• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከተማርኩት ቁጥር 2

April 10, 2016 01:11 am by Editor 1 Comment

አንዳንድ ጊዜ ሳስበው ምን ከምን እንደሚሰራ የማያውቅ ሰው ምንም የሚሰራ አይመስለኝም። እውነት ይሆን? አዎ!

እውነት ሳይሆን አይቀርም። እስቲ አሁን ምርጥ ሾርባ እንዴት እንደሚጠጣ እንጂ ከምንና እንዴት  እንደሚዘጋጅ የማያውቀውን የኔን ብጤ ሾርባ ስራልኝ ብትሉት ምን ይውጠዋል? ለሾርባ የሚሆን ቁሳቁስ በሙሉ በቤት ውስ ቢኖር እንኳን ሾርባ እንዴት እንደሚሰራ ካልታወቀ እዚያ ቤት ውስጥ መቼም ቢሆን ሾርባ አይኖርም። ምክንያቱም ጥሬ እቃው እንጂ ጥበቡ አልተገኘማ!

እናም እስኪ እንጠይቅ። ሀገር የሚሰራው ከምንድነው? በተለይ ታላቅ ሀገር? እንደዱሮዋ ኢትዮጵያና እንደዛሬዋ አሜሪካ ያለ ማለቴ ነው።

ባለፈው ፅሁፌ አሜሪካኖች ካካሄዱት የርእስ በርእስ ጦርነት ሰላምን፣ ፍትህንና ልማትን መፍጠራቸውን ጠቁሜ ያገሬ ሰዎችም ባለፈ የጦርነት ታሪክ መቆዘምና መራገምን ትተው ከጥፋትና ስህተታችን ልማት፣ ሰላም፣ ፍቅር፣ ፍትህና እድገትን ይማሩ ዘንድ ምኞቴን ገልጬ ነበር። ዛሬም በዚሁ መስመር ልቀጥል።

የዛሬው ፅሁፌ ማጠንጠኛ ሃሳብ ላወቀበት ከልዩነት ሀያልነትን መፍጠር ይቻላል የሚል ነው። እናም እንግዲህ ካሜሪካኖች የተማርኩ የመሰለኝ ሌላው ቁም ነገር በልዩነት ታላቅ ሀገር መፍጠር እንደሚቻል ነው። ያሜሪካ ህዝብ ዛሬም ሆነ ዱሮ በባህል፣ በቋንቋ፣ ባስተሳሰብ፣ በዘር፣ በሀይማኖት፣ በመልክ፣ ወዘተ የተለያየ ነው። ልባድርጉልኝ! ልዩነቱ በኢትዮጵያ ህዝብ መካከል ያለውን ያህል ልዩነት ያህል ጠባብ አይደለም። ባሜሪካ ህዝብ መካከል ያለው ልዩነት በተለያዩ ሀገር ህዝቦች መካከል ያለ ልዩነት ያህል ነው። ሰፊና ፈርጀ-ብዙ።

አሜሪካ የተመሰረተችው ባመዛኙ በሀገሬው ተወላጂ አይደለም። ቁጥር ስፍር ከሌላቸው ሀገሮች በተሰባሰቡና ዥንጉርጉር ማንነት ይዘው በመጡ ያለም ህዝቦች ነው። ምናለፋችሁ አሜሪካ ያለም ህዝብ ቅጂ ማለት ናት።

ታዲያ ይህ ከነውጥንቅጥ ተፈጥሮው በዚህ ምድር የሰፈረው ህዝብ ኑሮ ሲጀምር በቋንቋ፣ በባህልና በስነልቡና በማይመስለው ሌላ ቡድን ላይ ጦርነት አልጀመረም። ቋንቋዬን ስለማትናገር የኔ አይደለህምና አትጠጋኝ አላለም። እንደየማንነታችን እንከለልም አላለም። የግዛት ክፍሉም በቋንቋ ወይም በዘር አልነበረም። እኔ እስከተረዳሁት ድረስ በዚህ ሀገር የእስፔን ክልል፣ የጀርመን ክልል፣ የኢራን ክልል፣ የኢትዮጵያ ክልል፣ የናይጄሪያ ክልል ወዘተ የሚል ግዛት የለም።

በሌላ አነጋገር በልዩነታቸው ልዩነትን አልፈጠሩም። ይልቁንም ልዩነታቸውን ሳይረሱ ትኩረታቸውን ህብረትና አብሮ መኖር ላይ አደረጉት። ምኞትና ፍላጎታቸውን አጥብበው ጠባብ ጎሬ ከመፈለግ ይልቅ የጋራ ፍላጎታቸውን የሚያረካ ሰፊ ሀገርና ስርአት መሰረቱ። እያንዳንዱን ህዝብ በየዘሩ በመለየት ለእያንዳንዱ እንደየአመሉ ተለይቶ የሚገባባቸውን ጥቃቅን ጎጆዎችን በመስራት ጊዜያቸውን አላጠፉም። ይልቁንም ለሁሉም ፍላጎት የሚመች ስርአት በመፍጠር ከየሀገሩ የመጣውን ልዩልዩ ስልጣኔ አንድ ላይ በማድረግ በለፀጉበት። ግዛታቸውንም ከምስራቅ ወደምእራብ በማስፋት የጋራ ምድራቸውን አግዝፈው አቀኑት።

እናም አሜሪካኖች ዛሬ በሀምሳ የማይነቃነቁ የብረት ምሰሶዎች በሰሩት ማማ ላይ ተቀምጠው አለምን ቁልቁል ይመለከታሉ። በልዩነት ታላቅነትን መፍጠር ማለት ይህ ነው። የልዩነት ቤት ጠባብ ነው። የህብረት ግን ሰፊ። ለእያንዳንዱ ህዝብ ደካማ ጎጆዎችን ከመቀለስ ይልቅ ለሁሉም የሚሆን ጠንካራ ቤት ሰሩ። አሁንም ልዩነታቸው በሁለት የኢትዮጵያ ብሄረሰቦች መካከል ያለውን ያህል የጠበበ እንዳልነበረ አስተውሉልኝ። ባባትም በናትም የማይገናኙ ያለም ህዝቦች በአንድ ምድር ተሰብስበው ያለጠብ ታላቅ ሀገር ፈጠሩ። አያስቀናም?

ይህን ስታዘብ ታዲያ ኢትዮጵያን አሰብኳት። በዘርማንዘር የማይገኙ ፍጡራን ከየማእዘኑ ተሰባስበው ግዙፍ ሀገር በመመስረት በየሄዱበት አንቱ ተብለው ሲኖሩ ወንድማማቹ የኢትዮጵያ ህዝብ ልዩነቱን እያሰላ ቁልቁል ሲኳትን ስመለከት ልቤ አዘነ። አንዱ ለሌላው ባእድ የሆነው ያሜሪካ ህዝብ ድምፁ ሳይሰማ አዲስና ታላቅ ሀገር ሲገነባ ሊበጠስ በማይችል የዝምድና ገመድ የተሳሰርነው እኛ ግን ተንጫጥተን እንኳን ነባሩን ክብራችንን ለማስጠበቅ ያለመቻላችን እንቆቅልሽ ሆነብኝ።

ላሜሪካውያን ልዩነት መታደል ሆኖላቸው መታፈርንና መከበርን ሲያስገኝ ለኛ እርግማን ሆኖ ለውርደትና ሀፍረት ሊዳርገን የበቃበት ሚስጢር አልፈታልህ አለኝና ተቸገርኩ። በማይገናኝ ባህልና አስተሳሰብ አለምን የገዛ ህብረት መፍጠር መቻሉን በተጨባጭ ስመለከት ባአባትና እናቶቻችን ህብረት የተላለፈልንን ክብርና ታላቅነት መሸከም አቅቶን በመንገዳገድ በልዩነት ታናሽነትን ለመግዛት የምንማስንበት ምክንያት አልገለፅልህ ይለኛል።

በተለይ አንዳንድ ወገኖች (በብዛት ተምረናል የሚሉትን ይመለከታል) ልዩነት ታላቅነትን ሊፈጥር በሚችል ጎዳና እንዲሄድ ከመምራት ይልቅ ከውነተኛ ተፈጥሮው በላይ ተደምሮ በመስጠት መስመሩን ሲያስቱት መመልከት ረፍት ይነሳል። ነባር ታሪክ ያላትን ሀገር በጎደለው ሞልቶ በጋራ ታላቅ ለመሆን ከመድከም ይልቅ ለልዩነት የሚዘምቱበት ምክንያት የተከሰተላቸው ሰዎች ካሉ እድለኞች ናቸው። ለኔ ግን እንደአሜሪካኖች በልዩነት ከመበልፀግ ይልቅ በልዩነት መቆርቆዝ የጤና አይመስለኝም። ከህዝብ ተፈጥሯዊ ልዩነት ሀያል የሆነ ሀገራዊ ማንነት እንደሚገኝ ካላወቅን ወይም ካልፈለግን ምን እንደምንሰራ ልናውቅ አንችልም። ምን ከምን እንደሚሰራ የማያውቅ ሰው ምንም ሊሰራ አይችልምና።

እናም ወገኖቼ፣ የኔ ምኞት የኢትዮጵያን ህዝብ ልዩነት ጉልበት መሆኑን በማመን ያፍሪካ ኮከብ በነበረችው ሀገር ፍትህ በማንገስ ልጆቿ ከዳር እስከዳር ባዲስ ጉልበትና ፍቅር ተነስተው ባጭር ጊዜ ያጣችውን ክብርና ሞገስ በማስመለስ ታምር ሲሰሩ ማየት ነው። ያ ጊዜም የደረሰ ይመስለኛል።

እናየው ዘንድ እድሜውን ያድለን።

ሰላም ሁኑልኝ።

ህሩይ ደምሴ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. eunetu says

    April 13, 2016 05:07 pm at 5:07 pm

    ወንድሜ ህሩይ!

    በሐርያት ሥራ 8፡26 ላይ የተገለጸው ኢትዮጵያዊው ጃንዳረባ የንግሥቲቷ ባለሟል ሆኖ ሳለ ለመሳለም ሩቅ መንገድ ቢጓዝም እንደማያውቅ ተረድቶ የሚያነበው የሕይወት መጽሐፍ እንዳልጋባው በግልጽነት በመናገሩ ለችግሩ መፍትሔ በማግኘት ደስተኛ ሆነ። ከዚህ በሳልና የግል ስም እያለው ኢትዮጵያዊ ተብሎ ከተጠራ ሰው የምንማራቸው ሁለት ነገሮች፡ 1/ የሂሳብ ባለሙያ ቢሆንም የማይገባውን መጽሃፍ የሚያነብና አገር አቋርጦ በመሄድ ሊሳለመው የፈለገው ሁሉን ቻይ አምላክ በቦታ የማይወሰን እንደሆነ አለማወቁን ባለመደበቁ የደስታ ምንጭ የሆነውን እውቀት መቀበሉን፣ 2/ የተቀዳንበት እውተኛው ምንጭና ያሁኑ የእኛ ማንነት(አንዳችን ካንዳችን ከመማር ይልቅ ሁሉን አውቃለሁ ባይነት)ፈጽሞ የማይገናኝ በመሆኑ ይባስ ብሎ ኢትዮጵያ የሚለውን የጋራ መጠሪያ ስም መስማት የማይፈልግና የራሱን ታሪክ የማያውቅ አዋቂ ትውልድ ተነስቷል። ጉድ ያለው ገንፎ አድሮ ይፋጃል ይሏል ይሄ ነው!!!

    በእርግጥ አገራችን የአዋቂወች/ያስተማሪዎች ደሃ አይደለችም!እደግመዋለሁ አይደለችም!!! ከራሳችን ሰዎች ለመማር የቀና ልብ ስላጣን እንጂ! ወይም በሌላ ቋንቋ እንደ ኮከብ ብልጭ ሲሉ በብዙዎቻችን ውስጥ ባለው ጨለማ ለሞት አሳልፈን ስለምንሰጣቸው! ስለዚህ እኔ በበኩሌ ከነጭ አዋቂዎች ብቻ ሳይሆን እናዳንተ ካሉ ወገኖቼ በተለይ ማንነቴን የበለጠ ለመማር 100% ዝግጁ ነኝና በርታ ወንድሜ ህሩይ! ደግሞም በነቢዩ ዳንኤል እንደሆነው ቅንነትን የራበው አንበሳ ሳይቀር አይበላውምና ከመምሸቱ በፊት በርታ! በርታ!! በርታ!!!እናንተ አላዋቂ አዋቂ ወገኖቻችንም ቆም ብላችሁ አጠገባችሁ ካለው ወገናችሁ ተማሩ።

    እግዚአብሔር የኢትዮጵያዊውን ጃንደረባ ልብ ይስጠን!!!
    እውነቱ

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule