• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በአዲስ ዓመት ለተግባራዊ ዕርምጃ መዘጋጀት ይገባል

September 10, 2014 12:06 am by Editor Leave a Comment

እንኳን ለ፪ሺ፯ ዓ.ም. አደረሠን፣ አደረሣችሁ!

ውድ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን፦

እኛ ኢትዮጵያውያን በየዓመቱ የመስከረምን ወር የመጀመሪያ ቀን የዘመን መለወጫ ዕለት አድርገን ማክበር የጀመርነው በሺህዎች ለሚቆጠሩ ዘመናት እንደሆነ ይታወቃል። በረዥሙ ታሪካችን እንደየአመጣጣቸው፦ ደስታን እና ሐዘንን፣ መከራን እና ብሥራትን፣ ጦርነትን እና ሰላምን፣ መቆርቆዝን እና መበልፀግን፣ ረሃብን እና አንፃራዊ ጥጋብን፣ ወዘተርፈ አስተናግደናል። ያለፈውን ዘመን ሸኝተን አዲስ ዓመት ስንቀበል ዘወትር መልካም ምኞታችንን እንገልፃለን። ስለዚህ ይህ መግለጫም የኢትዮጵያውያን የዘመናት ትውፊት አንዱ አካል ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል።

ያገባደድነውን ዓመት ዘመነ-ማርቆስን ስንሸኝ በዓመቱ ውስጥ ያከናወናቸውን ተግባሮች መመዘን ጠቃሚ ይሆናል። ስለሆነም፦

«እኔ ለራሴ ነፃነት መከበር፣ እንዲሁም ወገኖቼ ኢትዮጵያውያንም ከአረመኔያዊው የትግሬ-ወያኔ ናዚያዊ አገዛዝ ነፃ እንዲወጡ የድርሻዬን ምን አከናውኛለሁ?»

ብለን እያንዳንዳችን ራሣችንን መጠዬቅ ይገባናል። ያለበለዚያ ግን ዓመት ቆጥሮ፣ ለይስሙላ ብቻ «እንኳን አደረሰህ፣ አደረሰሽ፣ አደረሳችሁ!» መባባሉ ብቻ ፋይዳ የለውም።

ነገ የምንቀበለው ዘመነ-ሉቃስ፣ እያንዳንዳችን ለአገራችን ለኢትዮጵያ ዳግማዊ ትንሣኤ ታላቅ ታሪካዊ ኃላፊነትን ለመወጣት ከወሬ ባለፈ የመጀመሪያውን ተግባራዊ ዕርምጃ «ሀ» ብለን የምንጀምርበት ዕለት ሊሆን ይገባል። የዘመናዊ ቅኝ ገዢዎች ወኪሎች ሆነው፣ አገራችንን እና ወገኖቻችንን የመከራ ፍዳ የሚያስከፍሉትን የትግሬ-ወያኔዎችን እና መሠል ተባባሪዎቻቸውን ድል መንሣት የምንችለው፣ ከማንም የውጭ ኃይል በሚጣልልን ዳረጎት እና የዕርዳታ አሽክላ ሣይሆን፣ በራሣችን ኃይል ተማምነን ስንቆም መሆኑን ለአፍታም መጠራጠር የለብንም። ለዚህ ደግሞ «አንድነት ኃይል ነው!» የሚለውን ዕድሜ-ጠገብ ብሂል ልንከተል ይገባል።

በተለይ ለዐማራ ተወላጅ ኢትዮጵያውያን፦ ጥንትም ሆነ ዛሬ ነፃነታችንን አስከብረን የኖርነው በራሣችን ተጋድሎ እንጂ በውጭ ኃይሎች በጎ ፈቃን ያለመሆኑን አንዘንጋ። ስለዚህም በእኛ ላይ የዘር ማፅዳት እና የዘር ማጥፋት ዘመቻ ከፍቶ የኅልውና መጥፋት አደጋ ላይ ያደረሰንን የትግሬ-ወያኔ አገዛዝ እንደ ንብ ሠራዊት «ሆ» ብለን በአንድነት እንዝመትበት። «መጀመሪያ የመቀመጫዬን» እንዳለችዋ ብልህ እንስሣ፣ እኛም በያለንበት የሚገኙትን ወንጀለኛ የወያኔ-ናዚዎች ነባራዊ ሁኔታው በሚፈቅድልን መንገድ እንታገላቸው። ይህንን በማድረግ የጥንታዊት አገራችንን የኢትዮጵያን ዳግም ትንሣኤ እናረጋግጥ!

መልካም አዲስ ዓመት!

ረቡዕ ጳጉሜን ፭ ቀን ፪ሺ፮ ዓ.ም.

ዐማራን ከፈፅሞ ጥፋት እንታደግ!
ፈለገ-አሥራት የትውልዳችን ቃልኪዳን ነው!
ኢትዮጵያ በታማኝ እና ቆራጥ ልጆቿ መስዋዕትነት ለዘለዓለም ፀንታ ትኖራለች!

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ኢትዮጵያ ጨምሮ የቀይ ባሕር ሀገራት ቀጣናዊ ስጋቶች በመጨመራቸው የባሕር ትብብር ለማጠናከር ወሰኑ August 28, 2026 11:32 am
  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
Copyright © 2026 · Goolgule