• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“በኢትዮጵያ የዘር የበላይነት ሳይሆን የሕግ የበላይነት ሊኖር ይገባል” ኦባንግ ሜቶ አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ

December 23, 2018 07:43 pm by Editor 1 Comment

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ተቻችለው ለሀገራቸው ሰላምና አንድነት የበኩላቸውን እንዲወጡ የአዲስቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ዳይሬክተርና የሰብአዊ መብት ተሟጋች የሆኑት አቶ ኦባንግ ሜቶ ጠየቁ።

አቶ ኦባንግ ሜቶ በሀገራዊ  አንድነት ፣ ሰላምና መቻቻል ዙሪያ ትላንት ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ጋር ተወያይተዋል።

“በሀገራችን  በአሁኑ ጊዜ እየተስተዋለ ያለው ግጭት ባለፉት 27 ዓመታት ለኢትዮጵያዊ አንድነት ትኩረት አለመስጠታችን ነው፣ ይህ ደግሞ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚገኙ የነገይቱ ባለራዕዮችን እየተፈታተነ ይገኛል” ሲሉ ገልጸዋል።

ወደዚህች ምድር ብሔርን ምርጫ አድርጎ የመጣ ማንም እንደሌላ የተናገሩት አቶ ኦባንግ ሰው ማየት የሚገባው ሰው  መሆኑ እንጂ በዘርና በብሔር መሆን እንደማገባም አመልክተዋል።

በሀገሪቱ የህግ የበላይነት እንጂ የዘር የበላይነት ሊኖር እንደማይገባ ጠቁመው ኢትዮጵያ እንድትለወጥ እያንዳንዱ ዜጋ ከብሔር አመለካከት ነፃ መሆን እንዳለበት አስረድተዋል።

“በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚገኙ ተማሪዎች የኢትዮጵያ እንጂ ተዋጽኦ አይደሉም፣ ደግሞ አንዳችን ያለአንዳችን መኖር አንችልም ስለዚህ ተማሪዎች የጥላቻ ሳይሆን የአንድነት ነፀብራቅ ልሆኑ ያገባቸዋል” ብለዋል።

በሀገሪቱ የተለያዩ ግጭቶች ቢኖሩም የዴሞክራሲ መሠረት እየተጣለ መሆኑን የገለጹት አቶ ኦባንግ የተፈጠረው በነፃነት የመናገር ዕድል  በመጠቀም ለሀገሪቱ አንድነት፣ ለሰላምና መቻቻል ሞጋቾች እንዲሆኑ ጠይቀዋል።

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ዳምጠው ዳርዛ በበኩላቸው ኢትዮጵያ የበርካታ ብሄር ብሄረሰቦች ባለቤት እንደመሆኗ ባለፉት ጊዜያት በአንድነት ሳይሆን በልዩነት ላይ ትኩረት ሲደረግ መቆየቱን ገልጸዋል።

“ቀደምት አባቶቻችን በአንድነት ወግ ያደጉ በመሆናቸው የተለያዩ የሀገራችን ፈተናዎችን በድል ተወጥተው ለእኛ አስረክበዋል” ብለዋል።

ወደ ቀድሞ የአንድነት ታሪክ ለመመለስ የመሪነት ሚና መጫወት ያለባቸው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ማህበረሰብ መሆናችንን መዘንጋት እንደሌለባቸውም አመልክተዋል።

“ብሔራዊ መግባባትና አንድነት ላይ ባለመሠራቱ በክልል የታጠሩ ነፃ አዉጪ የፖለቲካ ድርጅቶች እየተፈጠሩ እንጂ ብሔራዊ አመለካከት ያላቸው ጥቂቶች ናቸው” ያለው ደግሞ በዩኒቨርስቲው የፕሮዳክሽን ምህንድስና የመጀመሪያ ዓመት ተማሪ ግሩም አጅሬ ነው።

ተማሪ ግሩም እንዳለው የዘር ፖለቲካ ባመጣው ጠባብ አመለካከት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ተቻችሎ ለመኖር እየከበዳቸው ይገኛል።

በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ላይ ስለ ኢትዮጵያ አንድነት፣ ሰላምና መቻቻል አቶ ኦባንግ ገለፃ መስጠታቸው ራሱን እንዲያገኝ ያስቻለው መሆኑን ተናግሯል።

የኤሌክትሮኒክስ ምህንድስና የአራተኛ ዓመት ተማሪ ሪሐና ኑሩ በበኩሏ “ሀገራችን በዘርና በብሔር በሽታ የታመመችው ከእኛ የተነሳ ነው” ብላለች።

ሆኖም አቶ ኦባንግ በአንድነትና ሰላም ዙሪያ ያደረጉት ገለጻ በካምፓስ ህይወታችን አንድነት በመፍጠር ተባብረው ለመኖር እንደሚያግዝ ተናግራለች።

ምንጭ፦ ኢዜአ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Belayneh sergoalem says

    January 13, 2019 03:33 pm at 3:33 pm

    I am what I have said justice ,justice ,justice before everything , everything with out justice is nothing !!!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule