• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ

January 6, 2023 03:26 pm by Editor Leave a Comment

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፍትህ ሚኒስቴር በሽግግር ፍትህ ዙርያ ያሉ የፖሊሲ አማራጮችን ለውይይት መነሻ እንዲሆኑ የቀረቡበትን የፖሊሲ ማዕቀፍ አማራጮች ሰነድ ይፋ አድርጓል።

በዚህም ተጠያቂ የሚሆኑ አጥፊዎች በሚለዩበት መንገድ ላይ ኹለት አማራጮች የቀረቡ ሲሆን፣ የመጀመሪያው አማራጭ በወንጀል ክስ ሂደቱ ዋና ጥፋት ፈፃሚዎችን፣ ትዕዛዝ የሰጡ፣ ያቀዱ፣ የመሩ እና ከፍተኛ ሀላፊነት ኖሮባቸው ኃላፊነታቸውን ባለመወጣታቸው ምክንያት ጉዳት እንዲደርስ ያደረጉ ግለሰቦች ላይ ብቻ ትኩረት አድርጎ ክስ እንዲመሰረት ማድረግ የሚል ነው፡፡

ኹለተኛው አማራጭ ደግሞ፤ የወንጀል ክስ ሂደቱን በማንኛውም ደረጃ በጉልህ የሰብአዊ መብት ጥሰት የተሳተፉ ሰዎችን በማካተት እንዲከናወን ማድረግ የሚል ነው፡፡

በፖሊሲ አቅጣጫ አማራጮች መሰረትም የትኞቹ ጉዳዮች እንደሚያስከስሱ፣ በተቋማዊ ጉዳዮች፣ እውነትን ማፈላለግ እና ይፋ ማውጣት፣ እርቅ፣ ምህረት፣ ማካካሻ እንዲሁም ተቋማዊ ማሻሻያዎች ላይ አማራጮች የቀረቡ ሲሆን፣ ውሳኔ የሚያስፈልጓቸው ጉዳዮችም ይፋ ተደርገዋል፡፡

ሰነዱን መነሻ በማድረግ በሽግግር ፍትህ ዙርያ በአገር-አቀፍ ደረጃ ውይይት እና ክርክሮችን በስፋት በማካሄድ፣ በአገራችን ነባራዊ ኹኔታ የተሻሉ አማራጮችን በመለየት እና የፖሊሲ መነሻ ሃሳቦቹን በማዳበር በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ማዕቀፍ እንዲኖር ለማድረግ መታሰቡንም ሚኒስቴሩ ገልጿል።

ከዚህ አንፃር፤ በቀጣይ በአገር-አቀፍ ደረጃ ተከታታይ የፖሊሲ ውይይት መድረኮች እንደሚዘጋጁ የገለጸው ፍትህ ሚኒስቴር፤ በቅድሚያ ለዚህ መነሻ ይሆን ዘንድ ሰነዱን ለህዝብ ይፋ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑ ታምኖበታል ብሏል።

ከውይይቶች ባሻገርም በሰነዱ ዙሪያ ያሉ አስተያየቶችን ለሚኒስቴሩ ማቅረብ እንደሚቻል ፍትህ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

ለውይይት የቀረበው የሽግግር ፍትሕ የፖሊሲ ማዕቀፍ አማራጮች ሰነድ ከዚህ በታች ይገኛል።

ኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ የፖሊሲ አቅጣጫ አማራጮች 2015Download
Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Law, Right Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule