• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የተመላሾች ጉዳይ …

January 14, 2014 03:46 am by Editor Leave a Comment

በርካታ ከሳውዲ ወደ ሃገር ቤት የተመለሱ ዜጎችን በሚመለከት የጀርመንና የአሜሪካ ራዲዮን ጨምሮ በርካታ የመገናኛ ብዙሃን አንድ አይነት የሚመስል መረጃ  ግፉአን ተመላሾችን እማኝ እያደረጉ መረጃ አቀብለውናል ። “ራፕለር ” በታዝነው ሳምንት ባቀበለን መረጃ ሻንጣቸው ጠፍቷቸው በአንድ የሻንጣ ማጠራቀሚያ ግቢ ሻንጣቸውን ሲፈትሹ የሚያሳየውን ፎቶ አስደግፎ የተመላሾችን አስተያየት አካቶበታል። ዜጎች ወደ ሳውዲ ሲሰደዱ ከቤተሰብ ፣ ከዘመድ አዘመድ አዝማድና ከተለያዩ ቦታወች የወሰዱትን የብድር ገንዘብ ስላልመለሱ ኑሯቸው የሰመረ እንዳልሆነ እየተናገሩ ነው ።  ሃገር ቤት ገብተው የስራ ማጣት እና እሳት የሆነው  የኑሮ ውድነት ግራ ያጋባቸው  በርካቶችም አሁንም መልሰው ለስደት እንደቋመጡ እኛ የምንቀርበው መረጃ ባይስማማ የፈረንጆቹ መገናኛ ብዙሃን የሚያቀርቡት የገሃዱን እውነት አንድምታ ያሳያል።

በግል ሃገር ግብተው  የማገኛቸውን  በርካቶች ሃገር ቤት ተመልሰው የጋጠማቸው የኑሮ ውድነት አማሯቸዋል።  መልሶ ማቋቋሙ ደግሞ ከወሬ ባለፈ አለመጀመሩን እየሰማን ነው ። ባሳለፍነው እሁድ በጀርመን ራዲዮ እንዎያይ ፕሮግራም የቀረበው ተመላሽ ወንድምም ተመላሾችን በማደራጀቱና መልሶ በማቋቋሙ ረገድ የተጀመረ ነገር እንደ ሌለ መረጃውን አካፍሎናል። በአንጻሩ በመንግስት ኢቲቪና የቀሩት በስሩ የሚተዳደሩት መገናኛ ብዙሃን የሚናገሩት የሚታመን ከሆነ “ተመላሾቹ በየክልሉ ተደራጅተው እራሳቸውን የሚያቋቁሙበት ስራ ተጀመሯል!” የሚል መልካም መረጃ እያስተላለፉ ይገኛሉ …ከዚህ ጋር ያያዝኩት አዲስ ዘመን ጋዜጣ “ከስደት ተመላሾች ሥልጠና ጀምረዋል !” በሚል ሁላችንም ሳውዲን ለቀን ወደ ሃገር እንገባ ዘንድ የሚያበረታታ መልካም የብስራት ዜና አሰራጭቷል። …  እውነት ከሆነ ማለቴ ነው !  ይህንን አሻግሮ ተቀምጦ “እውንት እውሸት “ማለት አይቻልምና ሊናገሩ የሚገባቸው ባለቤቶቹ ብቻ ናቸው ። ተመላሾች ሆይ ምን ትላላችሁ?

አለም አቀፉ የስደተኞች ተጠሪ IOM መስሪያ ቤት ተመላሾችን መልሶ ለማቋቋም  $13.1 ሚሊዮን ዶላር ወይም 9.5 ዩሮ እንደሚያስፈልግ ይፋ አድርጓል ።  የስደተኞች ንብረት በተለይ የሻንጣ ጌጣጌጡን መጥፋት  ጉዳይ አሳሳቢነት ግን ከፍተኛ ሃላፊዎችን ሳይቀር ያስደመመ እንደሆነ በሚሰራጩት መረጃዎች ለመረዳት አልገደደንም ።

“ወደ ሃገር  ግቡ አንገባም ፣ እንግባ አትገቡም …”

ከአሰሪያቸው ጋር የማይሰሩና በህገ ወጥነት የተፈረጁ ዜጎች  ወደ ሃገር እንዲመለሱ የሚጠይቀው የሳውዲ መንግስትን ጨምሮ የኢትዮጵያ ኢንባሲና የቆንስል መስሪያ ቤቶች ጥሪ ነው ። ጥሪው በቀጥታ የሚመለከታቸው ሰነዳቸውን ያላሟሉ የሚባሉት በባህር በኡምራና ሃጅ ብቻ ሳይሆን በስራ ኮንትራት መጥተው ከአሰሪዎቻቸው ጋር የማይሰሩ “ህገ eth saudi1ወጥ ” የተባሉ ዜጎች ግን “ሳውዲን ለቃችሁ ውጡ! ” የሚለውን ጥሪ ችላ በማለት ዘና ብለው የተለመደ ኑሯቸውን መኖር ጀምረዋል።  ፍርሃትና  ጭንቀቱ የት እንደገባ ባይታወቅም የሳውዲ መንግስት ባሳለፍነው ሳምንት ጉዳያቸውን ጀምረው ላልጨረሱ የሰጠው የሁለት ወር ማስተካከያ ጊዜ ገደብ ነዋሪውን ያዘናጋው ይመስላል።  ያን ሰሞን በስጋት እቃቸውን ሲጠራርፉ  የነበሩት ዛሬ እቃቸውን ወደ ነበረበት መልሰው የለመዱትን የመዘናጋት ኑሮ መግፋት ይዘዋል። አንዳንዶቹን ጠይቄያቸው “ዛሬም የሳውዲ መንግስት አይጨክንም ህጉን ያሻሽለዋል !” በማለት ሲመልሱልኝ አንዳንዶቹ ደግሞ “ሃገር ቤት የሄዱት የኑሮ ውድነት እያማረራቸው እየሰማን መሄዱ ማበድ ነው “ሲሉ መልሰውልኛል ። እስርና ቅጣቱስ አልኳቸው እንዴት ትቋቋሙት አላችሁ?  አልኳቸው ” የፈለገው ቢሆን እዚሁ ሁኔ መቋቋም እና መቀበሉ ይቀላል !” ሲሉ ክችም ያለ መልስ ሰጥተውኛል  ! እኒህ ለእኔ ቀቢጸ ተስፈኞች ናቸው ..

የሳውዲን መንግስት ወደፊት ጠንከር ብሎ ይወስደዋል ተብሎ የሚጠበቀውን  እርምጃ  የፈሩ ጥቂቶች አሁንም ወደ መጠለያ በመግባት እና ለመግባት በዝግጅት ላይ ናቸው።  ያም ሆኖ በጅዳ የሽሜሲ መጠለያ ሰነዳቸው ይሰራላቸው ዘንድ በመጠባበቅ ላይ እንዳሉ በስልክ እየደወሉ  “ተቸገርን! ።የምግቡ ችግር ቢቻልም ፣ በመጓጓዙ ላይ ዘገየን፣ መላ ወደሚገኝበት ቦታ ጩኸልን !” እያሉ ተማጽነውኛል ።  ትናንት ሰኞ ከቀትር በኋላ ጀምሮ እስከ እኩለ ሌሊት መረጃ ያቀበሉኝ “ከመዲናና ከጅዳና ከተለያዩ ቦታወች ከቀናትና ከሳምንታት እና ከወር በፊት ወደ ሽሜሲ ገባን!” ያሉኝ ወገኖች ” ጉዟችን ለማፋጠን በቆንስላችን ክትትልና ትብብር ስለማይደረግልን  እየተጉላላን ነው !” ሲሉ ጭንቀታቸውን ገልጸውልኛል። በኮንትራት ስራ የመጡትን ወደ ሃገር ቤት ለመመለስ ችግሩ መቋጫ አግኝቷል ቢባልም አሁን ድረስ ችግሩ አለመፈቱን ነዋሪዎች ከሽሜሲ መጠለያ  በምሬት ገልጸውልኛል ። “ካለፉት ሶስት ቀናት ወዲህ ወደ መጠለያ ለመግባት ፈልገን ወደ መጠለያ የሚወስደን የሚቀበልን አጣን! ውጡ ብለውን እንውጣ ስንል የሚያስወጣን አጣን  !” ያሉኝ በርካቶችም በጅዳ ሸረፍያ እንደሚገኙ አጫውተውኛል ። ህግን ተጋፍተው በሳውዲ ለመኖር ተስፋቸው የተሟጠጠ እንህኞች የሚደግፋቸው ይሻሉ … !

የጀዛን … እውነት

በጅዛን በተደጋጋሚ የሚደርሰኝ መረጃ በማቅረቤ ያን ሰሞን የወገን ለወገን ደራሽ ኮሚቴን የጠለፉት የመንግስት ፖለቲካ ድርጅት አንዳንድ ካድሬዎች እዚህ ጅዳ ከጎኔ ተቀምጠው አዲስ የማጥላላት ዘመቻ ጀምረዋል። የወገንን ሳይሆን ለመንግስት ሃላፊዎች በማደገግደግ  እንደፈለጉ በሚፈነጩበት የህዘብ ግንኙነት የፊስ ቡክ ገጽ ” እውነቱ  ይሄ ነው ” በሚል ባስነበቡን መረጃ የእኔን ሳይሆን የተበዳዮችን እውንት ጥላሸት ሊቀቡት ከጅለው ሳይ አዝኛለሁ። “በሉ !” ትዕዛዙን ይፈጽሙ ዘንድ አንደተባሉት በማስተጋባት እውነቱን ” ውሸት!”  ብለውታል። ሳያፍሩ፣ ሳይፈሩ!

የተሳሳተ መረጃ ደረወሶኝ ይሆን ስል አጠራጠሩኝ ። ግን እንዲያ አልነበረም ። መረጃውን ለማጣራት ጅዛኖችን ደጋግሜ  “ሃሎ” ብያቸው ነበር …  ያገኘኋቸው አስገራሚና አሳዛኝ መረጃዎች  ” አሳ ጎርጓሪ ዘንዶ ያወጣል !” አስብሎኛል ። ከህግ ታሳሪዎቹ ጋር በነበረኝ ቆይታ “የጅዳ ቆንስል ሃላፊዎች የእናንተን ጉዳይ  እየሰሩ እንደሆነ  ተነግሮኛል ፣ እውነት ነውን?   !”ያልኳቸው ወንድሞች የተባለው መረጃ ትክክል አለመሆን ተበሳጭተው የሚጠይቅላቸው ስላጡትነና በሚሰራው ስራ ዙሪያ  ብዙ አጫውተውኛል ። በአሳዛኝ እና በአስገራሚው የስደት ህይወት እጁ የተቆረጠውን ወንድም ፣ ታናሽ ወንድሙን  እና እሱ በርሃ ላይ ሲጓዙ ተይዘው ዛፍ ላይ ታስረው ተንጠልጥለው ሲውሉ አቅም አንሶት ከፊቱ ላይ ደክሞ ተዝለፍልፎ የሞተ ታናሽ ወንድሙን ታሪክ ወንድሙ ራሱ ይነግረናል … ይህ ወንድሙን በበርሃ ላይ ያጣ ወንድም ስድስት ወር እንዲታሰር ቢፈረድበትም ከአመት በላይ ጠያቂ አጥቶ መንገላታቱን መስማት ያማል ! ይህንንም በድምጽ ይዠዋለሁ ! ትሰሙታላችሁ …  እናም በጀዛን ፍርዳቸውን የጨረሱ የህግ ታራሚዎች ድምጽ  “ወደ ሃገር እንድንገባ ድጋፍ የሚያደርግልን የመንግስታችን ሃላፊዎችን አጣን ! ” የሚል ነው ! የጅዛን እውነቱ ይህ ነው!eth saudi2

መንግስት ሆይ ስማን … ወገን ሆይ ስማን!

ሰነድ የሌላቸው ዜጎች “ህግን ተላልፋችኋል!” ተብለው “ከሃገር ይውጡ!” ተብሏል!  ዜጎች ከሃገር ውጡ ሲባሉ መንገዱን በማመቻቸቱ ረገድ ከኢትዮጵያ መንግስት የኢንባሲና ቆንስል መስሪያ ቤቶች ከመረጃ ጀምሮ ብዙ ይጠበቃል!  ቢያንስ ሁሌ እንደምለው “መውጣት አልፈልግም !” የሚለውን ዜጋ ምክንያት ሊሰማበሊደመጥ ይገባልና ፣ ስሙት ! ” እንውጣ!”ሲል እንግልት የሚገጥመውን ዜጋ ታደጉት! በአረብ አሰሪዎች ቤት ሆነው “ወደ ሃገራችን እንግባ ድረሱልን!”  የሚሉ የኮንትራት ሰራተኞችን ያላባራ ጩኸት ይሰማል ።  የሰማነውን ለሃላፊዎች ብናሰማም መፍትሔ የሚሰጥ ጠፍቷል!  ይሀወ አሁንመወ ያሳስባል!  “ድረሱልን! ” ሲሉ ደራሽ ያጡትን የኮንትራት ሰራተኞች  ፈጥናችሁ ድረሱላቸው!  መውጣት ያለበት “ህገ ወጥ ” የተባለ ሁሉ ዜጋ ይውጣ  !  አስከፊውን የስደት እንግልትና መከራን ማየቱ ይብቃን!

ሰው ተጨንቆ ተጠቦ ፣ የመረጃዎችን እውነት እውሸት የሙግት ጅማሮ  ቀልቤን ባይስበውና መነታረኩን ባልፈልገውም ለሚወረወረው አሳሳች መረጃ እውነቱ ለማስጨበጥ ስድቡን ባልገባበትም ትክክለኛውን መረጃ ከምንጩ ለማቅረብ ወደ ኋላ የምል አይደለሁም!  ይህም በመሆኑ ይህንና ያንን በሰፊው እስክመለስበት ሰላም  !

አስኪ ቸር ያሰማን  !

ነቢዩ ሲራክ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule