• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሞረሽ የአቋም መግለጫ

December 10, 2015 01:11 am by Editor Leave a Comment

እኛ የሞረሽ ወገኔ ዐማራ ድርጅት ማዕከላዊ ምክር ቤት አባላት እሑድ ኅዳር ፳፮ ቀን ፪ሺህ፰ ዓ.ም. (Sunday December 6, 2015) ባደረግነው የማዕከላዊ ምክር ቤቱ ሰባተኛ መደበኛ ስብሰባ ፣ በማዕከላዊ ምክር ቤቱ ስድስተኛ መደበኛ ስብሰባ በጸደቁት የ፮(ስድስት) ወራት የሥራ ዕቅዶች አፈጻጸም ምዘና ሪፖርት፣ በድርጅቱ የቁጥጥርና ፍተሻ የአካላትና የአባላት የሥራ እንቅስቃሴና የገንዘብ አሰባሰብና አጠቃቀም ሪፖርት በአንክሮ አዳምጠን አስፈላጊውን ውይይት በማድረግ ሪፖርቶቹ ከምክር ቤቱ አባሎች የቀረቡትን ገንቢ ሀሳቦችን አካትቶ የድርጅቱ ቋሚ ሰነድ እንዲሆን በሙሉ ድምፅ ወስነናል።

ከሁሉም በላይ በዚህ መደበኛ ስብሰባ ምክር ቤቱ አጽንዖት ሰጥቶ ሠፊ ጊዜ ወስዶ የተወያየበት «የድርጅቱን ዓላማና ተልዕኮ በተሻለ መንገድ እንዴት ማከናወን ይቻላል?» ለሚለው ጥያቄ ተገቢና ሁነኛ መልስ ለማግኘት ነበር። በተደረገው ውይይት ከአባላቱ የተለያዩ አስተያየቶች ተሰጥተዋል። በውይይቱ ሚዛን ደፍቶ የቀረበው ኃሣብ ዐማራው ከተከፈተበት የዘር ማጥፋትና የዘር ማጽዳት ዘመቻ ራሱን ተከላክሎ ዘሩን ማትረፍ የሚችለው፣ ሲነቃ፣ ሲደራጅ እና ሲታጠቅ እንደሆነ ምክር ቤቱ አምኗል። ራሱን መከላከል ያልቻለ ማኅበረሰብ ተዋራጅ፣ ተገዥ፣ ተጨቋኝና በመጨረሻም ጠፊ እንደሚሆን ከታሪክ የታየና የታወቀ ነው። ስለሆነም በዐማራው ላይ እየተደረገ ያለው መጠነ-ሠፊ ዘመቻ የሚያመለክተው ብቻ ሳይሆን፣ እየሆነ ያለው የነገዱን መጥፋት ስለሆነ፣ ሞረሽ ወገኔ ሁለንተናዊ አቅሙን አጠናክሮ ዓላማውን ከሚጋሩት ኃይሎችና ቡድኖች ጋር በመተባበር የዐማራውን ነገድ ከፈጽሞ ጥፋት የሚታደግበትን ማናቸውም ዓይነት ተገቢ ሥልት በመከተል የዐማራውን ኅልውናና ማንነት የማስጠበቅ ኃላፊነቱን በብቃት እንዲወጣ ከምንጊዜውም በላቀ ቁርጠኝነት እንዲቀሳቀስና አባላትም የተጠየቁትን ማናቸውም ዓይነት ተገቢ መስዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ መሆናቸውን በሙሉ ድምፅ ተስማምተዋል።

ማዕከላዊ ምክር ቤቱ ይህን ቁርጠኝነት በተግባር ለመግለጽ እንዲቻል የቀጣዩ እንቅስቃሴ አቅጣጫ አመላካች ከሆኑ አቋሞች ላይ ደርሷል። በዚህም መሠረት የድርጅቱ አካላት፣ አባላት እና ደጋፊዎች ለመጭዎቹ ስድስት ወሮች በሚከተሉት አቋሞች ዙሪያ ኃይላቸውን፣ ዕውቀታቸውንና ገንዘባቸውን አስተባብረው እንዲቀሳቀሱ የጋራ ውሣኔ ላይ ደርሷል።

  1. ኢትዮጵያን የሚመለከት የብዙኃን መገናኛ ተቋሞች ያሏቸው ድርጅቶችና ግለሰቦች የዐማራውን ጉዳይ በአግባቡና በሚመጥነው መልኩ እያስተናገዱት እንዳልሆነ ባለፉት ሦስት ዓመታት በተጨባጭ ለማረጋገጥ ችለናል። ይህም ዐማራው እየተፈጸመበት ያለው ግድያ፣ እስራት፣ መፈናቀል፣ ንብረት ነጠቃ፣ ግፍና በደል ዐውቆ ራሱን ከጥቃት ለመከላከል እንዳይችል መረጃ እንዳይደርሰው ያደረገ ስለሆነ፣ ዐማራው ብሦቱንና ችግሩን የሚገልጽበት የራሱ የሆነ የመገናኛ ብዙኃን እንደሚያስፈልገው ሁኔታዎች በተጨባጭ አሳይተዋል። መረጃ የማድረግ ብቃት ማረጋገጫ ከመሆኑም በላይ የኃሣብ አንድነትን ገንብቶ ድርጅታዊ ኃይል ለመሆን የሚያስችል የትግል መሣሪያ ነው። ስለሆነም ዐማራው የተጋረጠበትን የዘር ማጥፋትና የዘር ማጽዳት ዘመቻ ለመቋቋም የሚችለው ትክክለኛው መረጃ በአግባቡ ሲደርሰው ነው። ያላወቀ፣ ያልነቃና ያልተደራጀ ማኅበረሰብ ለተለያዩ ጥቃቶች ተጋላጭ መሆኑ ዕውቅ ነው። ስለሆነም ዐማራው ከተከፈተበት ሁለንተናዊ ጥቃት ራሱን መከላከል እንዲችል አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎች ሊደርሱት ይገባል። በዚህም ምክንያት ዐማራው የራሱ የሆነ አንደበት የመኖሩ ጉዳይ ምርጫ ሳይሆን ግዴታ ነው። በመሆኑም የተጀመረውን የሬዲዮ ፕሮጀክት ሥራ ለማስፈጸም የሚያስችለው ገንዘብ በአስቸኳይ ተሰባስቦ የሞረሽ ሬዲዮ በኢትዮጵያ አየር ላይ እንዲናኝ እንዲደረግ የሚፈለግብንን ሁሉ አስተዋፅዖ በትጋት ለመወጣት የየበኩላችን ጥረት እናደርጋለን።
  2. ሞረሽ ወገኔ ያነገበውን ጥልቅና ሠፊ ዓላማ እንዲሁም ተልዕኮ በአግባቡ ለመወጣት አስተማማኝ የሆነ የገቢ ምንጭ ያሻዋል። ያለገንዘብ የድርጅቱ ዓላማ የትም ሊደርስ እንደማይችል ይታወቃል። ገንዘብ የሁሉም ነገር የማድረግና የበላይነት መገለጫ ሁነኛ መሣሪያ መሆኑ ግልጽ ነው። ያለገንዘብ ምንም ነገር ማድረግ እንደማይቻል ይታወቃል። በመሆኑም ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት ከዚህ ግንዛቤ በመነሳት፣ ድርጅቱ ቋሚ የገቢ ምንጭ እንዲኖረው ባለፉት ዓመታት ከፍተኛ ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል። በዚህ ጥረቱም የቋሚ ገቢ ማስገኛ ፕሮጀክት አጥንቶ ለተግባራዊነቱ በእንቅስቃሴ ላይ ይገኛል። ስለሆነም፣ ለፕሮጀክቱ ሥራ መጀመር የሚያስፈለግውን ገንዘብ ለማሰባሰብ የተያዘው ጥረት በተፋጠነ ሁኔታ በማከናወን ፕሮጀክቱ ባስቸኳይ ሥራ ላይ እንዲውል፤ ለዚህም አካላትና አባላት የሚፈለግባቸውን እንዲወጡ የበኩላችን ጥረት ለማድረግ ቃል እንገባለን።
  3. ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት ከሚታገልላቸው ዓላማዎች አንዱ በዐማራው ነገድ ላይ የዘር ማጥፋትና የዘር ማጽዳት ወንጀል የፈጸሙ ቡድኖችና ግለሰቦችን ለፍትኅ ማቅረብ ነው። ይህን ዓላማ ተግባራዊ ለማድረግ፣ በነገዱ ላይ የተፈጸሙ ወንጀሎችን ከጥርጣሬ ውጭ በሆነ ሁኔታ፣ ለሁለተኛ እና ለሦስተኛ ወገን ማስረዳትና ማሳመን የሚችሉ ዝርዝር መረጃዎች እንዲሰበሰቡ ጥረት ተደርጓል። በዚህም መሠረት ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ የመረጃ አሰባሳቢና አጥኝ ቡድን ተቋቁሞ ባዘጋጀው ፕሮጀክት መሠረት በሁሉም የኢትዮጵያ ክፍሎች በዐማራው ላይ የተፈጸሙ የዘር ማጥፋትና የዘር ማጽዳት ወንጀሎችን በተጨባጭ የሚያረጋግጡ መረጃዎች ተሰባስበዋል። የጉባኤው ተሣታፊዎች እኒህ መረጃዎች ለተፈላጊው ግልጋሎት እንዲውሉ በአመራሩ በኩል አስፈላጊው ሁሉ እንዲደረግ በሙሉ ድምፅ ወስነናል።
  4. ድርጅቱ ወደፊት በተሳካ ሁኔታ መጓዝ የሚችለው ዕውቀት፣ መረጃ፣ ጊዜ እና ገንዘብ በበቂ መጠን ሲኖሩት ነው። የእነዚህ አስፈላጊ ጉዳዮች ብቸኛ ምንጭ ደግሞ ሰው ነው። ስለሆነም የሞረሽ ወገኔን ዓላማ ለማሳካት ቁልፉ ጉዳይ የአባላት ምልመላ ስለሆነ፤ እያንዳንዱ የምክር ቤት አባል ለሚቀጥሉት ስድስት ወሮች ተጨማሪ አባላት በመመልመል ለሰው ኃይል ማደራጃና ዝግጅት መምሪያ እንዲያሳውቅ ምክር ቤቱ ወስኗል።

ዐማራን ከፈጽሞ ጥፋት እንታደጋለን!

ፈለገ አሥራት የትውልዳችን ቃል ኪዳን ነው!

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule