• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የመከራ ደወል በጋዛ!

July 11, 2014 09:16 am by Editor 2 Comments

ባሳለፍናቸው ሳምንታት የሶስት እስራኤል ታዳጊዎች መጥፋትና ከቀናት በኋላ ተገድሎ ተገኘ። ይህም እስራኤላውያንን አስቆጥቶ በአንድ ታዳጊ ፍልስጥኤማዊ ላይ የበቀል እርምጃ አስወሰደ። ሟች እንጅ ገዳይ አይታወቅም ተባለ። ውጥረቱ ማየል መክረር ያዘ  … የፍልስጥኤም ታጣቂዎች ተፈጸመብን ያሉትን በደል ለመበቀል በአጸፋው በተወንጫፊ ሮኬት ሚሳኤል የእስራኤን መዲና ሳይቀር ማጥቃት ያዙ። ቴል አቢብን፣ እየሩሳሌምና ወደ የተለያዩ ከተሞች ዘልቆ የደረሰው ጥቃት ድንጋጤን ፈጠረ። ጠቅላይ ሚነኒስትር ናታንያሁ ተበሳጩ፣ ተሶረፉ! “እስራኤል አጸፋ ትወስዳለች!” ብለው በተናገሩ ቅጽበት የማጥቃት እርምጃውን አዘዙ! ጥቂቶችን ለማጥቀሰት በጋዛ ፍልስጥኤማውያን ላይ የመከራው ደወል ተደወለ…!

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ናታንያሁ ጋዛን መልሰው ለማጥቃት የክተት አዋጅ ጠሩ። ሰኞ  አጸፋ የአየር ጥቃት እርምጃም ተጀመረ። ማክሰኞ ሮብ ቀጠለ … በርካታ የጋዛ ግፉአን ንጹሃን ዜጎች ህይወት መቀጠፍ ጀመረ ከስምንት አመት በፊት ጋዛን ካደቀቃትና በሽዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የተቀጠፉበት ወረራ በኋላ የመጀመሪያ በሆነው በዚህ የቀጠለ ጥቃት ከ500 በላይ በእስራኤል የተጠኑ የፍልስጥኤም ሚሊሽያ ኢላማዎች ላይ ያነጣጠረ መሆኑ ተነግሯል። ባሳለፍነው ሰኞ በተጀመረው የአየር ድብደባ አቅመ ደካማ ህጻናት፣ ሴቶችና አዛውንትንቶችን ጨምሮ 75 ፍልጥኤማውያን በጥቃቱ መገደላቸውና 500 ያህል ንጹሃን በጸና መቁሰላቸው እየተሰማ ነው።

gazaከጋዛ በፍልስጥኤም ሚሊሽያ ታጣቂዎች በኩል የተተኮሱት ከ200  የማያንሱ ተወንጫፊ ሚሳየሎች በሰው ህይወት ላይ ከባድ የሚባል ጉዳት ባያደርሱም ነዋሪውን ስጋት ውስጥ ጥለውታል። ከተተኮሱት ሚሳየሎች መካከል 40 ያህሉ በእስራኤል ሚሳየል መከላከያ መክሸፋቸውም ተጠቁሟል።

የተቀሰቀሰውን ሁከት ተከትሎ የአለም መራሔ መንግስታት ከመግለጫ  ያለፈ ስራ ሲሰሩ አልታየም። የንጹሃንና የግፉአን ፍልስጥኤም ተራ ዜጎች ደም ሲፈስ መፍትሔ ማምጣት ያልቻለው የተባበሩት መንግስታት ጸሃፊ ባንኪሙን ሁከቱን እና ድብደባውን ከኮነኑበት መግለጫና የአስቸኳይ ስብሰባ ጥሪ አልፈው የፈየዱትና የሚፈይዱት አለ አልልም! የማያልቅበት ስብሰባ መፍትሄ ላይሆን ተጠርቷል። የውግዘት መግለጫ ብቻውን መፍትሄ ሆኖ ነፍስን አይታደግ ነገር ንጹሃን በጠራራ ጸሃይ ግፍ እየተፈጸመባቸው አለም ዝም ያለ ይመስላል!

ቀንደኛ የተባሉትን የሃማስ አላቅሳ ሚሊሽያ ታጣቂዎችን ለማጥቃት በሚል የጋዛ ፍልስጥኤም ንጹሃን በጥይት አረር እየተቃጠሉ፣ እየቆሰሉና  እየሞቱ ነው። በግፉአኑ ላይ ዛሬም አሳዛኝና ልብ ሰባሪ  ግፍ እተፈጸመባቸው ነው!  ይህ ሁሉ እየሆነ አለም ዛሬም ይህን የለየለት የንጹሃን ደም መፈረሰስ ለማስቆም የተጋ አይመስልም።

ብቻ … ለጋዛ ጸልዩ!

ነቢዩ ሲራክ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Tazabi says

    July 12, 2014 05:35 pm at 5:35 pm

    Nebiyu S
    We Ethiopians are living in hell, silent war, our people are being killed quietly for 23 years and still no one knows when it is going to stop. Unfortunately, we have enough destruction not to struggle by being together (united), either by woyane servants, or selfish citizens/so called politicians, could not to stand together and struggle for real freedom of right to live. Now, here you are asking us to cry for Palestine? As human beings we are sorry for them, but they have the whole world to be with them. On the other hand, no country cares about our suffrage. Abused immigrants case by Saudi Government is one good example for Ethiopians horrific problems and no country did care. I think you are enough to do it because you live in the right place to appeal for them. We have full plate of problems that we don’t even know how to solve. Even now, right this moment, citizens are being thrown to jail, being killed at any time, suffering with economic crisis, health issues …, you name it. To cry for your case will be “Yerasua Eyarerebat Yesew Tamasilalch,” for us.

    Reply
  2. Jarso says

    July 17, 2014 05:55 am at 5:55 am

    Who the hell you think sypmathise for dead woods who accepts slavery as a matter of right and waiting for devine or rather the invisible one to fight his enemy, the woyane thugs.it is inconcievable to wipe woyane unless fully commited and put up genuine struggle like youths of the 60 &70. Thus until we take up our macheteand lock horns, weyane shall continue to rule with the usual iron hand.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule