃ እንደሚጠቁመው በቀጣይ ግለሰቦቹ ጉዳያቸው ወደ ሕግ የሚሄድበት መንገድ እየተመቻቸ ያለ ይመስላል። በተለይ ወ/ሮ ጠይባ ሻሸመኔ ከንቲባ በነበሩበት ጊዜ በከተማዋ ለተፈጸሙ ዘግናኝ ግፎች ተጠያቂ የሚሆኑበት ሁኔታ አለ የሚለው ገዝፎ እየወጣ ነው። እንደሚታወቀው ወ/ሮ ጠይባ ከንቲባ በነበሩበት ጊዜ በሻሸመኔ ከተማ እጅግ ዘግናኝ የሆነው ግድያ ያውም ገድሎ ዘቅዝቆ የመስቀልና የማቃጠል አሰቃቂ ወንጀል ተፈጽሟል።

የብልጽግና ኦሮሚያ ቅርንጫፍ አመራሮችም ጉዳዩን በግልጽ ባይናገሩትም የጠይባን በሕግ የመጠየቅ ሁኔታ በተደጋጋሚ ሲያስተጋቡ እንደነበር ሰሞኑን በሰጡት ቃለመጠይቆች ተሰምተዋል።

ሚልኬሣ ሚደጋም (ዶ/ር) እንዲሁ ከፓርቲው አሠራር ውጪ መልዕክቶችን በማሰማትና ጸንፈኛ አካሄድ በመከተል የፈጸሙት ከሕግ አንጻር የሚታይበት ሁኔታ ሊኖር እንደሚችል ጥቆማዎች አሉ።

አቶ ለማ ወያኔን በማስወገድ ትግል የፈጸሟቸው ተግባራትና የሰጡት አመራር እንደ ውለታ ተቆጥሮ በሕግ የመጠየቃቸው ጉዳይ ወደጎን ሊደረግ ይችላል የሚሉ ግምቶች አሉ። ከዚህ በተጨማሪም በኦሮሞ ውስጥ መከፋፈል ላለመፍጠርና ውጥረቶችን ለማርገብ አቶ ለማ በገዛ ፈቃዳቸው ከመከላከያ ሚ/ር ሥልጣናቸው እንዲነሱ እንደሚደረግ አንዳንድ መረጃዎች ይጠቁማሉ።

የሪፖርተሩ ዮሐንስ አንበርብር “የመከላከያ ሚኒስትሩ ከፌዴሬሽን ምክር ቤት አባልነታቸው መነሳታቸው ታወቀ” በሚል ርዕስ የዘገበው ከዚህ በታች ይነበባል።

የኦሮሚያ ክልልን በመወከል የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባል የነበሩት የመከላከያ ሚኒስትሩ አቶ ለማ መገርሳ ከአባልነታቸው መነሳታቸው ተጠቆመ። ሰሞኑን ደግሞ ከኦሮሚያ የብልፅግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነታቸው መታገዳቸው ተሰምቷል።

ከአቶ ለማ በተጨማሪ ሌሎች ሁለት አመራሮችም ከፌዴሬሽን ምክር ቤት አባልነታቸው መነሳታቸውን ሪፖርተር ያገኘው መረጃ አመልክቷል። 

ክልሉን በመወከል የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባል የነበሩት አቶ ለማ መገርሳ እና ሌሎቹ ሁለት አባላት ከፌዴሬሽን ምክር ቤት አባልነት እንዲነሱ የተወሰነው ጨፌ ኦሮሚያ ከሁለት ሳምንት በፊት ባካሄደው ስብሰባ ላይ እንደሆነም የሪፖርተር መረጃ ያመለክታል። 

አቶ ለማን ጨምሮ ሦስቱ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባላት በተለያዩ ምክንያቶች ተጓድለዋል በሚል ምክንያት ጨፌው ሌሎች አባላትን በመምረጥ እንዲተኩ ማደረጉን መረጃዎቹ አመልክተዋል።

ጨፌው በአቶ ለማ እና በሌሎቹ ሁለት አባላት ምትክ አዲስ አባላትን መርጦ ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ያስታወቀ ሲሆን፣ አቶ ለማን ተክተው የተመረጡትም በአሁኑ ወቅት የብልጽግና ፓርቲ ኦሮሚያ ቅርንጫፍ ኃላፊ እና በጨፌ ኦሮሚያ የክልሉ መንግሥት ተጠሪ ሆነው እያገለገሉ የሚገኙት አቶ ፍቃዱ ተሰማ ናቸው።

በሌሎቹ ሁለት አባላት ምትክ ደግሞ የክልሉ ፓርቲ አደረጃጀት የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሳዳት ነሻና አቶ አብዱል ሐኪም መመረጣቸው ታውቋል። የአገሪቱ የመከላከያ ሚኒስትር የሆኑት አቶ ለማ ሰሞኑን በተካሄደ የፓርቲ ስብሰባ ከኦሮሚያ ብልፅግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነታቸው መታገዳቸውም ይፋ ሆኗል።

የኦሮሚያ ብልፅግና ፓርቲ በአዲስ አበባ በጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤት አዳራሽ ለሁለት ቀናት ያካሄደውን ስብስባ ነሐሴ 3 ቀን 2012 ዓ.ም. አጠናቆ ባወጣው መግለጫ፣ አቶ ለማን ጨምሮ ሦስቱ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ላልተወሰነ ጊዜ መታገዳቸውን አስታውቋል።

የኦሮሚያ ብልፅግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፍቃዱ ለሁለት ቀናት የተካሄደውን ስብሰባና ውሳኔዎቹን አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ፣ ስብሰባው በፓርቲው ክልላዊ መዋቅር ላይ የተስተዋሉ ድክመቶች ላይ በስፋት ተወያይቶ የመፍትሔ አቅጣጫዎችን የተመለከቱ ውሳኔዎችን እንዳሳለፈ ገልጸዋል።

በፓርቲው የክልል መዋቅር ከፍተኛ አመራሮች ላይ ባደረገው ግምገማም በማዕከላዊ አባልነት ሲያገለግሉ የነበሩት የመከላከያ ሚኒስትሩ አቶ ለማ፣ ወ/ሮ ጠይባና ሚልኬሳ (ዶ/ር) ላልተወሰነ ጊዜ ከማዕከላዊ አባልነታቸው እንዲታገዱ መወሰኑን አስታውቀዋል።

አቶ ለማ መገርሳ ከማዕከላዊ አባልነታቸው እንዲታገዱ ምክንያት ከሆኑት ጉዳዮች መካከል አንዱ፣ በፓርቲው የሥራ አስፈጻሚ ስብሰባዎች ላይ በተደጋጋሚ አለመገኘታቸው መሆኑን አመልክተዋል።

በተጨማሪም የመከላከያ ሚኒስትር ከመሆናቸው ጋር ተያይዞ በተጣሉባቸው መንግሥታዊ ኃላፊነቶች ላይም በተደጋጋሚ አለመገኘታቸውን አቶ ፍቃዱ በምክንያትነት አንስተዋል።

አቶ ለማ የአገር መከላከያ ሚኒስትርን በመወከል የፌዴራሉ መንግሥት የሚኒስትሮች ምክር ቤት አባል መሆናቸው የሚታወቅ ሲሆን፣ በምክር ቤቱ ስብሰባዎች ሲሳተፉ አይስተዋሉም። አቶ ለማ ላይ ሌላው የቀረበው የዲሲፕሊን ጥሰት አባል በሆኑበት የጨፌ ኦሮሚያ ምክር ቤት ስብሰባ ላይም በተደጋጋሚ አለመሳተፋቸውና ለሁለት ቀናት በተካሄደው የፓርቲው ስብሰባ ላይ እንዲገኙ ተደጋጋሚ ጥሪ ተደርጎላቸው አለመገኘታቸውን ገልጸዋል። በመሆኑም አቶ ለማ ከማዕከላዊ አባልነታቸው ታግደው እንዲቆዩ የኦሮሚያ ብልፅግና ፓርቲ ባካሄደው ስብሰባ በሙሉ ድምፅ መወሰኑን አስረድተዋል።

ወ/ሮ ጠይባም ኦሮሚያ ክልል ውስጥ በተለያዩ ጊዜያት በነበሩ ግጭቶች ጋር በተገናኘ ስማቸው ሲነሳ መቆየቱ ጠቁመው፣ ከፍተኛ አመራሩና አባሉም አመኔታ በማጣቱ ጥያቄ ያነሳ ስለነበር ጉዳያቸው እስከሚጣራ ድረስ ከማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነታቸው እንዲታገዱ መደረጉን ገልጸዋል።

ሚልኬሳ (ዶ/ር) ከፓርቲው ሥነ ምግባር ባፈነገጠ መልኩ በውስጥ ማድረግ የሚገባን ትግል ወደ ውጭ በማውጣትና መገኘት በሚገባቸው ስብሰባዎች ላይ ሊገኙ ባለመቻላቸው እንዲሁም የፓርቲውን ሚስጥር በተለያዩ መድረኮች በማውጣታቸው ታግደው እንዲቆዩ መወሰኑን ገልጸዋል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: lemma megerssa, milkessa, tayiba

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule