• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ባቡር ይሄድበታል”

October 24, 2015 01:05 am by Editor Leave a Comment

አቶ ማሞ፣ የዘመናይና የእስከዳር አባት፣ የወ/ሮ ከልካይ ባለቤት፣ አንድ ወፍጮ ቤት አላቸው። እህልም ይነግዳሉ። ጤፍ፣ ስንዴ፣ ገብስ እዚያው ገዝተው እዚያው የሚያስፈጩ ደምበኞች ሞልተዋል። አቶ ማሞ በሰፈሩ ተወዳጅ ናቸው። ተወዳጅ ያደረጋቸው ደግሞ ምርቃታቸው ነው። ምርቃቶቹ በቄንጥ የተደረደሩ ቃላት ሳይሆኑ 50 ኪሎ ጤፍ ላይ ሁለት ወይም ሶስት ኪሎ መጨመራቸው ነው።

“እጅ አጠረኝ …” ላለ ጎረቤት ደግሞ መልሳቸው፤

“ምን ችግር አለ! ሲያገኙ ይከፍላሉ …” ነው። የተበጠሰ ቺንጋ እየቀየሩ፤ መፋቂያ የተሰኩባቸውን ጉራማይሌ ጥርሶቻቸውን በፈገግታ ብልጭ እያደረጉ።

አቶ ማሞ ሃብታም አይደሉም። ድሃም አይደሉም። የሚያገኙት ቤተሰባቸውን ለማስተዳደር ይበቃቸዋል። ያቶ ማሞ መኖሪያ ቤትና ወፍጮ ቤት የተያያዘ ነው። አጥር ነው የሚለየው። ሌሊት ወፍጮ ቤቱ ሲዘጋ እንዳይላሉ የሚባለው፤ ቀኑን ሙሉ ታሥሮ የሚውለው ውሻቸው፤ ከመኖሪያ ግቢያቸው ይለቀቅና የወፍጮ ቤቱ በረንዳ ላይ ተኝቶ ሲጠብቅ ያድራል።

የሰፈሩን አቧራ ነፋስ በሚያቦንበት አንድ ሾዳዳ ቀን አቶ ማሞ ደብዳቤ ደረሳቸው። ትዕዛዙ የተንዛዛ መግቢያ አለው። መደምደሚያው ግን አጭር ነው።

“መኖሪያ ቤትዎን ለቀው እንዲወጡ እናሳስባለን። በወፍጮ ቤቱ ውስጥ ያለውን፤ ማንኛውንም ተንቀሳቃሽም ሆነ የማይንቀሳቀስ ንብረት በተጠቀሰው ቀንና ሰዓት እንዲያወጡና ወደ ሚዘጋጅሎት ሥፍራ እንዲያዛውሩ በጥብቅ እናሳስባለን። መኖሪያ ቤትዎና ወፍጮ ቤቱ የሚይዙትን ሥፍራ የባቡር ሃዲድ ይዘረጋበታል፤ ባቡርም ይሄድበታልና።”

የሚዘጋጅላቸው ሥፍራ መቼ እና የት እንደሆነ አልተጠቀሰም ነበር። ከደብዳቤው ግርጌ ፊርማ አለ። ከፊርማው ግርጌ፣

“ልማትና እድገት እንደ ሰደድ እሳት ናቸው። የሚገታቸው ሃይል የለም!” የሚል ይነበባል።

ከጥቂት ወራት በኋላ ያቶ ማሞ የመኖሪያ ቤትና ወፍጮ ቤት ላይ ግሬደር ሄደበት። ሃዲዱ ሲዘረጋና ባቡር ሲሄድበት ሳይታይ ግን አምሥት አመታት አለፉ። ሃዲዱ በሌላ መሥመር ተዘረጋ። በቻይናዊ የሚነዳም ባቡር ይሄድበት ጀመር።

ዛሬ እንዳይላሉ ግሬደር ያፈረሰው ቦታ፤ ድሮ ወፍጮ ቤት ቆሞበት የነበረው ሥፍራ፤ እየሄደ ያድራል። ቀኑን ሰፈር ውስጥ ሲዞር ውሎ። ወ/ሮ ከልካይ በየሃብታሙ ቤት እየሄዱ እንጀራ ይጋግራሉ። ዘመናይና እስከዳር ቦሌ አካባቢ ዘመናዊ ካፌዎች ውስጥ ያስተናግዳሉ። አቶ ማሞ ደግሞ ቻይናዊ የሚነዳውን ባቡር እያዩ ብቻቸውን ሲያወሩ ይውላሉ።

“ልማትና እድገት እንደ ሰደድ እሳት ናቸው። ይፋጃሉ!” ያሾፋሉ። “እኔና የምንሊክ ሃውልት የትም ወድቀን መቅረታችን ነው?” ያክሉበታል።


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm
  • “ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንግቤ እዋጋለሁ” የሚሉ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል – የመከላከያ ሠራዊት August 1, 2023 09:25 am
  • ደቡብ አፍሪካ የመሸጉ ወንጀለኞች ለሕግ ተላልፈው ሊሰጡ ነው July 31, 2023 09:27 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule