• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ዘረኛ ፋሺስቶችን ለፍርድ እናቅርብ

July 3, 2020 09:12 am by Editor 4 Comments

የፋሽስታዊው አመለካከት ያላቸው (ethno-fascists) የጸጋዬ አራርሳ፣ የህዝቄል ገቢሳ፣ መሰሎቻቸው፣ እንዲሁም የትግራይ ሚዲያ ሀውስ መርዘኛ፡ ሃሰተኛ ቅስቀሳዎችና ትርክቶች የብሄር ለብሄር፣ የዘር ፍጅት (ጄኖሳይድ) ከማድረሳቸው በፊት በአለም ዙሪያ የሚገኙ ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ሁሉ በጋራ ሆነው የተደራጀ፣ የተቀናጀ፣ የተናበበ ስራ መስራት ይገባል። ባልተናበበና በተበታተነ ሁኔታና እንቅስቃሴ ውጤት ለማምጣት እጅግ አዳጋች ይሆናል፣ ሁሉም ባለው መሰለፍ ይገባል፣ የመጣውን ኣደጋ ለመከላከል እንደ ኢትዮጵያውያን ዜጎች በጋራ መቆም የግድ ነው። የፖለቲካ አመለካከት ወደ ጎን አድርጎ በአንድ ላይ፣ በጋራ መቆም ወሳኝ ይመስለኛል።

የሁላችንም ሀገር የሆነችው ቤተሰብ፣ ዘመድ፣ አዝማዶች፣ ወገኖችና፣ ባጠቃላይም ህዝባችን የሚኖርባት ሀገረ ኢትዮጵያ ውስጥ እየሆነ ያለው ሁኔታ ፍጹም ወደ አለተጠበቀ እጅግ አውዳሚ ሂደት ሊሸጋገር ይችላል። ለዚህ አደገኛ ሂደት ደግሞ በደምብ በተጠና፣ በተቀናጀ መልክ ቤንዚን የሚያርከፈክፉትን እነዚህ ፋሽስታዊ የኦሮሞ ጽንፈኞች፣ እንዲሁም ያጣውን ስልጣን ዳግም ለመፈናጠጥ ካልቻለ ኢትዮጵያን ለማተራመስ በሙሉ አቅሙ 24 ሰአት አየሰራ የሚገኘው የአሸባሪው የህወሃት ልሳን የሆነው የትግራይ ሚዲያ ሃውስ ናቸው።

በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የህግ ባለሙያዎችም ይህን እጅግ አደገኛ ሂደት በህግ እንዲታይና የህግ መሣሪያዎችን (Legal instruments) መፈተሽና መጠቀም ይገባቸዋል። የተቀነባበረ፣ የተደራጀ ስራ መስራት፣ በኢትዮጵያ ሀገራችን እንዲሁም በመላው ህዝባችን ላይ የተጋረጠውን ከባድ ሰላም አደፍራሽ፣ ህዝብ ለህዝብ አጫራሽ፣ ሀገርንም ሊበትን የሚችል አደጋ ለመከላከል በጋራ መንቀሳቀስ፣ መናበብና፣ ተጽእኖ በሚፈጥር ሁኔታ መመከት፣ ማጋለጥ፣ በህግም እንዲጠየቁ ለማድረግ መንቀሳቀስ የሚገባው ጊዜው አሁን ነው።
ነአምን ዘለቀ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, Opinions Tagged With: alula solomon, ezikiel gebissa, omn, tigrai media house, tmh, tsegaye ararsa

Reader Interactions

Comments

  1. Zewdu says

    July 3, 2020 09:44 pm at 9:44 pm

    Well this better reporting
    However, the posting on Ethio 360 by the Editor is based on here say fictional propaganda not based on fact .if based on fact I am the first to demand The accused be removed::: please stop posting without a a source. You are insulting our intelligence
    Make a correction . I hope you do
    Ps
    I am one of your followers including a a group I admire
    Thanks

    Reply
  2. ነፃ ሕዝብ says

    July 4, 2020 12:35 am at 12:35 am

    በነገራችን ላይ እኔም የአቶ ነዓምን ዘለቀን ሃሳብ እጋራለሁ ፥ እነዚህ ሰዎች ኢትዮጵያን ለማፍረስ ቆርጠው የተነሱና ለረጅም ጊዜ ሕዝብን ከሕዝብ ለማጫረስ ቀን ከሌት ሳይታክቱ የሚሰሩ ዕኩይ ተልዕኮ ያላቸው ጸረ-ኢትዮጵያ ናቸው ፥ በያሉበት ሀገር በሕግ ቁጥጥር ሥር ውለው አስፈላስጊውን ሕጋዊ እርምጃ ሊወሰድባቸው ይገባል ፥ ለዚህ ደግሞ ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያኖች በተለይ በውጭ ሀገር የምንገኝ ከሕግ ባለሙያዎች ጋር በመቀናጀት አስፈላጊውን የማቴሪያልና ሌሎችንም ድጋፍ በማድረግ በተቀናጀ መልኩ ሀገራችንን ከማፍረሳቸው አስቀድሞ እነርሱን ማፍረስ ያስፈልጋል ።

    Reply
  3. Nahusenay Metaferia says

    July 5, 2020 08:10 am at 8:10 am

    360 የኢትዮጵያዊነት ጠበቃ እውነቱን ፍርጥ አድርገው ይሚናገሩ ሐሰተኞችና ሌቦች አይወዷቸውም።ወያኔን የታገሉና የጣሉና አሸማቀው መቀሌ የሰደዱትን ጀኞች በአታላዩ የወውያኔ ግርፎች ስማቸውን ብቻ ብልጽግና ብለው የሚዘርፉ ና የሚያስገድሉ የከትማ ቤትና ቦታ ባልተመረጠና በማይገባው ከንቲባ እንደ ንጉሥ የፈለገውን የሚያፈርስ ለፈልገው ወገኖቹ ቦታና ቤታችሀውን ሸጠው ምትክ ቦታ ከወሰዱ በኋላ ከነልጅልጃቸው ኮንዶምኒየም የሚያድል የአብይ እንደራሴ ታከለ ኡማን የማያውቅ የለም። የወያኔ አስገዳይ የነበረው ምርጫ 97 ወርቅነህ ገበየሁ የውጭ ጉዳይ ምኒስቴርነት መሾም የሌቦቹ የነአባዱላ ና የግርማ ብሩ ሥልጣን ላይ መቀመጥ እንድያው አያሳዝንም።አባይጸሃዬና ስዩም መስፍን ወያኔዎቹ ሊቦች ከኦሮም ሌቦች በምን ተሽለው ነው ያብይ ሹም የሆኑት፡፡ይልቅ አብይን ኢትዮጵያዊ መሆን ባፍ ብቻ አይደለም በትግባር ሌባ ትግሬ ሆነ ኦሮሞ ሆነ አማራ ሆነ ሌባ ነው።ሃቅን ካልያዘ በምቀላመድ አገር አይገነባም። መንጋ አንድ ቀን የተከልከውን ዛፍና አበባ እንድልነበር ያደርገዋል።ጠንካራ ህጋዊ ርምጃ መውሰድ አብይን ተማር በሉት፡፡የወያኔ ሹሞች ከቀበሌ ወደላይ ቀይር።የወያኔን ሕግ ካልለወጥክ ያንተ ብልጽግ ና ወዳቂ ነው።

    Reply
  4. getachew gebru says

    July 23, 2020 10:49 am at 10:49 am

    terrorists ( olf & tplf) will be disappear! while prosperity rise up!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule