• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሞረሽ የአቋም መግለጫ

December 10, 2015 01:11 am by Editor Leave a Comment

እኛ የሞረሽ ወገኔ ዐማራ ድርጅት ማዕከላዊ ምክር ቤት አባላት እሑድ ኅዳር ፳፮ ቀን ፪ሺህ፰ ዓ.ም. (Sunday December 6, 2015) ባደረግነው የማዕከላዊ ምክር ቤቱ ሰባተኛ መደበኛ ስብሰባ ፣ በማዕከላዊ ምክር ቤቱ ስድስተኛ መደበኛ ስብሰባ በጸደቁት የ፮(ስድስት) ወራት የሥራ ዕቅዶች አፈጻጸም ምዘና ሪፖርት፣ በድርጅቱ የቁጥጥርና ፍተሻ የአካላትና የአባላት የሥራ እንቅስቃሴና የገንዘብ አሰባሰብና አጠቃቀም ሪፖርት በአንክሮ አዳምጠን አስፈላጊውን ውይይት በማድረግ ሪፖርቶቹ ከምክር ቤቱ አባሎች የቀረቡትን ገንቢ ሀሳቦችን አካትቶ የድርጅቱ ቋሚ ሰነድ እንዲሆን በሙሉ ድምፅ ወስነናል።

ከሁሉም በላይ በዚህ መደበኛ ስብሰባ ምክር ቤቱ አጽንዖት ሰጥቶ ሠፊ ጊዜ ወስዶ የተወያየበት «የድርጅቱን ዓላማና ተልዕኮ በተሻለ መንገድ እንዴት ማከናወን ይቻላል?» ለሚለው ጥያቄ ተገቢና ሁነኛ መልስ ለማግኘት ነበር። በተደረገው ውይይት ከአባላቱ የተለያዩ አስተያየቶች ተሰጥተዋል። በውይይቱ ሚዛን ደፍቶ የቀረበው ኃሣብ ዐማራው ከተከፈተበት የዘር ማጥፋትና የዘር ማጽዳት ዘመቻ ራሱን ተከላክሎ ዘሩን ማትረፍ የሚችለው፣ ሲነቃ፣ ሲደራጅ እና ሲታጠቅ እንደሆነ ምክር ቤቱ አምኗል። ራሱን መከላከል ያልቻለ ማኅበረሰብ ተዋራጅ፣ ተገዥ፣ ተጨቋኝና በመጨረሻም ጠፊ እንደሚሆን ከታሪክ የታየና የታወቀ ነው። ስለሆነም በዐማራው ላይ እየተደረገ ያለው መጠነ-ሠፊ ዘመቻ የሚያመለክተው ብቻ ሳይሆን፣ እየሆነ ያለው የነገዱን መጥፋት ስለሆነ፣ ሞረሽ ወገኔ ሁለንተናዊ አቅሙን አጠናክሮ ዓላማውን ከሚጋሩት ኃይሎችና ቡድኖች ጋር በመተባበር የዐማራውን ነገድ ከፈጽሞ ጥፋት የሚታደግበትን ማናቸውም ዓይነት ተገቢ ሥልት በመከተል የዐማራውን ኅልውናና ማንነት የማስጠበቅ ኃላፊነቱን በብቃት እንዲወጣ ከምንጊዜውም በላቀ ቁርጠኝነት እንዲቀሳቀስና አባላትም የተጠየቁትን ማናቸውም ዓይነት ተገቢ መስዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ መሆናቸውን በሙሉ ድምፅ ተስማምተዋል።

ማዕከላዊ ምክር ቤቱ ይህን ቁርጠኝነት በተግባር ለመግለጽ እንዲቻል የቀጣዩ እንቅስቃሴ አቅጣጫ አመላካች ከሆኑ አቋሞች ላይ ደርሷል። በዚህም መሠረት የድርጅቱ አካላት፣ አባላት እና ደጋፊዎች ለመጭዎቹ ስድስት ወሮች በሚከተሉት አቋሞች ዙሪያ ኃይላቸውን፣ ዕውቀታቸውንና ገንዘባቸውን አስተባብረው እንዲቀሳቀሱ የጋራ ውሣኔ ላይ ደርሷል።

  1. ኢትዮጵያን የሚመለከት የብዙኃን መገናኛ ተቋሞች ያሏቸው ድርጅቶችና ግለሰቦች የዐማራውን ጉዳይ በአግባቡና በሚመጥነው መልኩ እያስተናገዱት እንዳልሆነ ባለፉት ሦስት ዓመታት በተጨባጭ ለማረጋገጥ ችለናል። ይህም ዐማራው እየተፈጸመበት ያለው ግድያ፣ እስራት፣ መፈናቀል፣ ንብረት ነጠቃ፣ ግፍና በደል ዐውቆ ራሱን ከጥቃት ለመከላከል እንዳይችል መረጃ እንዳይደርሰው ያደረገ ስለሆነ፣ ዐማራው ብሦቱንና ችግሩን የሚገልጽበት የራሱ የሆነ የመገናኛ ብዙኃን እንደሚያስፈልገው ሁኔታዎች በተጨባጭ አሳይተዋል። መረጃ የማድረግ ብቃት ማረጋገጫ ከመሆኑም በላይ የኃሣብ አንድነትን ገንብቶ ድርጅታዊ ኃይል ለመሆን የሚያስችል የትግል መሣሪያ ነው። ስለሆነም ዐማራው የተጋረጠበትን የዘር ማጥፋትና የዘር ማጽዳት ዘመቻ ለመቋቋም የሚችለው ትክክለኛው መረጃ በአግባቡ ሲደርሰው ነው። ያላወቀ፣ ያልነቃና ያልተደራጀ ማኅበረሰብ ለተለያዩ ጥቃቶች ተጋላጭ መሆኑ ዕውቅ ነው። ስለሆነም ዐማራው ከተከፈተበት ሁለንተናዊ ጥቃት ራሱን መከላከል እንዲችል አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎች ሊደርሱት ይገባል። በዚህም ምክንያት ዐማራው የራሱ የሆነ አንደበት የመኖሩ ጉዳይ ምርጫ ሳይሆን ግዴታ ነው። በመሆኑም የተጀመረውን የሬዲዮ ፕሮጀክት ሥራ ለማስፈጸም የሚያስችለው ገንዘብ በአስቸኳይ ተሰባስቦ የሞረሽ ሬዲዮ በኢትዮጵያ አየር ላይ እንዲናኝ እንዲደረግ የሚፈለግብንን ሁሉ አስተዋፅዖ በትጋት ለመወጣት የየበኩላችን ጥረት እናደርጋለን።
  2. ሞረሽ ወገኔ ያነገበውን ጥልቅና ሠፊ ዓላማ እንዲሁም ተልዕኮ በአግባቡ ለመወጣት አስተማማኝ የሆነ የገቢ ምንጭ ያሻዋል። ያለገንዘብ የድርጅቱ ዓላማ የትም ሊደርስ እንደማይችል ይታወቃል። ገንዘብ የሁሉም ነገር የማድረግና የበላይነት መገለጫ ሁነኛ መሣሪያ መሆኑ ግልጽ ነው። ያለገንዘብ ምንም ነገር ማድረግ እንደማይቻል ይታወቃል። በመሆኑም ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት ከዚህ ግንዛቤ በመነሳት፣ ድርጅቱ ቋሚ የገቢ ምንጭ እንዲኖረው ባለፉት ዓመታት ከፍተኛ ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል። በዚህ ጥረቱም የቋሚ ገቢ ማስገኛ ፕሮጀክት አጥንቶ ለተግባራዊነቱ በእንቅስቃሴ ላይ ይገኛል። ስለሆነም፣ ለፕሮጀክቱ ሥራ መጀመር የሚያስፈለግውን ገንዘብ ለማሰባሰብ የተያዘው ጥረት በተፋጠነ ሁኔታ በማከናወን ፕሮጀክቱ ባስቸኳይ ሥራ ላይ እንዲውል፤ ለዚህም አካላትና አባላት የሚፈለግባቸውን እንዲወጡ የበኩላችን ጥረት ለማድረግ ቃል እንገባለን።
  3. ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት ከሚታገልላቸው ዓላማዎች አንዱ በዐማራው ነገድ ላይ የዘር ማጥፋትና የዘር ማጽዳት ወንጀል የፈጸሙ ቡድኖችና ግለሰቦችን ለፍትኅ ማቅረብ ነው። ይህን ዓላማ ተግባራዊ ለማድረግ፣ በነገዱ ላይ የተፈጸሙ ወንጀሎችን ከጥርጣሬ ውጭ በሆነ ሁኔታ፣ ለሁለተኛ እና ለሦስተኛ ወገን ማስረዳትና ማሳመን የሚችሉ ዝርዝር መረጃዎች እንዲሰበሰቡ ጥረት ተደርጓል። በዚህም መሠረት ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ የመረጃ አሰባሳቢና አጥኝ ቡድን ተቋቁሞ ባዘጋጀው ፕሮጀክት መሠረት በሁሉም የኢትዮጵያ ክፍሎች በዐማራው ላይ የተፈጸሙ የዘር ማጥፋትና የዘር ማጽዳት ወንጀሎችን በተጨባጭ የሚያረጋግጡ መረጃዎች ተሰባስበዋል። የጉባኤው ተሣታፊዎች እኒህ መረጃዎች ለተፈላጊው ግልጋሎት እንዲውሉ በአመራሩ በኩል አስፈላጊው ሁሉ እንዲደረግ በሙሉ ድምፅ ወስነናል።
  4. ድርጅቱ ወደፊት በተሳካ ሁኔታ መጓዝ የሚችለው ዕውቀት፣ መረጃ፣ ጊዜ እና ገንዘብ በበቂ መጠን ሲኖሩት ነው። የእነዚህ አስፈላጊ ጉዳዮች ብቸኛ ምንጭ ደግሞ ሰው ነው። ስለሆነም የሞረሽ ወገኔን ዓላማ ለማሳካት ቁልፉ ጉዳይ የአባላት ምልመላ ስለሆነ፤ እያንዳንዱ የምክር ቤት አባል ለሚቀጥሉት ስድስት ወሮች ተጨማሪ አባላት በመመልመል ለሰው ኃይል ማደራጃና ዝግጅት መምሪያ እንዲያሳውቅ ምክር ቤቱ ወስኗል።

ዐማራን ከፈጽሞ ጥፋት እንታደጋለን!

ፈለገ አሥራት የትውልዳችን ቃል ኪዳን ነው!

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ፍፁም ብርሃኔና ታምራት የማነ በቁጥጥር ሥር ዋሉ April 16, 2021 10:06 am
  • “ለአንድ ፓርቲ የማደላ ከሆነ ሄጄ እዚያው ፓርቲ እገባለሁ” ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ April 16, 2021 08:45 am
  • “ተዋግተን አይደለም ስንተኛ ብንውል እንኳን መቀሌና አዲስ አበባ አይገቡም” ጄኔራል ባጫ April 14, 2021 09:06 am
  • የስኳር ፋብሪካዎች ተሽጠው ዕዳቸውን እንዲከፍሉ ተወሰነ April 14, 2021 08:53 am
  • “ኤርትራዊ ነን” በማለት የመኖሪያ ፈቃድ ሲቀበሉ የኖሩ የትግራይ ሰዎችን መለየት ተጀመረ April 1, 2021 02:01 am
  • ምርጫ ቦርድ የኦነግን ጥያቄ ውድቅ አደረገ April 1, 2021 01:15 am
  • “እርግጠኛ ሆኜ የምነግራችሁ መንግሥት ኮሮጆ አይሰርቅም” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ April 1, 2021 01:09 am
  • መንግሥት ካልደረሰልን አሁንም ግድያ ይኖራል – ነዋሪዎች April 1, 2021 01:04 am
  • በትግራይ ሊዘረፍ የነበረ የእርዳታ እህል ተያዘ April 1, 2021 12:39 am
  • “በኢትዮጵያ ክብርና ጥቅም ከመጣችሁ አንገቴ ይቀላል እንጂ አልደራደርም” March 24, 2021 01:22 am
  • “ከዚህ በኋላ ህወሓት ማለት በነፋስ የተበተነ ዱቄት ነው” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ March 23, 2021 11:28 pm
  • እነ ስብሃት ነጋ ጥያቄያቸው ውድቅ ሆነ March 23, 2021 10:23 pm
  • በርግጥ ኢትዮጵያ ዝናብ አዝንባለች? March 23, 2021 10:15 pm
  • አሜሪካ በሴናተሯ አማካይነት “ለቅሶ” ደረሰች March 21, 2021 08:57 pm
  • ቪኦኤ በወለጋ ሆሮ ጉድሩ ለተጨፈጨፉ ኦነግ ሸኔን ከደሙ ንጹህ አደረገ March 19, 2021 04:32 pm
  • ባልደራስና የአብን የትብብር ስምምነት ተፈራረሙ March 18, 2021 01:56 pm
  • ኤርሚያስ ለገሰ “የወያኔ የፕሮፖጋንዳ ሰራተኛ እያለ የለመደው የቁጥር ጫወታ አለቀቀውም” March 17, 2021 09:54 pm
  • በትግራይ ሰብዓዊ ድጋፍ በተቀላጠፈ ሁኔታ እየተካሄደ ነው – የተመድ የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት March 17, 2021 04:54 am
  • ምርጫ ቦርድ ከፈቀደለት ኦነግ በምርጫው እንደሚወዳደር አስታወቀ March 17, 2021 04:30 am
  • በዓለምአቀፍ ሚዲያ ዘጋቢዎች ላይ እርምጃ ሊወሰድ ነው March 15, 2021 11:25 am
  • በሲዳማ/ሀዋሳ 128 ቱርክ ሰራሽ ሽጉጥ፤ 2 መትረየስ ከ8,129 ጥይት ጋር ተያዘ March 15, 2021 10:13 am
  • የአክሱም ጅምላ ጭፍጨፋ ተብሎ የተሰራጨው ፎቶ የሐሰት ሆነ March 15, 2021 09:26 am
  • በትግራይ ትምህርት ቤቶች በቅርቡ ሥራ ይጀምራሉ March 15, 2021 09:04 am
  • በማይካድራ የጅምላ መቃብር ተገኘ፤ በህወሓት የተገደሉት ቁጥር ከ1300 እንደሚበልጥ ተነገረ March 15, 2021 08:54 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule