• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በአዲስ ዓመት ለተግባራዊ ዕርምጃ መዘጋጀት ይገባል

September 10, 2014 12:06 am by Editor Leave a Comment

እንኳን ለ፪ሺ፯ ዓ.ም. አደረሠን፣ አደረሣችሁ!

ውድ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን፦

እኛ ኢትዮጵያውያን በየዓመቱ የመስከረምን ወር የመጀመሪያ ቀን የዘመን መለወጫ ዕለት አድርገን ማክበር የጀመርነው በሺህዎች ለሚቆጠሩ ዘመናት እንደሆነ ይታወቃል። በረዥሙ ታሪካችን እንደየአመጣጣቸው፦ ደስታን እና ሐዘንን፣ መከራን እና ብሥራትን፣ ጦርነትን እና ሰላምን፣ መቆርቆዝን እና መበልፀግን፣ ረሃብን እና አንፃራዊ ጥጋብን፣ ወዘተርፈ አስተናግደናል። ያለፈውን ዘመን ሸኝተን አዲስ ዓመት ስንቀበል ዘወትር መልካም ምኞታችንን እንገልፃለን። ስለዚህ ይህ መግለጫም የኢትዮጵያውያን የዘመናት ትውፊት አንዱ አካል ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል።

ያገባደድነውን ዓመት ዘመነ-ማርቆስን ስንሸኝ በዓመቱ ውስጥ ያከናወናቸውን ተግባሮች መመዘን ጠቃሚ ይሆናል። ስለሆነም፦

«እኔ ለራሴ ነፃነት መከበር፣ እንዲሁም ወገኖቼ ኢትዮጵያውያንም ከአረመኔያዊው የትግሬ-ወያኔ ናዚያዊ አገዛዝ ነፃ እንዲወጡ የድርሻዬን ምን አከናውኛለሁ?»

ብለን እያንዳንዳችን ራሣችንን መጠዬቅ ይገባናል። ያለበለዚያ ግን ዓመት ቆጥሮ፣ ለይስሙላ ብቻ «እንኳን አደረሰህ፣ አደረሰሽ፣ አደረሳችሁ!» መባባሉ ብቻ ፋይዳ የለውም።

ነገ የምንቀበለው ዘመነ-ሉቃስ፣ እያንዳንዳችን ለአገራችን ለኢትዮጵያ ዳግማዊ ትንሣኤ ታላቅ ታሪካዊ ኃላፊነትን ለመወጣት ከወሬ ባለፈ የመጀመሪያውን ተግባራዊ ዕርምጃ «ሀ» ብለን የምንጀምርበት ዕለት ሊሆን ይገባል። የዘመናዊ ቅኝ ገዢዎች ወኪሎች ሆነው፣ አገራችንን እና ወገኖቻችንን የመከራ ፍዳ የሚያስከፍሉትን የትግሬ-ወያኔዎችን እና መሠል ተባባሪዎቻቸውን ድል መንሣት የምንችለው፣ ከማንም የውጭ ኃይል በሚጣልልን ዳረጎት እና የዕርዳታ አሽክላ ሣይሆን፣ በራሣችን ኃይል ተማምነን ስንቆም መሆኑን ለአፍታም መጠራጠር የለብንም። ለዚህ ደግሞ «አንድነት ኃይል ነው!» የሚለውን ዕድሜ-ጠገብ ብሂል ልንከተል ይገባል።

በተለይ ለዐማራ ተወላጅ ኢትዮጵያውያን፦ ጥንትም ሆነ ዛሬ ነፃነታችንን አስከብረን የኖርነው በራሣችን ተጋድሎ እንጂ በውጭ ኃይሎች በጎ ፈቃን ያለመሆኑን አንዘንጋ። ስለዚህም በእኛ ላይ የዘር ማፅዳት እና የዘር ማጥፋት ዘመቻ ከፍቶ የኅልውና መጥፋት አደጋ ላይ ያደረሰንን የትግሬ-ወያኔ አገዛዝ እንደ ንብ ሠራዊት «ሆ» ብለን በአንድነት እንዝመትበት። «መጀመሪያ የመቀመጫዬን» እንዳለችዋ ብልህ እንስሣ፣ እኛም በያለንበት የሚገኙትን ወንጀለኛ የወያኔ-ናዚዎች ነባራዊ ሁኔታው በሚፈቅድልን መንገድ እንታገላቸው። ይህንን በማድረግ የጥንታዊት አገራችንን የኢትዮጵያን ዳግም ትንሣኤ እናረጋግጥ!

መልካም አዲስ ዓመት!

ረቡዕ ጳጉሜን ፭ ቀን ፪ሺ፮ ዓ.ም.

ዐማራን ከፈፅሞ ጥፋት እንታደግ!
ፈለገ-አሥራት የትውልዳችን ቃልኪዳን ነው!
ኢትዮጵያ በታማኝ እና ቆራጥ ልጆቿ መስዋዕትነት ለዘለዓለም ፀንታ ትኖራለች!

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule