• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሽብርተኛ ትርጉም

March 31, 2016 01:31 am by Editor 1 Comment

የሚማር የለም እንጂ የሚማር ቢኖር የሽብርተኛነትን ትርጉም ሰሞኑን በቤልጂክ እያየንና እየሰማን ነው፤ በኢትዮጵያ ያሉ የእውቀት ምልክቶችን በዶላር እየገዙ ስማቸው ላይ የለጠፉ ጉልበተኞች ተናገርክ(ሽ) ብለው ብቻ ሳይሆን አሰብህ(ሽ) ብለው ሰፋፊ እስር ቤቶች እያሰሩ ወጣቶችን ሲያጉሩበት ምክንያታቸው ሽብርተኛነት ነው፤ ሽብር ማለት ሰሞኑን በቤልጂክ አውሮጵላን ጣቢያና በባቡር ጣቢያ ላይ እንደታየው ከሆነ ኢትዮጵያ ውስጥ አልታየም፤ ከታየም በአገዛዙ ኃይሎች የተፈጸመ ነው፤ ለብዙ ዓመታት ሲፈጸም የቆየ ነው፤ የኢትዮጵያ ጉልበተኞች ከቻሉ ሊያስተውሉት የሚገባ አንድ ነገር አለ፡- ሽብርም ነጻነትን ይፈልጋል፤ በቤልጂክ ሽብሩን የፈጸሙት ሁሉ ነጻነትን ፈልገው ከአገራቸው የተሰደዱና በአገራቸው ያላገኙትን ነጻነት በሰው አገር እየተሞላቀቁበት እንደሆነ የሚያመለክት ነው፤ ትርጉሙ፡- ነጻነት በሌለበት ሽብር አይኖርም፤ እንዴት ብሎ? የት ተደብቆ? የት ሸምቆ?

ሽብርን የጸነሰውን እንዳያስብ አፍኖ፣ እንዳይናገር አንደበቱን መርጎ፣ እንዳይንቃሳቀስ በዳኛ ትእዛዝ ወህኒ ቤት ውስጥ ቆልፎ ሽብርን ማቆም አይቻልም፤ የሚቻለው፣ እየሆነ ያለውም ዝንባሌው ያላቸው ኢትዮጵያውያን ለሽብር ትምህርት ወደአውሮፓና ወደአሜሪካ እንዲሄዱ የሚገፋፋቸው ነው፤ የዚህን ግፊት ውጤት የኢትዮጵያ ጉልበተኞች የሚወዱት አይመስለኝም፤ መጠቃት እንደማጥቃት አያስደስትም!

የእኛ ጉልበተኞች ሽብር ምን እንደሆነ አያውቁም፡፡

የእኛ ጉልበተኞች በንግግርና በተግባር መሀከል ያለውን ልዩነት አያውቁም፤ በቤልጂክ ሽብር የተባለው ሠላሳ አንድ ያህል ሰዎች የሞቱበት፣ ወደሦስት መቶ ሠላሳ ያህል ሰዎች የተጎዱበት ነው፤ ኢትዮጵያ ውስጥ እንዲህ ያለ ነገር ደርሶ ያውቃል? እንዴታ! በዙ ጊዜ፤ ግን ሽብርተኞች በተባሉትና በታሰሩት አይደለም፤ በተመቻቸውና ሕግ በማይደርስባቸው ሌሎች ጉልበተኞች የተፈጸመ ነው፡፡

የእኛ ጉልበተኞች በፍርሃት የደነዘዘው አንጎላቸው ዓይናቸው እውነቱን እንዲያይ፣ ጆሮአቸው እውነትን እንዲሰማና ልባቸው ወደመወያየትና ወደእርቅ እንዲያቀና አያደርጋቸውም፤ ወላጆቻቸውን ንቀው ብቻቸውን የቆሙ ስለሆኑ መካሪ የላቸውም፤ መንፈስ ስለሌላቸው መንፈሳዊ አባት የላቸውም፤ ያሳዝናሉ፡–

ሀሳቤን አንዱ ግጥሜ ይገልጽልኛል መሰለኝ፡– የሞተ ኅሊና

የማይጣላ ኅሊና ያለው

እንዴት የታደለ ነው!

እግዜር ብቻ ነው ኅሊና የሌለው፤

የማይሳሳት የማየወቆጨው፡፡

ሰው ሰውነቱ፣ ጭንቀቱና ልፋቱ፣

ኅሊናው ከስሜቱና ከፈላጎቱ መጣላቱ፣

የሚረሳ የሚሳሰት፣ የማይታየው የፊቱ፣

የሚወድ፣ የሚጠላ፣ የሚፈራ፣ ኧረ ስንቱ!

ከሳሽ፣ ተከሳሽ፣ ዳኛ መሆን

እንዴት ይችላል መበየን?

ሲያፍነው ግን ኅሊናውን

አይለይም ጨለማውን ከብርሃን!

ኅሊናውን ገደለ ሰው

ማን ሊቀረው? ምን ሊያቅተው?

የጉልበቱ መሣሪያ ነው፤

ጊዜ ጉልበቱን እስቲሰብረው! … …

እውነተኞቹ ሽብርተኞች በኢትዮጵያ ውስጥ ካሉ ከሥልጣን ውጭ አይደሉም፤ ከሥልጣን ውጭ ሆነው ቅራኔ የሚያሰሙ ጉልበታቸው እዚያው ላይ ያበቃል፤ በምድረ ኢትዮጵያ ሽብርን መቃወም ሽብርተኛ ያደርጋል፤ ወህኒ ያስገባል፤ ተመስገን ደሳለኝ፣ እስክንድር ነጋ፣ አብርሃ ደስታ፣ … በወህኒ ቤት የሚማቅቁት ቅንጣት የሚያህል የሽብር ተግባር ፈጽመው አይደለም፤ ሽብር እንዳይፈጸም ስለታገሉ ነው፤ ሽብር ከነገሠ ሰላም ወንጀል ይሆናል፤ በኢትዮጵያ ሰላም ዋጋ እያጣ መሄድ ላይ መሆኑን የሚጠራጠር የለም፤ ከባሕር ማዶ የተጀመረው ቀረርቶ ወደተግባር ሲለወጥ መፍራት ፋይዳ የለውም፤ ለጉልበተኞቹ የሚያዋጣው የፍርሃት ጊዜው አሁን ነው! እንደሳዳም ሁሴንና እንደጋዳፊ እንደአይጥ ከተሸጎጡበት ስርቻ እየተጎተቱ ሲወጡ አይደለም፡፡

መጋቢት 2008

(ምንጭ: Mesfin Wolde-Mariam Blog)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. eunetu says

    April 13, 2016 05:47 pm at 5:47 pm

    እጅግ የማከብርዎትና የምወድዎት የተከበሩ ፕ/ር መስፍን
    ከእርስዎና ከመሳሰሉት ለራሳቸው ከማይኖሩ ስጦታዎቻችን
    የመማር ልብ የሌለው ሰው በምድሪቷ ላይ የሌለ ቢመስልም
    አንዳንዶቻችን ስለእውነት መኖር ማለት ምን ማለት እንደሆነ
    ከኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል ቀጥሎ ከእርስዎ ተምረናል!
    እየተማርንም ነውና የዘመናት ጮኸትዎ ባዶ እንዳልቀረ
    ላረጋግጥልዎ እወዳለሁ!!! እንዲያውም ከ 12 ዓመት
    በፊት ስለየወት ”ካለመጽሐፍ ቅዱስ ወንጌል ሰባኪ ወንጌላዊ” ብየ
    በአንድ አርቲክል ላይ ስም አውጥቼልዎት ነበር!!!ከተቀበሉኝ
    ታዲያ ወንጌል ቢጨመርበት ምን ይሆን እንደነበር እንገምት???
    ጤ ና ዎ ት ን እግዚአብሔር ይጠብቅ !!!

    በሐርያት ሥራ 8፡26 ላይ የተገለጸው ኢትዮጵያዊው ጃንዳረባ የንግሥቲቷ ባለሟል ሆኖ ሳለ ለመሳለም ሩቅ መንገድ ቢጓዝም እንደማያውቅ ተረድቶ የሚያነበው የሕይወት መጽሐፍ እንዳልጋባው በግልጽነት በመናገሩ ለችግሩ መፍትሔ በማግኘት ደስተኛ ሆነ። ከዚህ በሳልና የግል ስም እያለው ኢትዮጵያዊ ተብሎ ከተጠራ ሰው የምንማራቸው ሁለት ነገሮች፡ 1/ የሂሳብ ባለሙያ ቢሆንም የማይገባውን መጽሃፍ የሚያነብና አገር አቋርጦ በመሄድ ሊሳለመው የፈለገው ሁሉን ቻይ አምላክ በቦታ የማይወሰን እንደሆነ አለማወቁን ባለመደበቁ የደስታ ምንጭ የሆነውን እውቀት መቀበሉን፣ 2/ የተቀዳንበት እውተኛው ምንጭና ያሁኑ የእኛ ማንነት(አንዳችን ካንዳችን ከመማር ይልቅ ሁሉን አውቃለሁ ባይነት)ፈጽሞ የማይገናኝ በመሆኑ ይባስ ብሎ ኢትዮጵያ የሚለውን የጋራ መጠሪያ ስም መስማት የማይፈልግና የራሱን ታሪክ የማያውቅ አዋቂ ትውልድ ተነስቷል። ጉድ ያለው ገንፎ አድሮ ይፋጃል ይሏል ይሄ ነው!!!

    በእርግጥ አገራችን የአዋቂወች/ያስተማሪዎች ደሃ አይደለችም!እደግመዋለሁ አይደለችም!!! ከራሳችን ሰዎች ለመማር የቀና ልብ ስላጣን እንጂ! ወይም በሌላ ቋንቋ እንደ ኮከብ ብልጭ ሲሉ በብዙዎቻችን ውስጥ ባለው ጨለማ ለሞት አሳልፈን ስለምንሰጣቸው!(በደቂቀ እስጢፋኖስ መጽሐፍ ላይ እርስዎና ፕ/ር ጌታቸው ሃይሌ እንደገለጻችሁልን) ስለዚህ እኔ በበኩሌ ከነጭ አዋቂዎች ብቻ ሳይሆን እንደናንተ ካሉ አባቶቼ/ወገኖቼ በተለይ ማንነቴን የበለጠ ለመማር 100% ዝግጁ ነኝና እስከ ነፍስ ህቅታ ድረስ በርቱ! ደግሞም በነቢዩ ዳንኤል እንደሆነው ቅንነትን የራበው አንበሳ እንኳ አይበላውምና ከመምሸቱ በፊት በርቱ! በርቱ!! በርቱ!!!እናንተ አላዋቂ የሆናችሁ አዋቂ ወገኖቻችንም ቆም ብላችሁ አጠገባችሁ ካለው ወገናችሁ ተማሩ እንማር?ለነገሩ ተማር ያላለው በ40 ዓመቱም አይማርም! ይባል የለ!!! በእውነት ይህ አይሁንባችሁ!!!

    እግዚአብሔር የኢትዮጵያዊውን ጃንደረባ ልብ ይስጠን!!! የገባው አሜን ይበል?
    ፕሮፌሰሮቻችንም አሜን ብትሉ ታተርፋላችሁ እንጂ አትከስሩም።
    ፕ/ር መስፍን ትክክል አይደለሁም?

    እውነቱ /eunethiwot@gmail.com/ ነኝ
    እንድኖር ተፈቅዶልኝ ካለሁበት!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule