• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የእነ ለማ ጉዳይ ወደ ሕግ ሊያመራ ይችላል ተባለ

August 13, 2020 08:05 am by Editor Leave a Comment

ሰሞኑን ከኃላፊነታቸው መታገዳቸው የተሰማው የኦሮሚያ ከፍተኛ አመራሮች አቶ ለማ መገርሣ፥ ወ/ሮ ጠይባና ሜልኬሣ ሚደጋ ከፌዴሬሽን ምክርቤት አባልነታቸውም ተነስተዋል ተብሎ በሥፋት ሲናፈስ ነበር። ሆኖም ዜናው ሐሰት ነው ተብሎ ማስተባበያም ተሰጥቶበታል።

ጎልጉል ከወደ አዲስ አበባ ያሰባሰበው መረጃ እንደሚጠቁመው በቀጣይ ግለሰቦቹ ጉዳያቸው ወደ ሕግ የሚሄድበት መንገድ እየተመቻቸ ያለ ይመስላል። በተለይ ወ/ሮ ጠይባ ሻሸመኔ ከንቲባ በነበሩበት ጊዜ በከተማዋ ለተፈጸሙ ዘግናኝ ግፎች ተጠያቂ የሚሆኑበት ሁኔታ አለ የሚለው ገዝፎ እየወጣ ነው። እንደሚታወቀው ወ/ሮ ጠይባ ከንቲባ በነበሩበት ጊዜ በሻሸመኔ ከተማ እጅግ ዘግናኝ የሆነው ግድያ ያውም ገድሎ ዘቅዝቆ የመስቀልና የማቃጠል አሰቃቂ ወንጀል ተፈጽሟል።

የብልጽግና ኦሮሚያ ቅርንጫፍ አመራሮችም ጉዳዩን በግልጽ ባይናገሩትም የጠይባን በሕግ የመጠየቅ ሁኔታ በተደጋጋሚ ሲያስተጋቡ እንደነበር ሰሞኑን በሰጡት ቃለመጠይቆች ተሰምተዋል።

ሚልኬሣ ሚደጋም (ዶ/ር) እንዲሁ ከፓርቲው አሠራር ውጪ መልዕክቶችን በማሰማትና ጸንፈኛ አካሄድ በመከተል የፈጸሙት ከሕግ አንጻር የሚታይበት ሁኔታ ሊኖር እንደሚችል ጥቆማዎች አሉ።

አቶ ለማ ወያኔን በማስወገድ ትግል የፈጸሟቸው ተግባራትና የሰጡት አመራር እንደ ውለታ ተቆጥሮ በሕግ የመጠየቃቸው ጉዳይ ወደጎን ሊደረግ ይችላል የሚሉ ግምቶች አሉ። ከዚህ በተጨማሪም በኦሮሞ ውስጥ መከፋፈል ላለመፍጠርና ውጥረቶችን ለማርገብ አቶ ለማ በገዛ ፈቃዳቸው ከመከላከያ ሚ/ር ሥልጣናቸው እንዲነሱ እንደሚደረግ አንዳንድ መረጃዎች ይጠቁማሉ።

የሪፖርተሩ ዮሐንስ አንበርብር “የመከላከያ ሚኒስትሩ ከፌዴሬሽን ምክር ቤት አባልነታቸው መነሳታቸው ታወቀ” በሚል ርዕስ የዘገበው ከዚህ በታች ይነበባል።

የኦሮሚያ ክልልን በመወከል የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባል የነበሩት የመከላከያ ሚኒስትሩ አቶ ለማ መገርሳ ከአባልነታቸው መነሳታቸው ተጠቆመ። ሰሞኑን ደግሞ ከኦሮሚያ የብልፅግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነታቸው መታገዳቸው ተሰምቷል።

ከአቶ ለማ በተጨማሪ ሌሎች ሁለት አመራሮችም ከፌዴሬሽን ምክር ቤት አባልነታቸው መነሳታቸውን ሪፖርተር ያገኘው መረጃ አመልክቷል። 

ክልሉን በመወከል የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባል የነበሩት አቶ ለማ መገርሳ እና ሌሎቹ ሁለት አባላት ከፌዴሬሽን ምክር ቤት አባልነት እንዲነሱ የተወሰነው ጨፌ ኦሮሚያ ከሁለት ሳምንት በፊት ባካሄደው ስብሰባ ላይ እንደሆነም የሪፖርተር መረጃ ያመለክታል። 

አቶ ለማን ጨምሮ ሦስቱ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባላት በተለያዩ ምክንያቶች ተጓድለዋል በሚል ምክንያት ጨፌው ሌሎች አባላትን በመምረጥ እንዲተኩ ማደረጉን መረጃዎቹ አመልክተዋል።

ጨፌው በአቶ ለማ እና በሌሎቹ ሁለት አባላት ምትክ አዲስ አባላትን መርጦ ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ያስታወቀ ሲሆን፣ አቶ ለማን ተክተው የተመረጡትም በአሁኑ ወቅት የብልጽግና ፓርቲ ኦሮሚያ ቅርንጫፍ ኃላፊ እና በጨፌ ኦሮሚያ የክልሉ መንግሥት ተጠሪ ሆነው እያገለገሉ የሚገኙት አቶ ፍቃዱ ተሰማ ናቸው።

በሌሎቹ ሁለት አባላት ምትክ ደግሞ የክልሉ ፓርቲ አደረጃጀት የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሳዳት ነሻና አቶ አብዱል ሐኪም መመረጣቸው ታውቋል። የአገሪቱ የመከላከያ ሚኒስትር የሆኑት አቶ ለማ ሰሞኑን በተካሄደ የፓርቲ ስብሰባ ከኦሮሚያ ብልፅግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነታቸው መታገዳቸውም ይፋ ሆኗል።

የኦሮሚያ ብልፅግና ፓርቲ በአዲስ አበባ በጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤት አዳራሽ ለሁለት ቀናት ያካሄደውን ስብስባ ነሐሴ 3 ቀን 2012 ዓ.ም. አጠናቆ ባወጣው መግለጫ፣ አቶ ለማን ጨምሮ ሦስቱ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ላልተወሰነ ጊዜ መታገዳቸውን አስታውቋል።

የኦሮሚያ ብልፅግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፍቃዱ ለሁለት ቀናት የተካሄደውን ስብሰባና ውሳኔዎቹን አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ፣ ስብሰባው በፓርቲው ክልላዊ መዋቅር ላይ የተስተዋሉ ድክመቶች ላይ በስፋት ተወያይቶ የመፍትሔ አቅጣጫዎችን የተመለከቱ ውሳኔዎችን እንዳሳለፈ ገልጸዋል።

በፓርቲው የክልል መዋቅር ከፍተኛ አመራሮች ላይ ባደረገው ግምገማም በማዕከላዊ አባልነት ሲያገለግሉ የነበሩት የመከላከያ ሚኒስትሩ አቶ ለማ፣ ወ/ሮ ጠይባና ሚልኬሳ (ዶ/ር) ላልተወሰነ ጊዜ ከማዕከላዊ አባልነታቸው እንዲታገዱ መወሰኑን አስታውቀዋል።

አቶ ለማ መገርሳ ከማዕከላዊ አባልነታቸው እንዲታገዱ ምክንያት ከሆኑት ጉዳዮች መካከል አንዱ፣ በፓርቲው የሥራ አስፈጻሚ ስብሰባዎች ላይ በተደጋጋሚ አለመገኘታቸው መሆኑን አመልክተዋል።

በተጨማሪም የመከላከያ ሚኒስትር ከመሆናቸው ጋር ተያይዞ በተጣሉባቸው መንግሥታዊ ኃላፊነቶች ላይም በተደጋጋሚ አለመገኘታቸውን አቶ ፍቃዱ በምክንያትነት አንስተዋል።

አቶ ለማ የአገር መከላከያ ሚኒስትርን በመወከል የፌዴራሉ መንግሥት የሚኒስትሮች ምክር ቤት አባል መሆናቸው የሚታወቅ ሲሆን፣ በምክር ቤቱ ስብሰባዎች ሲሳተፉ አይስተዋሉም። አቶ ለማ ላይ ሌላው የቀረበው የዲሲፕሊን ጥሰት አባል በሆኑበት የጨፌ ኦሮሚያ ምክር ቤት ስብሰባ ላይም በተደጋጋሚ አለመሳተፋቸውና ለሁለት ቀናት በተካሄደው የፓርቲው ስብሰባ ላይ እንዲገኙ ተደጋጋሚ ጥሪ ተደርጎላቸው አለመገኘታቸውን ገልጸዋል። በመሆኑም አቶ ለማ ከማዕከላዊ አባልነታቸው ታግደው እንዲቆዩ የኦሮሚያ ብልፅግና ፓርቲ ባካሄደው ስብሰባ በሙሉ ድምፅ መወሰኑን አስረድተዋል።

ወ/ሮ ጠይባም ኦሮሚያ ክልል ውስጥ በተለያዩ ጊዜያት በነበሩ ግጭቶች ጋር በተገናኘ ስማቸው ሲነሳ መቆየቱ ጠቁመው፣ ከፍተኛ አመራሩና አባሉም አመኔታ በማጣቱ ጥያቄ ያነሳ ስለነበር ጉዳያቸው እስከሚጣራ ድረስ ከማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነታቸው እንዲታገዱ መደረጉን ገልጸዋል።

ሚልኬሳ (ዶ/ር) ከፓርቲው ሥነ ምግባር ባፈነገጠ መልኩ በውስጥ ማድረግ የሚገባን ትግል ወደ ውጭ በማውጣትና መገኘት በሚገባቸው ስብሰባዎች ላይ ሊገኙ ባለመቻላቸው እንዲሁም የፓርቲውን ሚስጥር በተለያዩ መድረኮች በማውጣታቸው ታግደው እንዲቆዩ መወሰኑን ገልጸዋል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: lemma megerssa, milkessa, tayiba

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule