• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የእርቅ ቀመር/ፎርሙላ

May 17, 2014 04:23 am by Editor Leave a Comment

የኢትዮጵያ ህዝብ 65 በመቶው እድሜያቸው ከ24 አመት በታች ነው። ለዚህ ተተኪ ትውልድ የመግባባትን ፓለቲካ በአርዓያነት ማውረስ አስፈላጊነት ስላመንኩበት ስለ እርቅና መግባባት ለመሟገትና ፋና ወጊ ሚና ለመጫወት የዜግነት ሃላፊነቴን ጀምሬያለሁ።

65ሰዎች እርቅን የተለያዬ ትርጉም እንደሚሰጡት የ65Percent.org ድረ-ገጽን ከጀመርኩበት ከዚህ አመት አጥቢያ አንስቶ እየተረዳሁ ነው። ድረ-ገጼን ከመጀመሬ በፊት ከ16 ኢትዮጵያውያን ጋር በፓልቶክ የፖለቲካ መወያያ ክፍሎች የሃሳብ አሰሳ አድርጌያለሁ። ከአሰሳው እንደተረዳሁት ስለእርቅ እና ፖለቲካዊ መግባባት በቂ የሚዲያ ሽፋንም ሆነ ውይይት አልተደረገም።

ለአገራችን የፖለቲካ ሁኔታ ከትጥቅ ትግልና ከአመጽ የላቀ አማራጭ አለን፦ የእርቅና መግባባት አማራጭ። በዚህ አጭር ጽሁፍ  ሰለፖለቲካዊ እርቅና መግባባት በጽንሰ ሃሳብ ደረጃ ጥቂት አጠቃላይ ነጥቦችን እዳስሳለሁ።

ሁለት ጭብጦች፦ ውጥረትና አለመግባባት

አንደኛ፦ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ስርአትና ሂደት በውጥረት ውስጥ ይገኛል። ሁለተኛ፦ የአገራችን ፖለቲካ በእጅጉ ባለመግባባት የተጠመደ ነው። እነዚህ ሁለት ጭብጦች የአደባባይ ሚስጥር ቢሆኑም መፍትሄ ለመቅረጽ በነዚህ ነጥቦች ላይ መስማማቱ እንደ ቅደመ ሁኔታ እመለከተዋለሁ። ውጥረትና አለመግባባት የሰፈነበትን ፖለቲካችንን ማርገብና ማግባባት መሰረታዊ የእርቅ ግብ ነው።

victims of red terror
(ፎቶ፦ የቀይ ሽብር ሰማእታት)

መደበኛ ፓለቲካዊ ሂደት

የፓለቲካችንን ውጥረት ማርገብ ለፓለቲካዊ መግባባት ሁኔታዎችን ያመቻቻል። የአገራችን ፖለቲካ ላለፉት 40 አመታት ከነውጥ  ወደ ቀውስ ፤ ከአመጽ ወደ እልቂት ፤ ከቁስል ወደ ቂምና ጥላቻ ሲገለባበጥ የቆየ ነው። ፖለቲካችን መደበኛ ሆኖ አያቅም። መደበኛ ፓለቲካዊ ሂደት ማለት ከቀውስ ፥ ከደም መፋሰስ ፥ ከአላስፈላጊ ውጥረትና ከጥላቻ ውጥቶ ፥ ወደ ሚዛናዊ የሃሳብ ፉክክርና ፍትሃዊ ሂደት ውስጥ የገባ ማለት ነው።

ፓለቲካዊ ቅራኔ

የፓለቲካዊ ውጥረታችን መንስኤው ፓለቲካዊ ቅራኔ ነው። የአገራችን ፓለቲካዊ ውጥረት የብዙ ዘመናት ፡ የልዩ-ልዩ ድርብርብ ቁስሎች ፡ ቁርሾዎች ፡ ያልተቋጩ ታሪካዊ ክስተቶች ፡  ርዮተአለሞች ፡ ማንነቶች ፡ ስሜቶች … ወዘተ ውጤት ነው። እነዚህ ድርብርብና ዘርፈ-ብዙ የቅራኔ መንስኤዎች አልፎ አልፎ ምልክታዊ ትኩረት አግኝተዋል። እንደ ዋቢ ከሚጠቀሱት አንዱ የቀይ ሽብር መታሰቢያ ሙዚየም ሲሆን ፡ ሌላው የወታደራዊው መንግስት ባለስልጣናት ከእስር መለቀቅ ነው።

m and d
(ፎቶ፦ ማንዴላና ዴክላርክ)

ሆኖም ግን የፖለቲካ ቅራኔያችን ሲባባስ ፥ የፖለቲካ ምህዳር ሲጠብ ፥ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ከመድብለ ፓርቲ ስርአት ወደ አሃዳዊ ፓርቲ ቁጥጥር ሲያዘነብል እንጂ ፡ ወደ መደበኛ ፖለቲካዊ ሂደት ሲገባ አይታይም።

ዘርፈ-ብዙ መፍትሄ

በቅራኔ እየከረረ ያለው ፓለቲካዊ ውጥረታችንን ማርገብ የምንችለው የቅራኔው መንስኤዎች ላይ በማተኮር ፥ ተግባራዊና አስታራቂ መፍትሄ በመወጠን ነው። ይሄንን ለማድረግ የሌሎች አገሮችን ተሞከሮ በአርአያነት በመጠቀም  የኢትዮጵያን ፖለቲካዊ ቅራኔ ምንጮች ማድርቅ እንችላለን።

ይሄን ለማድረግ የኔልሰን ማንዴላ መንግስት የወሰደውን ቀመር/ፎርሙላ መጠቀሙ አማራጭ የሌለው ሆኖ አግኘቼዋለሁ። ማንዴላ የደቡብ አፍሪካ ነጮች መንግስት በጥቁሮችና በሌሎች ዘሮች ላይ ያደረገውን ግፍና እልቂት በጥበብና  አርቆ አስተዋይነት አርግቦታል።

ምንም እንኳን ኢትዮጵያና ደቡብ አፍሪካ በእጅጉ የተለያዬ ፓለቲካዊ ሁኔታዎች ላይ ያሉ ቢሆንም፥  የማንዴላ ቀመር የኢትዮጵያን ፖለቲካዊ ውጥረት ለማርገብ ፍቱን መድሃኒት መሆኑን አምንበታለሁ። ላብራራ።

የማንዴላ ቀመር/ፎርሙላ፦ እውነታ + እውቅና + ፍትህ = እርቅ

የማንዴላ መንግስት የውጥረት ማርገብ ስራውን የጀመረው እውነታን በማፈላለግ ስራ ነው። ቀጥሎም በተሰበሰበው መረጃ ላይ recon22እውቅና የመስጠት ስራ ተካሄደ። የእውቅና ሂደቱን በቴሌቪዥን የተከታተላችሁ እንደምታስታውሱት በጣም ልብ ይሚነካ ሂደት ነበር። በመጨረሻም እውነታ ማፈላለጉና እውቅና የመስጠቱ ስራ ወደ ፍትህ አመራ።

የፍትህ ሂደቱ አንዳንድ የደቡብ አፍሪካ አፓርታይድ መንግስት ተሳታፊዎችን ከክስ ነጻ ማድረጉ ይታወሳል። ይህ የሆነው በእውነታና በእውቅና ሂደት ውስጥ ስለተሳተፉና ለፈጸሙት በደል ይቅርታ ሰለጠየቁ ፡  እንዲሁም ያንን በማድረጋቸው የማንዴላ መንግስት ለተሳታፊዎቹ ከሰጣቸው ዋስትና የተነሳ ነበር። ለተበዳዮችና ቤተሰቦቻቸውም የደቡብ አፍሪካ መንግስት የገንዘብ ካሳ ከፍሏል። ውጥረትን ማርገብ ማለት ይህ ነው።

የእርቅ ሂደት ውጥረትን ያረግባል ፡ ለመግባባት ምቹ ሁኔታዎችን ይፈጥራል።

እውነታ + እውቅና + ፍትህ = እርቅ!

*********

ያዬ አበበ የ65Percent.org መስራች ነው። የ65ፐርሰንት ድረ-ገጽ ግብ ለፓለቲካዊ እርቅና መግባባት የመሟገትና ፋና ወጊ መሆን ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm
  • “ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንግቤ እዋጋለሁ” የሚሉ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል – የመከላከያ ሠራዊት August 1, 2023 09:25 am
  • ደቡብ አፍሪካ የመሸጉ ወንጀለኞች ለሕግ ተላልፈው ሊሰጡ ነው July 31, 2023 09:27 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule