• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሞረሽ የአቋም መግለጫ

December 10, 2015 01:11 am by Editor Leave a Comment

እኛ የሞረሽ ወገኔ ዐማራ ድርጅት ማዕከላዊ ምክር ቤት አባላት እሑድ ኅዳር ፳፮ ቀን ፪ሺህ፰ ዓ.ም. (Sunday December 6, 2015) ባደረግነው የማዕከላዊ ምክር ቤቱ ሰባተኛ መደበኛ ስብሰባ ፣ በማዕከላዊ ምክር ቤቱ ስድስተኛ መደበኛ ስብሰባ በጸደቁት የ፮(ስድስት) ወራት የሥራ ዕቅዶች አፈጻጸም ምዘና ሪፖርት፣ በድርጅቱ የቁጥጥርና ፍተሻ የአካላትና የአባላት የሥራ እንቅስቃሴና የገንዘብ አሰባሰብና አጠቃቀም ሪፖርት በአንክሮ አዳምጠን አስፈላጊውን ውይይት በማድረግ ሪፖርቶቹ ከምክር ቤቱ አባሎች የቀረቡትን ገንቢ ሀሳቦችን አካትቶ የድርጅቱ ቋሚ ሰነድ እንዲሆን በሙሉ ድምፅ ወስነናል።

ከሁሉም በላይ በዚህ መደበኛ ስብሰባ ምክር ቤቱ አጽንዖት ሰጥቶ ሠፊ ጊዜ ወስዶ የተወያየበት «የድርጅቱን ዓላማና ተልዕኮ በተሻለ መንገድ እንዴት ማከናወን ይቻላል?» ለሚለው ጥያቄ ተገቢና ሁነኛ መልስ ለማግኘት ነበር። በተደረገው ውይይት ከአባላቱ የተለያዩ አስተያየቶች ተሰጥተዋል። በውይይቱ ሚዛን ደፍቶ የቀረበው ኃሣብ ዐማራው ከተከፈተበት የዘር ማጥፋትና የዘር ማጽዳት ዘመቻ ራሱን ተከላክሎ ዘሩን ማትረፍ የሚችለው፣ ሲነቃ፣ ሲደራጅ እና ሲታጠቅ እንደሆነ ምክር ቤቱ አምኗል። ራሱን መከላከል ያልቻለ ማኅበረሰብ ተዋራጅ፣ ተገዥ፣ ተጨቋኝና በመጨረሻም ጠፊ እንደሚሆን ከታሪክ የታየና የታወቀ ነው። ስለሆነም በዐማራው ላይ እየተደረገ ያለው መጠነ-ሠፊ ዘመቻ የሚያመለክተው ብቻ ሳይሆን፣ እየሆነ ያለው የነገዱን መጥፋት ስለሆነ፣ ሞረሽ ወገኔ ሁለንተናዊ አቅሙን አጠናክሮ ዓላማውን ከሚጋሩት ኃይሎችና ቡድኖች ጋር በመተባበር የዐማራውን ነገድ ከፈጽሞ ጥፋት የሚታደግበትን ማናቸውም ዓይነት ተገቢ ሥልት በመከተል የዐማራውን ኅልውናና ማንነት የማስጠበቅ ኃላፊነቱን በብቃት እንዲወጣ ከምንጊዜውም በላቀ ቁርጠኝነት እንዲቀሳቀስና አባላትም የተጠየቁትን ማናቸውም ዓይነት ተገቢ መስዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ መሆናቸውን በሙሉ ድምፅ ተስማምተዋል።

ማዕከላዊ ምክር ቤቱ ይህን ቁርጠኝነት በተግባር ለመግለጽ እንዲቻል የቀጣዩ እንቅስቃሴ አቅጣጫ አመላካች ከሆኑ አቋሞች ላይ ደርሷል። በዚህም መሠረት የድርጅቱ አካላት፣ አባላት እና ደጋፊዎች ለመጭዎቹ ስድስት ወሮች በሚከተሉት አቋሞች ዙሪያ ኃይላቸውን፣ ዕውቀታቸውንና ገንዘባቸውን አስተባብረው እንዲቀሳቀሱ የጋራ ውሣኔ ላይ ደርሷል።

  1. ኢትዮጵያን የሚመለከት የብዙኃን መገናኛ ተቋሞች ያሏቸው ድርጅቶችና ግለሰቦች የዐማራውን ጉዳይ በአግባቡና በሚመጥነው መልኩ እያስተናገዱት እንዳልሆነ ባለፉት ሦስት ዓመታት በተጨባጭ ለማረጋገጥ ችለናል። ይህም ዐማራው እየተፈጸመበት ያለው ግድያ፣ እስራት፣ መፈናቀል፣ ንብረት ነጠቃ፣ ግፍና በደል ዐውቆ ራሱን ከጥቃት ለመከላከል እንዳይችል መረጃ እንዳይደርሰው ያደረገ ስለሆነ፣ ዐማራው ብሦቱንና ችግሩን የሚገልጽበት የራሱ የሆነ የመገናኛ ብዙኃን እንደሚያስፈልገው ሁኔታዎች በተጨባጭ አሳይተዋል። መረጃ የማድረግ ብቃት ማረጋገጫ ከመሆኑም በላይ የኃሣብ አንድነትን ገንብቶ ድርጅታዊ ኃይል ለመሆን የሚያስችል የትግል መሣሪያ ነው። ስለሆነም ዐማራው የተጋረጠበትን የዘር ማጥፋትና የዘር ማጽዳት ዘመቻ ለመቋቋም የሚችለው ትክክለኛው መረጃ በአግባቡ ሲደርሰው ነው። ያላወቀ፣ ያልነቃና ያልተደራጀ ማኅበረሰብ ለተለያዩ ጥቃቶች ተጋላጭ መሆኑ ዕውቅ ነው። ስለሆነም ዐማራው ከተከፈተበት ሁለንተናዊ ጥቃት ራሱን መከላከል እንዲችል አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎች ሊደርሱት ይገባል። በዚህም ምክንያት ዐማራው የራሱ የሆነ አንደበት የመኖሩ ጉዳይ ምርጫ ሳይሆን ግዴታ ነው። በመሆኑም የተጀመረውን የሬዲዮ ፕሮጀክት ሥራ ለማስፈጸም የሚያስችለው ገንዘብ በአስቸኳይ ተሰባስቦ የሞረሽ ሬዲዮ በኢትዮጵያ አየር ላይ እንዲናኝ እንዲደረግ የሚፈለግብንን ሁሉ አስተዋፅዖ በትጋት ለመወጣት የየበኩላችን ጥረት እናደርጋለን።
  2. ሞረሽ ወገኔ ያነገበውን ጥልቅና ሠፊ ዓላማ እንዲሁም ተልዕኮ በአግባቡ ለመወጣት አስተማማኝ የሆነ የገቢ ምንጭ ያሻዋል። ያለገንዘብ የድርጅቱ ዓላማ የትም ሊደርስ እንደማይችል ይታወቃል። ገንዘብ የሁሉም ነገር የማድረግና የበላይነት መገለጫ ሁነኛ መሣሪያ መሆኑ ግልጽ ነው። ያለገንዘብ ምንም ነገር ማድረግ እንደማይቻል ይታወቃል። በመሆኑም ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት ከዚህ ግንዛቤ በመነሳት፣ ድርጅቱ ቋሚ የገቢ ምንጭ እንዲኖረው ባለፉት ዓመታት ከፍተኛ ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል። በዚህ ጥረቱም የቋሚ ገቢ ማስገኛ ፕሮጀክት አጥንቶ ለተግባራዊነቱ በእንቅስቃሴ ላይ ይገኛል። ስለሆነም፣ ለፕሮጀክቱ ሥራ መጀመር የሚያስፈለግውን ገንዘብ ለማሰባሰብ የተያዘው ጥረት በተፋጠነ ሁኔታ በማከናወን ፕሮጀክቱ ባስቸኳይ ሥራ ላይ እንዲውል፤ ለዚህም አካላትና አባላት የሚፈለግባቸውን እንዲወጡ የበኩላችን ጥረት ለማድረግ ቃል እንገባለን።
  3. ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት ከሚታገልላቸው ዓላማዎች አንዱ በዐማራው ነገድ ላይ የዘር ማጥፋትና የዘር ማጽዳት ወንጀል የፈጸሙ ቡድኖችና ግለሰቦችን ለፍትኅ ማቅረብ ነው። ይህን ዓላማ ተግባራዊ ለማድረግ፣ በነገዱ ላይ የተፈጸሙ ወንጀሎችን ከጥርጣሬ ውጭ በሆነ ሁኔታ፣ ለሁለተኛ እና ለሦስተኛ ወገን ማስረዳትና ማሳመን የሚችሉ ዝርዝር መረጃዎች እንዲሰበሰቡ ጥረት ተደርጓል። በዚህም መሠረት ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ የመረጃ አሰባሳቢና አጥኝ ቡድን ተቋቁሞ ባዘጋጀው ፕሮጀክት መሠረት በሁሉም የኢትዮጵያ ክፍሎች በዐማራው ላይ የተፈጸሙ የዘር ማጥፋትና የዘር ማጽዳት ወንጀሎችን በተጨባጭ የሚያረጋግጡ መረጃዎች ተሰባስበዋል። የጉባኤው ተሣታፊዎች እኒህ መረጃዎች ለተፈላጊው ግልጋሎት እንዲውሉ በአመራሩ በኩል አስፈላጊው ሁሉ እንዲደረግ በሙሉ ድምፅ ወስነናል።
  4. ድርጅቱ ወደፊት በተሳካ ሁኔታ መጓዝ የሚችለው ዕውቀት፣ መረጃ፣ ጊዜ እና ገንዘብ በበቂ መጠን ሲኖሩት ነው። የእነዚህ አስፈላጊ ጉዳዮች ብቸኛ ምንጭ ደግሞ ሰው ነው። ስለሆነም የሞረሽ ወገኔን ዓላማ ለማሳካት ቁልፉ ጉዳይ የአባላት ምልመላ ስለሆነ፤ እያንዳንዱ የምክር ቤት አባል ለሚቀጥሉት ስድስት ወሮች ተጨማሪ አባላት በመመልመል ለሰው ኃይል ማደራጃና ዝግጅት መምሪያ እንዲያሳውቅ ምክር ቤቱ ወስኗል።

ዐማራን ከፈጽሞ ጥፋት እንታደጋለን!

ፈለገ አሥራት የትውልዳችን ቃል ኪዳን ነው!

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule