• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ባቡር ይሄድበታል”

October 24, 2015 01:05 am by Editor Leave a Comment

አቶ ማሞ፣ የዘመናይና የእስከዳር አባት፣ የወ/ሮ ከልካይ ባለቤት፣ አንድ ወፍጮ ቤት አላቸው። እህልም ይነግዳሉ። ጤፍ፣ ስንዴ፣ ገብስ እዚያው ገዝተው እዚያው የሚያስፈጩ ደምበኞች ሞልተዋል። አቶ ማሞ በሰፈሩ ተወዳጅ ናቸው። ተወዳጅ ያደረጋቸው ደግሞ ምርቃታቸው ነው። ምርቃቶቹ በቄንጥ የተደረደሩ ቃላት ሳይሆኑ 50 ኪሎ ጤፍ ላይ ሁለት ወይም ሶስት ኪሎ መጨመራቸው ነው።

“እጅ አጠረኝ …” ላለ ጎረቤት ደግሞ መልሳቸው፤

“ምን ችግር አለ! ሲያገኙ ይከፍላሉ …” ነው። የተበጠሰ ቺንጋ እየቀየሩ፤ መፋቂያ የተሰኩባቸውን ጉራማይሌ ጥርሶቻቸውን በፈገግታ ብልጭ እያደረጉ።

አቶ ማሞ ሃብታም አይደሉም። ድሃም አይደሉም። የሚያገኙት ቤተሰባቸውን ለማስተዳደር ይበቃቸዋል። ያቶ ማሞ መኖሪያ ቤትና ወፍጮ ቤት የተያያዘ ነው። አጥር ነው የሚለየው። ሌሊት ወፍጮ ቤቱ ሲዘጋ እንዳይላሉ የሚባለው፤ ቀኑን ሙሉ ታሥሮ የሚውለው ውሻቸው፤ ከመኖሪያ ግቢያቸው ይለቀቅና የወፍጮ ቤቱ በረንዳ ላይ ተኝቶ ሲጠብቅ ያድራል።

የሰፈሩን አቧራ ነፋስ በሚያቦንበት አንድ ሾዳዳ ቀን አቶ ማሞ ደብዳቤ ደረሳቸው። ትዕዛዙ የተንዛዛ መግቢያ አለው። መደምደሚያው ግን አጭር ነው።

“መኖሪያ ቤትዎን ለቀው እንዲወጡ እናሳስባለን። በወፍጮ ቤቱ ውስጥ ያለውን፤ ማንኛውንም ተንቀሳቃሽም ሆነ የማይንቀሳቀስ ንብረት በተጠቀሰው ቀንና ሰዓት እንዲያወጡና ወደ ሚዘጋጅሎት ሥፍራ እንዲያዛውሩ በጥብቅ እናሳስባለን። መኖሪያ ቤትዎና ወፍጮ ቤቱ የሚይዙትን ሥፍራ የባቡር ሃዲድ ይዘረጋበታል፤ ባቡርም ይሄድበታልና።”

የሚዘጋጅላቸው ሥፍራ መቼ እና የት እንደሆነ አልተጠቀሰም ነበር። ከደብዳቤው ግርጌ ፊርማ አለ። ከፊርማው ግርጌ፣

“ልማትና እድገት እንደ ሰደድ እሳት ናቸው። የሚገታቸው ሃይል የለም!” የሚል ይነበባል።

ከጥቂት ወራት በኋላ ያቶ ማሞ የመኖሪያ ቤትና ወፍጮ ቤት ላይ ግሬደር ሄደበት። ሃዲዱ ሲዘረጋና ባቡር ሲሄድበት ሳይታይ ግን አምሥት አመታት አለፉ። ሃዲዱ በሌላ መሥመር ተዘረጋ። በቻይናዊ የሚነዳም ባቡር ይሄድበት ጀመር።

ዛሬ እንዳይላሉ ግሬደር ያፈረሰው ቦታ፤ ድሮ ወፍጮ ቤት ቆሞበት የነበረው ሥፍራ፤ እየሄደ ያድራል። ቀኑን ሰፈር ውስጥ ሲዞር ውሎ። ወ/ሮ ከልካይ በየሃብታሙ ቤት እየሄዱ እንጀራ ይጋግራሉ። ዘመናይና እስከዳር ቦሌ አካባቢ ዘመናዊ ካፌዎች ውስጥ ያስተናግዳሉ። አቶ ማሞ ደግሞ ቻይናዊ የሚነዳውን ባቡር እያዩ ብቻቸውን ሲያወሩ ይውላሉ።

“ልማትና እድገት እንደ ሰደድ እሳት ናቸው። ይፋጃሉ!” ያሾፋሉ። “እኔና የምንሊክ ሃውልት የትም ወድቀን መቅረታችን ነው?” ያክሉበታል።


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ኢትዮጵያ ጨምሮ የቀይ ባሕር ሀገራት ቀጣናዊ ስጋቶች በመጨመራቸው የባሕር ትብብር ለማጠናከር ወሰኑ August 28, 2026 11:32 am
  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
Copyright © 2026 · Goolgule