• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ልዑል በሉዓላዊ መንግስት ይሰለጥናል!

September 15, 2016 11:36 pm by Editor Leave a Comment

‶…ልዑሉ በሰዎች መንግስት ሁሉ ላይ ሙሉ ስልጣን እንዳለውና እነዚህንም መንግስታት ለወደደው እንደሚሰጥ እስክታውቅ ድረስ…″ ዳን.4፡32

ሉዓላዊ መንግስት (sovereign nation) በሌሎች ቅኝ ግዛት ወይም ባርነት ስር ያልወደቀ ራስ-ገዝና ነጻ መንግስት ሲሆን የሃገሪቱ የአመራር አካላት እንደመጨረሻው ውሳኔ ሰጪ አካላት ተደርገው ይወሰዳሉ፡፡ የህዝቡም ሰላምና የሁለንተና እድገት በሃገሪቱ አመራር አካላት ብቃትና ቅንነት ይወሰናል፡፡ ሉዓላዊነት ሌሎች አካላት በአንድ ሃገር የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ እንዳይገቡ (meddle) ዋስትና እንደሚሰጥ በማሰብ አንዳንድ መንግስታት በማንአለብኝነት ከእግዚአብሔርም ከሰውም የሚያነካካ እርምጃ ሲወስዱ ይስተዋላሉ፡፡

ከነዚህም አንዱ ለትምህርታችን በቅዱሱ መጽሀፍ በስፋት የተተረከልን የባቢሎን ንጉስ ናቡከደነጾር ነው፡፡ ይህ እግዚአብሔር ባርያዬ/አገልጋዬ እያለ ደጋግሞ የሚጠራውና ስኬትን ያበዛለት ንጉስ የዙፋኑንና የስኬቱን ምንጭ ዘንግቶ በብዙ ትዕቢትና ነውር ሲመላለስ የምድር ነገስታት ገዢ ከሆነው ከልዑል (the most high) እግዚአብሔር ዘንድ ፍርድ ወጣ—‶መንግስት ከአንተ ዘንድ አለፈች″ (ዳን.4፡31)፡፡ እንደጥፋቱም ጥልቀት አስተማሪ የሆነ ተጨማሪ ቅጣት ተበየነበት—‶ለሰባት ዘመን እንደአውሬ በዱር ተሰድደህ ትኖራለህ″ (ዳን.4፡32)፡፡ ንጉሱን ለዚህ ሁሉ ቅሌት ያበቃው ከላይ በርዕሱ እንደተጠቀሰው ልዑል እግዚአብሔር በሰዎች መንግስት ሁሉ ላይ ሙሉ ስልጣን እንዳለውና ሹም ሽርም በእጁ እንደሆነ አለማወቁ ነበር፡፡

ልዑል በሉዓላዊ መንግስት እንዲሰለጥን የሃገሬ መሪዎች ያውቁ ይሆን?

መሰልጠን ማለት ያገባኛል በሚልና በባለቤትነት መንፈስ በሃይልና ስልጣን በሰዎችና አሰራራቸው ላይ ጣልቃ መግባት ማለት ነው፡፡ እውነት ነው የአፍሪካ ህብረትም ሆነ የተባበሩት መንግስታት በሉዐላዊ መንግስት አመራርና አሰራር በቀጥታ መሰልጠን አይችሉም፡፡ ነገር ግን ልዑል እግዚአብሔር የኢህአዲግን መንግስት ጨምሮ በሁሉ ይሰለጥናል፡፡ ‶ከፍ ካለው በላይ ከፍ ያለ ይመለከታልና″ (መክ.5፡8) ልዑል በሰው ልብ የታሰበውን፣ በጓዳና በአደባባይ የሚደረገውን ያውቃል፡፡ እርሱን ፈርተን ህዝቡንም አክብረን በመልካም ብናስተዳድር ስልጣናችን ይጸናል/ይረዝማል፤ መተካታችንም በክብር ይሆናል፡፡

እንደባቢሎኑ ንጉስ እግዚአብሔርን ባለመፍራትና ሰውንም ባለማፈር በምንወስዳቸው እርምጃዎች ልዑሉ ሊንቀን፣ መንግስትን ሊነጥቀን፣ በግል ሊቆነጥጠን፣ ለወደድነው ሳይሆን ለወደደውም ስልጣኑን ሊሰጥ ይችላል፡፡ በተለይም እንደኢትዮጵያ ባሉ በጸሎት የሚበረቱ የእምነት ሰዎች ባሉበት ሃገር የልዑል ጣልቃ ገብነት ይፈጥናል፡፡

በገዛ ስልጣኑ መንግስትን ከደርግ ነጥቆ በሃገራችን የሾማችሁ የኢህአዲግ አመራር አካላት እያደገ ከመጣው የማንአለብኝነት አካሄድ ተመልሳችሁ በህዝቡና በእግዚአብሔር ፊት ቅንነት ያለበትን እርምጃ እንድትወስዱ አበረታታለሁ/እጸልይማለሁ፡፡ ናቡከደነጾር ተጸጽቶ ከክፉ ስራው በተመለሰ ጊዜ መንግስቱን እንደመለሰለት/እንዳጸናለት ምናልባትም ሽንገላ የሌለበትን የተሃድሶ እርምጃችሁን አይቶ ልዑል ህዝቡን ዳግም ሊያስገዛላችሁና የስልጣን ዘመናችሁንም ሊያረዝም ይችላል፡፡ በልበ-ደንዳናነት በአመጽ ብንጸና ግን ያሰማራነው ጦር እንኳን እግዚአብሔርን የህዝቡንም እንቅስቃሴ ሊያስቆም አይችልምና ለዘር ማንዘር የሚተርፍ ጠባሳ ትታችሁ እንዳታልፉ በጌታ ፍቅር አሳስባለሁ፡፡

በዚህ አጋጣሚ የአብያተክርስቲያናት መሪዎች እንደባለአደራ ነብያቶችንና ሊቃውንቱን አማክራችሁ የእግዚአብሔርን ሃሳብና የህዝቡ/መንግስት ምላሽ ምን ሊሆን እንዲገባ ምክር እንድትሰጡ በትህትና እጠይቃለሁ፡፡

‶እግዚአብሔር ሆይ መድኃኒትህን እጠብቃለሁ″ ዘፍ.49፡18
ዶ/ር ሳምሶን—ከሃገር ቤት


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule