• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በደቡብ ሱዳን የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ ከሸፈ

December 17, 2013 03:56 am by Editor Leave a Comment

በደቡብ ሱዳን የፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪርን መንግሥት ለመገልበጥ እሁድ ማታ ለሰኞ አጥቢያ ሙከራ ተደርጎ መክሸፉ ተሰማ፡፡ ፕሬዚዳንቱ ሙከራው መክሸፉንና መንግሥት ሁሉንም ነገር በቁጥጥር ሥር ማዋሉን በመግለጽ ለደቡብ ሱዳን ሕዝብ መግለጫ ሰጡ፡፡ በዋንኛው ጎሣ ዲንቃ እና ኑዌር ጎሣ መካከል የተከሰተው ፍጥጫ እስካሁን የለየለት መስመር አልያዘም፡፡

Pagan Amum
ፓጋን አሙን

ከወራቶች በፊት የደቡብ ሱዳን ነጻ አውጪ ንቅናቄ (ኤስ.ፒ.ኤል.ኤም.) ዋና ጸሐፊ የሆኑት ፓጋን አሙን የአመራር ብክነትና ሌሎች ችግሮች አሉባቸው በሚል እንዲገመገሙ ፕሬዚዳንቱ የመርማሪ ኮሚሽን አቋቁመው ነበር፡፡ ኮሚሽኑ ዋና ጸሐፊው የአመራር ጉድለት የታየባቸው በመሆኑ ከሥልጣን እንዲነሱ የውሳኔ ሐሳብ ሰጥቷል በሚል ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ዋና ጸሐፊውን ጨምሮ የአገሪቱን ምክትል ፕሬዚዳንት ዶ/ር ሬይክ ማቻር ከሥልጣናቸው ባለፈው ሐምሌ ወር አስወግደው ነበር፡፡ ከዚሁ ጋር ተያይዞም ኪር ካቢኔያቸውን በሙሉ ከሥልጣን በማባረር አዲስ የካቢኔ ሲያዋቅሩ ቆይተዋል፡፡

ሁኔታው በተከሰተበት ወቅት ብዙሃን በሆኑት የሳልቫ ኪር ዲንቃ ጎሣ እና ቀጣዩ አብላጫ ቁጥር ባላቸው የኑዌር ጎሣዎች መካከል ያለውን የኃይል ፍጥጫ በግልጽ የሚያሳይ መሆኑ ተነግሮ ነበር፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘም ፕሬዚዳንቱ አምባገነናዊ አካሄድ እየተከተሉ መሆናቸው እና ሁኔታው ወደ ከፍተኛ ደረጃ መድረሱ የማይቀር መሆኑ ሲተነበይ ቆይቷል፡፡

ለንዶን ለሚታተመው አሻራቅ አል-አውሳት ቃለምልልስ የሰጡት ዋና ጸሐፊ አሙም የኤስ.ፒ.ኤል.ኤም. ካውንስል ስብሰባ ላይ እንዳይገኙ ፕሬዚዳንቱ እንዳስከለከሏቸው ይናገራሉ፡፡ አሙም ሲቀጥሉም “የፖሊት ቢሮ አባል እንደመሆኔ ልከለከል አይገባኝም” በማለት በአሁኑ ጊዜ አገራቸው ወደ ሥርዓት አልበኝነት እየተጓዘች መሆኗን ተናግረዋል፡፡ ሳልቫ ኪርንም ኤስ.ፒ.ኤል.ኤም. ከተቋቋመበት ዓላማ ውጪ ድርጅቱንና አገሪቷን እየመሯት እንደሆነ በመናገር አማሯቸዋል፡፡ በአገራቸው ላይ ሥርዓት አልበኝነት እየሰፈነ መሆኑን በመግለጽ የንቅናቄው ዋና መሥራች የነበሩት ጆንግ ጋራንግ ከሞቱ ወዲህ አመራሩን የተቆጣጠሩት ሳልቫ ኪር ወደ አምባገነናዊ አገዛዝ እያመሩ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

ዶ/ር ሬይክ ማቻር
ዶ/ር ሬይክ ማቻር

በ2015 ለሚካሄደው ምርጫ ራሳቸውን እጩ ተወዳዳሪ አድርገው ለማቅረብ እያዘጋጁ የነበሩት ምክትል ፕሬዚዳንት ዶ/ር ሬይክ ማቻር በሳልቫ ኪር ከሥልጣን መባረራቸው በቀላሉ የሚያቆም ሳይሆን ወደከፋ የፖለቲካ ፍጥጫ ብሎም የጎሣ ግጭት እንደሚቀየር በአጽዕኖት ይታመናል፡፡ በጦሩ ውስጥ ይኸው የዘር ልዩነት መኖሩና በዲንቃ እና ኑዌር መካከል ያለው ጥላቻ አላስፈላጊ መጋጨት ፈጥሮ ችግሩ እንዳይሰፋ ቢታሰብም ይኸው ልዩነት አገርሽቶ ለመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ እንደበቃ ይታመናል፡፡ ከኑዌር ጎሣ የሆኑት ማቻር ከሥልጣን በተወገዱበት ወቅት አገራቸው ወደ “አንድ ሰው የበላይነት” እያመራች መሆኗን ተናግረው ነበር፡፡

በሳልቫ ኪር አመራር የተማረሩት ሌላዋ የጆን ጋራንግ ባለቤት ርብቃ ጋራንግ ናቸው፡፡ ባለፈው ሳምንት ለራዲዮ በሰጡት ቃለምልልስ ሲናገሩ “ይህችን አገር በተገቢው ሁኔታ እየመራናት አይደለም፤ ከዚህ ይልቅ ቀውሶችን ለማስተካከል ስንሞክር ነው የቆየነው፡፡ ባለቤቴ ከሞተ ወዲህ ምንም ደስተኛ አይደለሁም፤ ሳልቫ ኪር ለምን ደስተኛ እንዳልሆንኩ ጠይቆኝ አያውቅም፡፡ ኑሮን ለማሸነፍና ልጆቼን ለማሳደግ ጁባ ላይ የዶ/ር ጆን ጋራንግ ት/ቤት ከፍቻለሁ፡፡ በመንግሥት አመራር ላይ የሚገኙ ሚኒስትሮች ሥራቸውን ለማከናወን ምንም ዓይነት ግብዓት የላቸውም፤ የኤስ.ፒ.ኤል.ኤም. አመራር በደቡብ ሱዳን ውስጥ እያደረገ ያለው በነጻነት ትግሉ ወቅት (ለሞትንበት) ዓላማ አይደለም” ብለዋል፡፡

ሰኞ ዕለት ባልተለመደ መልኩ ሙሉ የወታደራዊ አለባበስ ተከትለው ንግግር ያደረጉት ሳልቫ ኪር መፈንቅለ መንግሥት መሞከሩን ካመኑ በኋላ “መንግሥት በጁባ ያለውን የደኅንነት ሁኔታ በቁጥጥሩ ሥር አድርጓል” ብለዋል፡፡ የከተማዋ አየርመንገድ እንዲሁም የቴሌቪዥን አገልግሎት ለበርካታ ሰዓታት ተቋርጦ እንደነበር ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

ሁኔታው ጋብ እንዳለ በባለሥልጣኖቻቸው ታጅበው ወደ ቴሌቪዥን መስኮት ብቅ ያሉት የጦሩ ዋና አዛዥና የፓርቲው ዋና ሊቀመንበር ሳልቫ ኪር “መፈንቅለ መንግሥት ሙከራ” መደረጉንና የቀድሞ ምክትል ፕሬዚዳንት ዶ/ር ማቻር ደጋፊ የሆኑ ወታደሮች ድርጊቱን መፈጸማቸውን በመግለጽ መንግሥታቸውና ጦሩ ሁኔታውን በቁጥጥር ሥር ማድረጉን ተናግረዋል፡፡ በመቀጠልም “ይህ ዓይነቱ ድርጊት አዲስ በተወለደችው አገራችን እንዲቀጥል ፈጽሞ አልፈቅድም፤ አልታገስም፡፡ ይህንን የወንጀል ተግባር በጥብቅ አወግዘዋለሁ” በማለት ድርጊቱን የፈጸሙትን ሁሉ ለፍርድ እንደሚቀርቧቸው ቃል ገብተዋል፡፡ ከሰኞ ጀምሮም ከጸሐይ ግባት እስከ ማለዳ ድረስ የሰዓት እላፊ አውጀዋል፡፡

ዶ/ር ባርናባ ማሪያል ቤንጃሚን
ዶ/ር ባርናባ ማሪያል ቤንጃሚን

በቅርቡ ወደ ሥልጣን የመጡትና ሰሞኑን በአሜሪካ ጉብኝት ላይ የነበሩት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የተወሰኑ ወታደሮች በዋና ከተማዋ የሚገኝ የጦር መሣሪያ ማከማቻ ላይ ጥቃት መሰንዘራቸውንና በአሁኑ ወቅት የተወሰኑ ፖለቲከኞች በቁጥር ሥር መዋላቸውን ለአሶሺየትድ ፕሬስ ተናግረዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት ዶ/ር ማቻር በቁጥጥር ሥር ውለዋል እየተባለ የሚነገር ቢሆንም እስካሁን ያሉበት ቦታ አልታወቀም፡፡ ቃል አቀባያቸው ግን በቁጥጥር ሥር እንዳልዋሉና በሰላም እንደሚገኙ መናገራቸውን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ወደ ደቡብ ሱዳን ጁባ በመደወል የተለያዩ ምንጮችን ለማነጋገር የሞከረ ሲሆን የኃይል ሚዛኑ ወዴት እንዳጋደለ በተጣራ ሁኔታ ለማወቅ እንደማይቻል ተረድቷል፡፡ ፍጥጫውና በጎሣ መካከል ያለው ውጥረት እንደቀጠለ ለመረዳትም ችሏል፡፡

ደቡብ ሱዳንን ነጻ ለማውጣት ሲታገልና በመሥራቹ ኮ/ል ዶ/ር ጆን ጋራንግ ይመራ የነበረውን የነጻ አውጪ ግንባር የቀድሞው ኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት መንግሥቱ ኃይለማርያምና አገዛዛቸው ይደግፍ እንደነበር ይታወሳል፡፡ በአንጻሩም እስላማዊው የሰሜን ሱዳን አገዛዝ ለሻዕቢና ለወያኔ የማያቋርጥ ዕገዛ በማድረግ ወደሥልጣን እንዲመጡ ትልቅ ሚና መጫወቱ ይታወቃል፡፡ ደቡብ ሱዳን ነጻ ከወጣች በኋላ ህወሃት/ኢህአዴግ “አዲስ አገር ለመገንባት” በሚል የደቡብ ሱዳንን ቴሌኮሙኒኬሽን፣ ደኅንነት፣ ፖሊስ፣ ኢኮኖሚ፣ ወዘተ በለመደው የተለያየ መረብ መቆጣጠሩን መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡

ይህ ዜና እሰከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ ሰኞ የተካሄደውን መፈንቅለ መንግሥት ሙከራ አስመልክቶ በደቡብ ሱዳን ውስጥ ካለው “ረዘም ያለ እጅ” አኳያ ህወሃት/ኢህአዴግ ምንም አልተነፈሰም፡፡ በሌላ በኩል ይህ የመፈንቀለ መንግሥት ሙከራ ከመደረጉ አንድ ቀን በፊት በአሜሪካ በጉብኝት ላይ ይገኙ የነበሩት የደቡብ ሱዳንን ውጭ ሚ/ር ዶ/ር ባርናባ ማሪያል ቤንጃሚን ዋሺንግተን ዲሲ  በማግኘት በአስቸኳይ የውስጥ ችግራቸውን በሰላማዊ መንገድ ካልፈቱ አደጋ እንደሚያጋጥማቸው፣ ችግሩ ከ21 በላይ ጎሣ ያለባት አገር ሊያምሳት እንደሚችል፣ የነጻነት ትግሉ ሲጀመርና ሲጠናቀቅ ዓላማው አምባገነናዊ ሥርዓት ለመፍጠር ባለመሆኑ ስህተታቸውን እንዲያርሙ አቶ ኦባንግ ሜቶ መክረው ነበር፡፡ ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ ከውጭ ጉዳይ ሚ/ሩ ጋር ስላደረጉት ውይይት የሰጡትን ዝርዝር ማብራሪያ እናቀርባለን፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule