• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ዓለም አቀፍ ሕብረት ለፍትሕ – የኢትዮጵያ ጉዳይ

December 15, 2014 05:52 pm by Editor Leave a Comment

ጋዜጣዊ መግለጫ

ዓለም አቀፍ ሕብረት ለፍትሕ-የኢትዮጵያ ጉዳይ በፍትሕ ለሚያምኑ ድርጅቶችና ሰዎች በሙሉ መልካም ምኞቱን እየገለጸ በቫቲካን ድጋፍ በመርዝ ጋዝ ጭምር በመጠቀም ኢትዮጵያ ላይ ስለ ተፈጸመወ የፋሺሽት የጦር ወንጀል የሰው እልቂትና እጅግ ከፍ ያለ ውድመት  የካቲት 12-14 ቀኖች 2007 ዓ/ም ወይም በዚያን ሰሞን በየሐገሩና በየከተማው የመታሰቢያ ክብረ በዓል በማዘጋጀት እንዲዘክሩት ግብዣውን በትሕትና ያቀርባል።

እንደሚታወቀው፤ ፋሺሽት ኢጣልያ ኢትዮጵያን በወረረችበት በ1928-34 ዘመን አንድ ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ከመጨፍጨፋቸው በላይ 2,000 ቤተ ክርስቲያኖችና 525,000 ቤቶች ወድመዋል። እንዲሁም በሚሊዮን የሚቆጠሩ እንስሳት አልቀዋል። በተለይ፤ በየካቲት 12-14 ቀኖች 1929 ዓ/ም ፋሺሽቶች አዲስ አበባ ከተማ 30000 ኢትዮጵያውያንን እንደ ጨፈጨፉ የታወቀ ነው። ስለዚህ ማሕበራችን በሚያከናውነው ዓለም አቀፍ ዘመቻ:

(ሀ) ኢጣልያ ተገቢውን ካሣ ለኢትዮጵያ እንድትከፍል፤

(ለ) ቫቲካን የኢትዮጵያን ሕዝብ ይቅርታ እንድትጠይቅ፤

(ሐ) ኢጣልያና ቫቲካን ከኢትዮጵያ የተዘረፉትን ንብረቶች እንዲመልሱ፤

(መ) የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ኢጣልያኖች በኢትዮጵያ ላይ የፈጸሙትን ወንጀል እንድትመዘግብ፤ እና

(ሰ) አፊሌ በምትሰኛ የኢጣልያ ከተማ ለጦር ወንጀለኛው ለግራዚያኒ በቅርቡ የተቋቋመው መታሰቢያ እንዲወገድ እየጣረ ነው።holding heads

በዚህም ዓመት በየካቲት 12 ሰሞን እንዲከናወን የሚጠበቀው የመታሰቢያ ክብረ በዓል ቀን፤ በጸሎት፤ በጉባኤ/በስብሰባ፤ እና/ወይም በሰላማዊ ሰልፍ እንዲሆን ይጠበቃል። ማሕበሩ፤ በዚያን ጊዜ የሚሰራጭ የአቤቱታ ደብዳቤዎች ያዘጋጃል።

ማሕበሩ ከፍ ካለ ምሥጋና ጋር የሚያስታውሰው፤ ባለፈው ዓመት የካቲት 12 የመታሰቢይ ቀን የተከበረው በ30 ከተሞች ሲሆን እነርሱም አዲስ አበባ፤ ዋሺንግተን ዲ.ሲ.፤ ኒው ዮርክ፤ ዳላስ፤ ሒዩስተን፤ አትላንታ፤ ሚኒያፖሊስ፤ ሲያትል፤ ሎዛንጀለስ፤ ዴንቨር፤ አውሮራ፤ ቺካጎ፤ ቦስተን፤ ታምፓ፤ ላስቬጋስ፤ ማያሚ፤ ኮሎኝ፤ ሙኒክ፤ ስቶክሆልም፤ ሮም፤ ኢየሩሳሌም፤ ቴልአቪቭ አምስተርዳም፤ ዘሔግ፤ ጃሜይካ፤ ሲድኒ፤ ቫንኩቨር፤ ጆሐንስበርግ፤ ዱባይ፤ እና ለንደን ነበሩ። በዚህ ዓመትም በነዚህና በሌሎች ከተሞች በሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች ክብረ በዓሉ በሞቀ ሁኔታ እንደሚከበር ይታመናል።

ለተጨማሪ መረጃ ከላይ የተጠቀሰውን ድረ-ገጽ መመልከት ይቻላል።

ቸሩ የኢትዮጵያ አምላክ፤ ለሐገራችን የሚያስፈልገውን ፍትሕ እንድናስገኝ ያበርታን።

PRESS RELEASE

The Global Alliance for Justice – The Ethiopian Cause (GAJEC) presents its compliments to all institutions, and people who believe in justice and calls on them to join and participate in the international event for the commemoration, during or around February 19-21, 2015, of the Ethiopian martyrs, victims of the Italian Fascist war crimes in Ethiopia, with the complicit support of the Vatican, as well as the vast destruction that was inflicted using various war materials including the forbidden mustard poison gas.

It is recalled that during the 1935-41 Italian Fascist occupation of Ethiopia, one million Ethiopians were massacred, 525,000 homes and 2,000 churches as well as millions of animals were destroyed. Therefore, GAJEC has been conducting a global campaign for:

(a) adequate reparations by Italy to Ethiopia;

(b) a Vatican apology to Ethiopia;

(c) restitution of looted Ethiopian properties by Italy and the Vatican;

(d) UN recognition of the Italian war crimes in Ethiopia; and

(e) dismantlement of the mausoleum recently established at Affile, Italy for the Fascist war criminal, Rodolfo Graziani.

GLOBAL_ALLIANCEThe February, 2015 commemoration event is expected to be conducted in the form of public demonstrations at the Italian/Vatican embassies/consulates to which GAJEC’s formal letters of appeal would be submitted, meetings/conferences/symposia, and/or prayers.

GAJEC recalls with appreciation all those supporters of justice who arranged the commemoration event in February, 2014 at Addis Ababa; Washington, DC; New York; Dallas; Houston; Atlanta; Minneapolis; Seattle; Los Angeles; Denver; Aurora; Chicago; Boston; Tampa; Las Vegas; Miami; Cologne; Munich; Stockholm; Rome; Jerusalem; Tel Aviv; Amsterdam; The Hague; Jamaica; Sidney; Vancouver; Johannesburg; Dubai; and London. It is greatly hoped that supporters of justice against Fascist war crimes in Ethiopia in these and other cities throughout the world would arrange the event during February, 2015.
____________________________________________________________________________________
Global Alliance for Justice – The Ethiopian Cause:
www.globalallianceforethiopia.org; info@globalallianceforethiopia.com
4002 Blacksmith Drive, Garland, TX 75044; Phone: (214)703 9022

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእምዬ ምኒልክ አዳራሽ October 30, 2023 10:27 am
  • የኢትዮጵያ መከላከያ መሥራች አጼ ምኒልክ መሆናቸውን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ተናገሩ October 26, 2023 01:30 pm
  • ጥቅምት 15 ለምን? October 26, 2023 01:29 am
  • “በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት” October 26, 2023 12:57 am
  • “ውትድርና ሕይወቴ ነው” October 26, 2023 12:13 am
  • መከላከያ በሁሉም መስክ ኢትዮጵያን የሚመጥን ኃይል እየገነባ ነው October 20, 2023 05:07 pm
  • “ሁሉም ኢትዮጵያዊ ትምህርት ቤት እኩል ነው በችሎታው ነው እንጂ የሚመዘነው” ፕ/ር ብርሃኑ October 20, 2023 04:47 pm
  • 42 የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አመራሮች እና ሠራተኞች ታሰሩ October 18, 2023 04:29 pm
  • በተማሪዎች ፈተና ውጤት ለታየው ውድቀት ትምህርት ሚ/ር ኃላፊ መሆን አለበት ተባለ October 18, 2023 04:00 pm
  • ቀይ ባሕር እና ዓባይ “የኅልውና ጉዳይ ናቸው”፤ “መተንፈሻ ወደብ ያስፈልገናል” October 13, 2023 10:04 pm
  • ከ3,106 ትምህርት ቤቶች 1,328ቱ (44%) አንድም ተማሪ አላሳለፉም October 10, 2023 01:51 pm
  • “አቋጥሬ” በአማራ ክልል እያጫረሰ ነው፤ ” ኑሮውን መቋቋም አልቻልንም ” ነዋሪዎች October 10, 2023 09:07 am
  • እሸቴ አሸባሪ፤ ቲዲኤፍ/ትሕነግ “ሰማዕት” – የዘመናችን ጉድ! October 7, 2023 06:47 am
  • በወልቃይት 1.1ሚሊዮን ኩንታል ሰሊጥ ለመሰብሰብ ከ1 ሚሊዮን በላይ ሠራተኛ ይፈለጋል September 27, 2023 10:42 am
  • በአማራ ክልል ሰላም ዕጦት ከ90.5 ቢሊዮን ብር በላይ ፕሮጀክቶች ቆመዋል September 27, 2023 08:41 am
  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule