• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የእርቅ ቀመር/ፎርሙላ

May 17, 2014 04:23 am by Editor Leave a Comment

የኢትዮጵያ ህዝብ 65 በመቶው እድሜያቸው ከ24 አመት በታች ነው። ለዚህ ተተኪ ትውልድ የመግባባትን ፓለቲካ በአርዓያነት ማውረስ አስፈላጊነት ስላመንኩበት ስለ እርቅና መግባባት ለመሟገትና ፋና ወጊ ሚና ለመጫወት የዜግነት ሃላፊነቴን ጀምሬያለሁ።

65ሰዎች እርቅን የተለያዬ ትርጉም እንደሚሰጡት የ65Percent.org ድረ-ገጽን ከጀመርኩበት ከዚህ አመት አጥቢያ አንስቶ እየተረዳሁ ነው። ድረ-ገጼን ከመጀመሬ በፊት ከ16 ኢትዮጵያውያን ጋር በፓልቶክ የፖለቲካ መወያያ ክፍሎች የሃሳብ አሰሳ አድርጌያለሁ። ከአሰሳው እንደተረዳሁት ስለእርቅ እና ፖለቲካዊ መግባባት በቂ የሚዲያ ሽፋንም ሆነ ውይይት አልተደረገም።

ለአገራችን የፖለቲካ ሁኔታ ከትጥቅ ትግልና ከአመጽ የላቀ አማራጭ አለን፦ የእርቅና መግባባት አማራጭ። በዚህ አጭር ጽሁፍ  ሰለፖለቲካዊ እርቅና መግባባት በጽንሰ ሃሳብ ደረጃ ጥቂት አጠቃላይ ነጥቦችን እዳስሳለሁ።

ሁለት ጭብጦች፦ ውጥረትና አለመግባባት

አንደኛ፦ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ስርአትና ሂደት በውጥረት ውስጥ ይገኛል። ሁለተኛ፦ የአገራችን ፖለቲካ በእጅጉ ባለመግባባት የተጠመደ ነው። እነዚህ ሁለት ጭብጦች የአደባባይ ሚስጥር ቢሆኑም መፍትሄ ለመቅረጽ በነዚህ ነጥቦች ላይ መስማማቱ እንደ ቅደመ ሁኔታ እመለከተዋለሁ። ውጥረትና አለመግባባት የሰፈነበትን ፖለቲካችንን ማርገብና ማግባባት መሰረታዊ የእርቅ ግብ ነው።

victims of red terror
(ፎቶ፦ የቀይ ሽብር ሰማእታት)

መደበኛ ፓለቲካዊ ሂደት

የፓለቲካችንን ውጥረት ማርገብ ለፓለቲካዊ መግባባት ሁኔታዎችን ያመቻቻል። የአገራችን ፖለቲካ ላለፉት 40 አመታት ከነውጥ  ወደ ቀውስ ፤ ከአመጽ ወደ እልቂት ፤ ከቁስል ወደ ቂምና ጥላቻ ሲገለባበጥ የቆየ ነው። ፖለቲካችን መደበኛ ሆኖ አያቅም። መደበኛ ፓለቲካዊ ሂደት ማለት ከቀውስ ፥ ከደም መፋሰስ ፥ ከአላስፈላጊ ውጥረትና ከጥላቻ ውጥቶ ፥ ወደ ሚዛናዊ የሃሳብ ፉክክርና ፍትሃዊ ሂደት ውስጥ የገባ ማለት ነው።

ፓለቲካዊ ቅራኔ

የፓለቲካዊ ውጥረታችን መንስኤው ፓለቲካዊ ቅራኔ ነው። የአገራችን ፓለቲካዊ ውጥረት የብዙ ዘመናት ፡ የልዩ-ልዩ ድርብርብ ቁስሎች ፡ ቁርሾዎች ፡ ያልተቋጩ ታሪካዊ ክስተቶች ፡  ርዮተአለሞች ፡ ማንነቶች ፡ ስሜቶች … ወዘተ ውጤት ነው። እነዚህ ድርብርብና ዘርፈ-ብዙ የቅራኔ መንስኤዎች አልፎ አልፎ ምልክታዊ ትኩረት አግኝተዋል። እንደ ዋቢ ከሚጠቀሱት አንዱ የቀይ ሽብር መታሰቢያ ሙዚየም ሲሆን ፡ ሌላው የወታደራዊው መንግስት ባለስልጣናት ከእስር መለቀቅ ነው።

m and d
(ፎቶ፦ ማንዴላና ዴክላርክ)

ሆኖም ግን የፖለቲካ ቅራኔያችን ሲባባስ ፥ የፖለቲካ ምህዳር ሲጠብ ፥ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ከመድብለ ፓርቲ ስርአት ወደ አሃዳዊ ፓርቲ ቁጥጥር ሲያዘነብል እንጂ ፡ ወደ መደበኛ ፖለቲካዊ ሂደት ሲገባ አይታይም።

ዘርፈ-ብዙ መፍትሄ

በቅራኔ እየከረረ ያለው ፓለቲካዊ ውጥረታችንን ማርገብ የምንችለው የቅራኔው መንስኤዎች ላይ በማተኮር ፥ ተግባራዊና አስታራቂ መፍትሄ በመወጠን ነው። ይሄንን ለማድረግ የሌሎች አገሮችን ተሞከሮ በአርአያነት በመጠቀም  የኢትዮጵያን ፖለቲካዊ ቅራኔ ምንጮች ማድርቅ እንችላለን።

ይሄን ለማድረግ የኔልሰን ማንዴላ መንግስት የወሰደውን ቀመር/ፎርሙላ መጠቀሙ አማራጭ የሌለው ሆኖ አግኘቼዋለሁ። ማንዴላ የደቡብ አፍሪካ ነጮች መንግስት በጥቁሮችና በሌሎች ዘሮች ላይ ያደረገውን ግፍና እልቂት በጥበብና  አርቆ አስተዋይነት አርግቦታል።

ምንም እንኳን ኢትዮጵያና ደቡብ አፍሪካ በእጅጉ የተለያዬ ፓለቲካዊ ሁኔታዎች ላይ ያሉ ቢሆንም፥  የማንዴላ ቀመር የኢትዮጵያን ፖለቲካዊ ውጥረት ለማርገብ ፍቱን መድሃኒት መሆኑን አምንበታለሁ። ላብራራ።

የማንዴላ ቀመር/ፎርሙላ፦ እውነታ + እውቅና + ፍትህ = እርቅ

የማንዴላ መንግስት የውጥረት ማርገብ ስራውን የጀመረው እውነታን በማፈላለግ ስራ ነው። ቀጥሎም በተሰበሰበው መረጃ ላይ recon22እውቅና የመስጠት ስራ ተካሄደ። የእውቅና ሂደቱን በቴሌቪዥን የተከታተላችሁ እንደምታስታውሱት በጣም ልብ ይሚነካ ሂደት ነበር። በመጨረሻም እውነታ ማፈላለጉና እውቅና የመስጠቱ ስራ ወደ ፍትህ አመራ።

የፍትህ ሂደቱ አንዳንድ የደቡብ አፍሪካ አፓርታይድ መንግስት ተሳታፊዎችን ከክስ ነጻ ማድረጉ ይታወሳል። ይህ የሆነው በእውነታና በእውቅና ሂደት ውስጥ ስለተሳተፉና ለፈጸሙት በደል ይቅርታ ሰለጠየቁ ፡  እንዲሁም ያንን በማድረጋቸው የማንዴላ መንግስት ለተሳታፊዎቹ ከሰጣቸው ዋስትና የተነሳ ነበር። ለተበዳዮችና ቤተሰቦቻቸውም የደቡብ አፍሪካ መንግስት የገንዘብ ካሳ ከፍሏል። ውጥረትን ማርገብ ማለት ይህ ነው።

የእርቅ ሂደት ውጥረትን ያረግባል ፡ ለመግባባት ምቹ ሁኔታዎችን ይፈጥራል።

እውነታ + እውቅና + ፍትህ = እርቅ!

*********

ያዬ አበበ የ65Percent.org መስራች ነው። የ65ፐርሰንት ድረ-ገጽ ግብ ለፓለቲካዊ እርቅና መግባባት የመሟገትና ፋና ወጊ መሆን ነው።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule