• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ካሚል ሸምሱ እውነት ነጻ ያወጣችው ጀግና

September 20, 2016 11:35 pm by Editor Leave a Comment

እውነትን መናገር ለራስ ነው የሚያምኑበትን ሳይናገሩ ከመኖር ይሰውረን!!!

ከአንድ አመት በፊት ልክ በዛሬዋ እለት ስለ ኡስታዝ ካሚል ሸምሱ የማውቀውን ከመቀሌ ዩኒቨርሲቲ እስከ ቂሊንጦ በሚል ርእስ አንዲት ጽሁፍ ጀባ ብዬ ነበር፤ ዛሬ ደግሞ እነ ካሚል ሸምሱ ከቂሊንጦ ቃሊቲ ከዛም ወደ ቤተሰብ ተቀላቅለዋል፤ ደስ የሚያሰኝ ዜና ነው፡፡

በርካታ ጓደኞቼን ስለ ካሚል ሳጫውታቸው በቅድሚያ ግራና ቀኛቸውን ይመለታሉ፣ ይቀጥሉና አንገታቸውን እስቲሰበር ድረስ ወደ ኋላቸው ገልመጥ ይላሉ፣ ይቀጥሉና የአግአዚ ስናይፐር እንዳይመታቸው ይመስል ወይንም ነፍሴን አደራ በሰማይ በሚመስል መልኩ ሽቅብ ያንጋጥጣሉ፣ በመጨረሻም ራሴውኑ በጥርጣሬ አይን ይመለከቱና ስለ ካሚል ሸምሱ ያላቸውን አስተያየት በሹክሹክታ ይነግሩኛል፡፡

ብሽቅ ብዬ ትቻቸው ልሄድ ስልም ምክንያታቸውን ይገልጹልኛል፣ ‹ምን ነካህ አብረውን የተማሩት እነ እከሌ እከሊት እኮ የማእከላዊ ባልደረባ ሆነዋል፣ እነ እንትና እኮ የደህንነቱን መስሪያ ቤት ከሚያሾሩት ውስጥ ይመደባሉ፣ በዛ ላይ ደግሞ ባለትዳርና የልጆች አባት ነኝ› ሲሉ ይደመጣሉ፤ እንዲህ አካባቢያቸውን በአይነ ቁራኛነት ሲከታተሉ ሳይ አዝኜላቸዋለው፤ በአንጻሩ ደግሞ ለመብቱ መከበር ሲል ዋጋ የከፈለውንና ድል ያደረገውን ካሚል ሸምሱን ሳስብ ሀገራችን ሰው እንዳላጣች ማረጋገጫ ይሆነኝና እጽናናለው፡፡

ወዳጄ ኡስታዝ ካሚል ሸምሱ የነጻነት ምልክት ሆነሀልና እንኳን ደስ አለህ! ከምትወዳቸው ቤተሰቦችህ ለመቀላቀል እንኳን አበቃህ፤ ከባለቤትህ ጋር ምን ያህል እንደምትዋደዱ አውቃለው፤ ካምፓስ እያለን ባለቤትህ ውጭ አገር ሆና ስትደውልልህ ‹ተራርቀን እስከመቼ?› ተባብላቹሁ የተላቀሳችሁበትን ጊዜ አስታውሳለው፤ ባለቤትህም እንኳን ከልደታ-ቂሊንጦ-ቃሊቲ ከመመላለስ አረፈች፤ አላህ እንኳን አንድ አደረጋችሁ!!!

በነገራችን ላይ ከሙስሊም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች መካከል በቀዳማይ ሚኒስትራችን አይተ መለስ ዜናዊ ጥርስ የገባ ሰው ቢኖር ካሚል ሸምሱ ነበር፤ ይህንንም በአፍ ወለምታ የምናገረው ሳይሆን በማስረጃ ነው፤ ካሚል ሸምሱ በተለያየ ጊዜ ለሙስሊሙ ህብረተሰብ መፍትሄ ለማፈላለግ ባደረገው ጥረት በርካታ ስብሰባዎችን መርቷል፤ ታዋቂው ደራሲ አሌክስ አብርሀም ካሚል በሻሸመኔ ከተማ ተገኝቶ ህገ መንግስቱን የተመረኮዘ ማብራሪያ ሲተረጉም የሚያሳይ ምስል በመጽሀፈ ገፁ ለጥፎ ተመልክተናል፡፡

ካሚል ሸምሱ በተደጋጋሚ የሚናገረው አንድ ኃይለ ቃልም ነበር፣ ‹መንግሥት እኛን ወንጀለኛ ብሎ ለማሰር ማስረጃ ሳይሆን መረጃ የለውም› የምትል ነበር፤ የሰዎችን ሀሳብ የራሳቸው እንደሆነ አድርገው ማቅረብ የሚቀናቸው አይተ መለስ ዜናዊ ፓርላማ ላይ እንደ ጎበዝ ተማሪ ከፊት ወንበር ላይ ተሰይመው፤ ‹ኮሚቴዎቹን ለማሰር ማስረጃ መረጃም አለን› ሲሉ ተናገሩ፤ የካሚል ሸምሱ አነጋገር እንቅልፍ ነስቷቸው እንደነበር ራሳቸውን በራሳቸው አጋለጡ፡፡

ጥርስ ውስጥ የገባው ካሚል ሸምሱ ፌዴራል ፓሊስ፣ የደህንነት መስሪያ ቤቱ፣ ኢቲቪ፣ ማእከላዊ፣ ቂሊኒጦና ቃሊቲን የመሳሰሉ የመንግሰት ተቋማት ተባብረው አብጠርጥሮ የሚያውቀውን ሰብአዊ መብት አንድ ሁለት … እያሉ አራቆቱት፡፡ አሸባሪ ነህ ሲሉም ሮቦት ዳኞች ፈረዱበት፤ ከወህኒም ጨመሩት፤ ጊዜ ለኩሉ እንዲል ጠቢቡ ከፍርግርጉ ጀርባ የነበረውን ካሚል ሸምሱ እውነት ነጻ አወጣችው፤ ምናልባትም አንዳንድ የዋሆች ይህንን የህወኃት ድርጊት ‹ምህረት› ብለው ይጠሩት ይሆናል፡፡

አትሳሳቱ ! ኮሚቴዎቻችን የታሰሩት፣ የተሰቃዩትና የተፈረደበቸወ ጥፋተኞች ሆነው እንዳልሆነ ራሱ ወያኔ አሳምሮ ያውቀዋል፤ እነ ካሚል ሸምሱን ነጻ ያወጣቸውም እውነትን ይዘው እስከ መጨረሻው በመጓዛቸው ነው፤ መሀሪ የሚባል የወያኔ አባል ሊኖር ይችላል፤ ወያኔ ግን መሀሪ አይደለም፡፡

(besufekadreje@gmail.com)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule