• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የእርቅ ቀመር/ፎርሙላ

May 17, 2014 04:23 am by Editor Leave a Comment

የኢትዮጵያ ህዝብ 65 በመቶው እድሜያቸው ከ24 አመት በታች ነው። ለዚህ ተተኪ ትውልድ የመግባባትን ፓለቲካ በአርዓያነት ማውረስ አስፈላጊነት ስላመንኩበት ስለ እርቅና መግባባት ለመሟገትና ፋና ወጊ ሚና ለመጫወት የዜግነት ሃላፊነቴን ጀምሬያለሁ።

65ሰዎች እርቅን የተለያዬ ትርጉም እንደሚሰጡት የ65Percent.org ድረ-ገጽን ከጀመርኩበት ከዚህ አመት አጥቢያ አንስቶ እየተረዳሁ ነው። ድረ-ገጼን ከመጀመሬ በፊት ከ16 ኢትዮጵያውያን ጋር በፓልቶክ የፖለቲካ መወያያ ክፍሎች የሃሳብ አሰሳ አድርጌያለሁ። ከአሰሳው እንደተረዳሁት ስለእርቅ እና ፖለቲካዊ መግባባት በቂ የሚዲያ ሽፋንም ሆነ ውይይት አልተደረገም።

ለአገራችን የፖለቲካ ሁኔታ ከትጥቅ ትግልና ከአመጽ የላቀ አማራጭ አለን፦ የእርቅና መግባባት አማራጭ። በዚህ አጭር ጽሁፍ  ሰለፖለቲካዊ እርቅና መግባባት በጽንሰ ሃሳብ ደረጃ ጥቂት አጠቃላይ ነጥቦችን እዳስሳለሁ።

ሁለት ጭብጦች፦ ውጥረትና አለመግባባት

አንደኛ፦ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ስርአትና ሂደት በውጥረት ውስጥ ይገኛል። ሁለተኛ፦ የአገራችን ፖለቲካ በእጅጉ ባለመግባባት የተጠመደ ነው። እነዚህ ሁለት ጭብጦች የአደባባይ ሚስጥር ቢሆኑም መፍትሄ ለመቅረጽ በነዚህ ነጥቦች ላይ መስማማቱ እንደ ቅደመ ሁኔታ እመለከተዋለሁ። ውጥረትና አለመግባባት የሰፈነበትን ፖለቲካችንን ማርገብና ማግባባት መሰረታዊ የእርቅ ግብ ነው።

victims of red terror
(ፎቶ፦ የቀይ ሽብር ሰማእታት)

መደበኛ ፓለቲካዊ ሂደት

የፓለቲካችንን ውጥረት ማርገብ ለፓለቲካዊ መግባባት ሁኔታዎችን ያመቻቻል። የአገራችን ፖለቲካ ላለፉት 40 አመታት ከነውጥ  ወደ ቀውስ ፤ ከአመጽ ወደ እልቂት ፤ ከቁስል ወደ ቂምና ጥላቻ ሲገለባበጥ የቆየ ነው። ፖለቲካችን መደበኛ ሆኖ አያቅም። መደበኛ ፓለቲካዊ ሂደት ማለት ከቀውስ ፥ ከደም መፋሰስ ፥ ከአላስፈላጊ ውጥረትና ከጥላቻ ውጥቶ ፥ ወደ ሚዛናዊ የሃሳብ ፉክክርና ፍትሃዊ ሂደት ውስጥ የገባ ማለት ነው።

ፓለቲካዊ ቅራኔ

የፓለቲካዊ ውጥረታችን መንስኤው ፓለቲካዊ ቅራኔ ነው። የአገራችን ፓለቲካዊ ውጥረት የብዙ ዘመናት ፡ የልዩ-ልዩ ድርብርብ ቁስሎች ፡ ቁርሾዎች ፡ ያልተቋጩ ታሪካዊ ክስተቶች ፡  ርዮተአለሞች ፡ ማንነቶች ፡ ስሜቶች … ወዘተ ውጤት ነው። እነዚህ ድርብርብና ዘርፈ-ብዙ የቅራኔ መንስኤዎች አልፎ አልፎ ምልክታዊ ትኩረት አግኝተዋል። እንደ ዋቢ ከሚጠቀሱት አንዱ የቀይ ሽብር መታሰቢያ ሙዚየም ሲሆን ፡ ሌላው የወታደራዊው መንግስት ባለስልጣናት ከእስር መለቀቅ ነው።

m and d
(ፎቶ፦ ማንዴላና ዴክላርክ)

ሆኖም ግን የፖለቲካ ቅራኔያችን ሲባባስ ፥ የፖለቲካ ምህዳር ሲጠብ ፥ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ከመድብለ ፓርቲ ስርአት ወደ አሃዳዊ ፓርቲ ቁጥጥር ሲያዘነብል እንጂ ፡ ወደ መደበኛ ፖለቲካዊ ሂደት ሲገባ አይታይም።

ዘርፈ-ብዙ መፍትሄ

በቅራኔ እየከረረ ያለው ፓለቲካዊ ውጥረታችንን ማርገብ የምንችለው የቅራኔው መንስኤዎች ላይ በማተኮር ፥ ተግባራዊና አስታራቂ መፍትሄ በመወጠን ነው። ይሄንን ለማድረግ የሌሎች አገሮችን ተሞከሮ በአርአያነት በመጠቀም  የኢትዮጵያን ፖለቲካዊ ቅራኔ ምንጮች ማድርቅ እንችላለን።

ይሄን ለማድረግ የኔልሰን ማንዴላ መንግስት የወሰደውን ቀመር/ፎርሙላ መጠቀሙ አማራጭ የሌለው ሆኖ አግኘቼዋለሁ። ማንዴላ የደቡብ አፍሪካ ነጮች መንግስት በጥቁሮችና በሌሎች ዘሮች ላይ ያደረገውን ግፍና እልቂት በጥበብና  አርቆ አስተዋይነት አርግቦታል።

ምንም እንኳን ኢትዮጵያና ደቡብ አፍሪካ በእጅጉ የተለያዬ ፓለቲካዊ ሁኔታዎች ላይ ያሉ ቢሆንም፥  የማንዴላ ቀመር የኢትዮጵያን ፖለቲካዊ ውጥረት ለማርገብ ፍቱን መድሃኒት መሆኑን አምንበታለሁ። ላብራራ።

የማንዴላ ቀመር/ፎርሙላ፦ እውነታ + እውቅና + ፍትህ = እርቅ

የማንዴላ መንግስት የውጥረት ማርገብ ስራውን የጀመረው እውነታን በማፈላለግ ስራ ነው። ቀጥሎም በተሰበሰበው መረጃ ላይ recon22እውቅና የመስጠት ስራ ተካሄደ። የእውቅና ሂደቱን በቴሌቪዥን የተከታተላችሁ እንደምታስታውሱት በጣም ልብ ይሚነካ ሂደት ነበር። በመጨረሻም እውነታ ማፈላለጉና እውቅና የመስጠቱ ስራ ወደ ፍትህ አመራ።

የፍትህ ሂደቱ አንዳንድ የደቡብ አፍሪካ አፓርታይድ መንግስት ተሳታፊዎችን ከክስ ነጻ ማድረጉ ይታወሳል። ይህ የሆነው በእውነታና በእውቅና ሂደት ውስጥ ስለተሳተፉና ለፈጸሙት በደል ይቅርታ ሰለጠየቁ ፡  እንዲሁም ያንን በማድረጋቸው የማንዴላ መንግስት ለተሳታፊዎቹ ከሰጣቸው ዋስትና የተነሳ ነበር። ለተበዳዮችና ቤተሰቦቻቸውም የደቡብ አፍሪካ መንግስት የገንዘብ ካሳ ከፍሏል። ውጥረትን ማርገብ ማለት ይህ ነው።

የእርቅ ሂደት ውጥረትን ያረግባል ፡ ለመግባባት ምቹ ሁኔታዎችን ይፈጥራል።

እውነታ + እውቅና + ፍትህ = እርቅ!

*********

ያዬ አበበ የ65Percent.org መስራች ነው። የ65ፐርሰንት ድረ-ገጽ ግብ ለፓለቲካዊ እርቅና መግባባት የመሟገትና ፋና ወጊ መሆን ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule