• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ ዘገባ በግድብ ሥራ ላይ ማስጠንቀቂያ ሰጠ

March 11, 2014 08:28 am by Editor 6 Comments

ታላላቅ ግድቦችን በመሥራት ላይ የሚገኙ ታዳጊ አገራት ለከፍተኛ ችግር መጋለጣቸው ተነገረ፡፡ በጉዳዩ ላይ ጥናት ያደረገው የኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ ባወጣው ዘገባ መሠረት አገራቱ ለከፍተኛ ዕዳ እና ከዚያ ጋር ተዛማጅ ለሆኑ ችግሮች የሚጋለጡ መሆናቸውን ፋይናንሺያል ታይምስ ጥናቱን ጠቅሶ ዘግቧል፡፡ “ለሕዝባችሁ የምታስቡ ከሆነ ገንዘቡን ለሌላ ተግባር አውሉት” በማለት ምክርም ሰጥቶዋል፡፡

እኤአ ከ1934ዓም ጀምሮ በ65 አገራት የተገነቡ 245 ግድቦችን በማካተት የተደረገው በዓይነቱ ለየት ያለው አጠቃላይ ጥናት በቅርቡ እየተገነቡ ያሉትን ታላቅ ግድቦችንም ያካተተ ነው፡፡

በኢትዮጵያ ካለው የግልገል ጊቤ ሦስት ግድብ ጀምሮ እስከ ብራዚሉ የአማዞን ቤሎ ሞንቴ የግድብ ፕሮጀክቶችን የሚገነቡት ታዳሽ ኃይልን አጠቃቀም ለማጎልበት እና የኤሌክትሪክ አቅርቦትን ለመጨመር በሚል እንደሆነ የጠቀሰው ጥናታዊ ዘገባ ግንባታው በርካታዎችን ከመኖሪያቸው እንዲፈናቀሉ የሚያደርግና ለብዝሃ ህይወት አደጋ እንዲጋለጡ የሚያደርግ መሆኑን ጠቁሟል፡፡

እንደነዚህ ዓይነቱን የግድብ ሥራ የሚቃወሙ ቡድኖች እንደሚሉት የታላላቅ ግድቦች የኮንስትራክሽን ወጪ ሲጀመር ከታሰበው በጀት በአማካይ ከ90 በመቶ በላይ ተጨማሪ ወጪ የሚያስከትል እንዲሁም ከአስር ግድቦች ስምንቱ ከተወሰነላቸው የመጠናቀቂያ ጊዜ እንደሚያልፉ ይናገራሉ፡፡ በመሆኑን በኢትዮጵያና በብራዚል የሚገነቡት ግድቦች የፓኪስታንንና የምያንማርን (በርማ) ጨምሮ “ከፍተኛ ወጪ እንዲሁም ከመመጠናቀቂያ ጊዜያቸው በማለፍ የአገራቱን የኢኮኖሚ ገጽታ ችግር ውስጥ” እንደሚከቱ ዘገባው ያስረዳል፡፡

ጥናቱን ያቀረቡት ምሁራን እንደሚሉት ግድብ መሥራት አስፈላጊና እነርሱም በዚህ ጉዳይ ላይ ተቃዋሚ አለመሆናቸውን በአጽዕኖት ተናግረዋል፡፡ ችግሩ ያለው ታዳጊ አገራቱ ካላቸው የኢኮኖሚ ሁኔታ አኳያ በእንደዚህ ዓይነት የታላላቅ ግድብ ሥራ ላይ መጠመዳቸው ወደፊት ግድቦቹ በሥራ ላይ ሲውሉ ከሚጠይቁት ከፍተኛ ወጪና አገራቱ ግድቦቹን ለማንቀሳቀስ ከሚጠፈለግባቸው ከፍተኛ የፋይናንስ ጥያቄና ብቃት ማነስ አኳያ ሁኔታው እጅግ አሳሳቢ መሆኑን በመዘርዘር አስረድተዋል፡፡ “በመሆኑም” ይላሉ ከምሁራኖቹ አንዱ “በመሆኑም ይህንን ሁሉ ሁኔታ አንድ ላይ ስንወስደው ግድቦቹን መገንባት ስሜት የሚሰጥ አይደለም፡፡”

እንዲህ ያለው መረጃና ማስጠንቀቂያ ይፋ ቢሆንም የግድቦቹን መሠራት የሚደግፉ ወገኖች ቀድሞ የተሠሩ ስህተቶች እንዳይደገሙ አድርገን ነው የምንገነባው በማለት ለሚቀርበው ማስረጃ መከላከያ ይሰጣሉ፡፡ ሆኖም የኦክስፎር ዩኒቨርሲቲ ዘገባ የበርካታ ዓመታት መረጃ በመውሰድ ያወጣው ዘገባ ላይ እንዳመለከተው የግድቦቹን ሥራ ለማጠናቀቅ፣ ከተሰሩም በኋላ ለጥገናና ግድቦቹ በሥራ ላይ እንዲቆዩ ለማካሄድ የሚወጣው ወጪ ባለፉት በርካታ ዓመታት እየጨመረ እንጂ እየቀነሰ እንዳልመጣ ያስረዳል፡፡ በጥናቱ ላይ የተሳተፉ ሌላው ምሁር ሲናገሩ “እነዚህ ኢኮኖሚያችን እያደገ ነው የሚሉ አገራት በእርግጥ ለዜጎቻቸው ዋስትና ግድ የሚላቸው ከሆነ ገንዘባቸውን ከታላላቅ ግድብ ሥራ ይልቅ በሌላ (ሰብዓዊ) ተግባር ላይ ቢያውሉት ይሻላል” ብለዋል፡፡

ዓለምአቀፉ የሰብዓዊ መብት ድርጅት የኦሞ ወንዝን ተከትሎ በሚገነባው ግድብ ላይ ስለተፈናቀሉት ዜጎች በቅርቡ ባወጣው በሳተላይት ፎቶ በተደገፈ ማስረጃ መሠረት በኢትዮጵያና በኬኒያ የኦሞን ወንዝ ተከትለው የሚኖሩ እስከ ግማሽ ሚሊዮን የሚደርሱ የአካባቢው ነዋሪዎች በግድቡ ሥራ ምክንያት የመኖር ኅልውናቸው ያከተመ መሆኑን ዘግቦ ነበር፡፡ ሰሞኑን የኢህአዴግ ባለሥልጣናት (ከግብርና ሚ/ር) በኢህአዴግ ፓርላማ ሲጠየቁ በሰጡት ቃል አንዳችም የተፈናቀለ ሰው የለም በማለት የመለሱ ሲሆን በተደጋጋሚ ማስረጃ ተደግፎ የሚወጣውን መረጃ አጣጥለውታል፡፡ (ፎቶ: AP)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. unity says

    March 12, 2014 08:01 am at 8:01 am

    westerners are evil people..especially on Ethiopian issue..nothing will stop us from constructing of our dam.

    Reply
  2. Tadesse says

    March 14, 2014 09:29 am at 9:29 am

    Funny!! But, the study should have told us how did the westerners pass this stage of development. May be the study has some flaws. Please, check again.

    Reply
  3. gomoraw says

    March 14, 2014 11:37 am at 11:37 am

    I could not find any scientific explanation form the report. It may be opinion of the writer. But what i can tell you is we can not stop building the GERD even if it is as you say.

    Reply
    • truth says

      March 15, 2014 12:42 pm at 12:42 pm

      have no time to think about stopping

      Reply
  4. solomon says

    March 19, 2014 02:18 am at 2:18 am

    i dont undestand the benifit the writer got from these rubish article este we de agerachu gebetachu tagelu be selamawi menged erero becha

    Reply
  5. tadesse Molla says

    March 24, 2014 09:52 am at 9:52 am

    Are you sure that you belong to an Ethiopia? Off course, I don’t think that you are responsible to this country .We need to contribute our resources, if need be , give our lives for the sake of beloved country.This never will be the headache of Europeans and YOU.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule