• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የግንቦት 20 አከባበር

May 28, 2016 07:22 am by Editor 1 Comment

* ግንቦት 20 ሲከበር
* አሸርጋጁ አደባባይ
* የግንቦት 20 ፍሬዎች

ልክ የዛሬ 25 ዓመት … የድሉ እወጃ!

በዚያች ቀን ነፍስ ያወቅን ሁላችንም  የምናስታውሳት አዋጅ ተነገረች  …”የዘመናት የህዝብ ብሶት የወለደው ጀግናው የኢህአዴግ ሠራዊት ደርግ ሲጠቀምበት የነበረውን የአዲስ አበባ ሬዲዮ ለሰፊው ህዝብ ጥቅም ሲል ተቆጣጥሮታል፣ ግንቦት 20፣ 1983 ዓ.ም!”

ግንቦት 20፣ 2008 ዓ.ም ማለዳ …

25 ዓመት የድል ነጻነት ኢዮቤልዩ የድል በአላቸውን የሚያከብሩት የኢህአዴግና ሹማምንትና ደጋፊዎች በአደባባዩ ተገኝተዋል፣ በኢህአዴግ ከፍተኛ ሹማምንት፣ በአዲስ አበባ ነዋሪዎች ታድመውበታል … ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ኋይለ ማርያም ደሳለኝ ድሮ ሀገሬው “ሰው በላ”  እያለ ያወግዘው የነበረበትን ቃል ተጠቅመው ዛሬ እሳቸው “ሰው በላ” ያሉት ደርግ የተገረሰሰበትን የግንቦት 20 የኢህአዴግ የኢዩቤልዩ በዓል ምክንያት በማድረግ ንግግር እያደረጉ ነው … የ25 ዓመቱ የሰመረ የልማት ትራንስፎርሜሽን ስኬት በጠቅላይ ሚኒስትሩ እየተዘረዘረ ነው፣ በንግግራቸው ባይመስጥም በ25 ዓመታት ተደረጉ ያሏቸው እድገቶች፣ ልማቶች፣ የተፈጥሮ አደጋ ጋር የተደረገው ፈታኝ ግብግብ፣ ዲሞክራሲያዊ መንግስት፣ የመልካም አስተዳደር ግንባታ፣ ኪራይ ሰብሳቢነትን ለማጥፋት እየተደረገ ስላለው ትግል ዘራዘሩ  … እንዲህ የሚሏት ሀገር ሀገሬ ስለመሆኗ ተጠራጠርኩ፣ የሆነው እውነት ከሆነ መልካም ነው ስል በትዝብት አንገቴን ደፋ አድርጌ ቆዘምኩ …

ከ25 ዓመቱን የኢህአዴግ አገዛዝ 4 ያህሉን አመታት ብቻ በሀገር ቤት ሆኘ የማውቅ፣ ከ20 ዓመት በላይ በሳውዲ ስደት የከተምኩ ኢትዮጵያዊ ነኝ!  25  ዓመቱን አገዛዝ፣ ኢትዮጵያውያንን  እንደ መረጃ ተቀባይና አቀባይ ማሰብ በራሱ ያማል … እናም ጠቅላይ ሚኒስትራችን ያሉት እድገት እያለ ዛሬ ድረስ፣ ድህነት፣ የኑሮ ውድነት፣ መልካም አስተዳደርና ፖለቲካው ገፍቶት ከሀገር የሚሰደደው ዜጋ እልፍ አእላፍ እየሆነ በመጣበት የታሪክ አጋጣሚ የጠቅላያችን ንግግር አልገባኝ አለ! የእድገት ትሩፋቱ ተጠቃሚዎች ከመላው ሀገሬ ምን ያህሉ ናቸው?  በ25 ዓመቱ አገዛዝ መብታችን ይከበር ባሉ የተረገጡት፣ በጻፉና በተናገሩ ወጣትነታቸውን እድሜ የተቀሙ፣ ለአመታት ለእስር የተዳረጉ፣ በህገ መንግስቱ የተሰጠው መብት ይከበር ባሉ ወህኒ የወረዱ … እኒህኞቹስ? አልኩ … አዎ በአሉ የእነሱ ሊሆን አይችልም! ድፍን 20 ዓመት በአረብ ሀገር ስደት የተጎሳቆሉት፣ አሁን ድረስ የመብት አስከባሪ አጥተው ለሚንገላቱት “በአሉ በአላችን አይሆንም!”  ቢሉ አልፈርድባቸውም፣  በአንጻሩ “በ25 ዓመቱ እድገትና ትራንስፎርሜሽን ተጠቅመናል” ያሉ ሰንጋ አርደው በዓሉን ቢያከብሩት አይደንቀኝም፣ ተጠቅመዋልና! ለእኔ ቁም ነገሩ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለአብዛኛው ሀገሬ የመጣው ድል አብዛኛው ሀገሬ ተጠቃሚ ነው ወይ? የሚለው ነው! ታዲያ ተጠቃሚ ከሆነ ሰው  ሞትን እየተጋፈጠ ለምን ስደትን ይመርጣል? ይህ አልገባኝ ብሏልና ዛሬም አጠይቃለሁ! ginbot20

አሸርጋጁ አደባባይ …

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ንግግን አብቅቶ ትርኢት መታየት ሲጀምር የመስቀል አደባባይ ትዝ አለኝ … አሸርጋጁ አደባባይ ያልኩትን የመስቀል አደባባይ “ይህ የተረገመ አደባባይ!” አልኩት በልቤ … መንግስት በሄደ  በመጣ ቁጥር ሰው ተመርጦ፣ በደቦ ተጠርቶ፣ ይሰበሰብበታል፣ ሰው ተመርጦ ” … ይህን መፈክር በል፣ ይህን መፈክር ያዝ … በዚህ ሂድ … ” ይባልና እንደ እውነተኛ የህዝብ ስሜት ይነገርበታል … ይህ አደባባይ፣ ሀገሬው በኑሮ ውድነት፣ በፖለቲካው ግለት እየታመሰ መሪዎች የሚመሯት ሀገር እድገቷ የመጠቀ፣ መጻኤ ህይወቷ ብሩህ እንደሆነ የሚደሰኩሩባት አደባባይ በእርግጥም የመቀል አደባባይ መባል አልነበረበትም! ቢያንስ ለሰው ልጅ ድህነት ምልክት የሆነው የመስቀሉ በዓል የሚከበርበት ቦታ ከዘመነ ደርግ እስከ ኢህአዴግ የውሸት ዲስኩር መናገሪያ፣ የውሸት ሰልፍና ሽለላ ማሳያ አደባባይ ባልሆነ በመረጥኩ ስል ከራሴ ጋር ተሟገትኩ …

በአደባባዩ የብሔር ብሔረብ ብዝሃ ህዝብ …ትርኢቱ እንደ ቀጠለ ነው፣ በስደቱ አለም የ 20 ዓመት መብት ማስከበር ክሽፈት ምስክር ነኝና ጠባቂ ባጣው ስደተኛ የሆነው ሁሉ ከፊቴ ድቅን አለ …

ግንቦት 20 ሳስታሰውስ ደግሞ ደርግ ትዝ አለኝ፣ ደርግ ክፉ ነበር፣ እንኳንም ወደቀ! በደርግ ግፍና ጭቆና ተማርራችሁ ስለ እውነተኛ ዲሞክራሲ ደክማችሁ ላለፋችሁ፣ ጭቆናን ተጸይፋችሁ ለኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን ስትሉ ከአባገነኑ ደርግ ጋር ለተፋለማችሁ ክብር አለኝ ፣ እንኳን ደርግ ከወደቀበት 25 ዓመት አደረሳችሁ!

… ግን የታገላችሁበት፣ የመጣው ድል ከብዝሃነት እስኪደርስ  የሆነው ያኮራል አልልም … ሌላው ቀርቶ ሀገር የተባለውን ያህል ካደገች ለምን ሰው ይሰደዳል?  አልኩ፣ እንደሞኝ ነገር ደጋግሜ የጠቅላያችን የዛሬ ንግግር አስታውሸ … ከራሴ ጋር መጃጃሉን ተውኩት፣ ዝግጅቱን መከታተሉንም አቁሜ ራሴን አቀርቅሬ የአረብ ሀገሩ ስደትና የግንቦት 20 ፍሬዎች ስል በማለዳ ወጌን  መሞነጫጨር ቀጠልኩ …! የግንቦት 20 ፍሬዎች … ይቀጥላል!

ቸር ያሰማን
ነቢዩ ሲራክ
ግንቦት 20 ቀን 2008 ዓም


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. ሸመልስይማም says

    June 2, 2016 09:18 am at 9:18 am

    ጨካኙና አረመኔው ህወሀት ኢሀዴግ አባታቸው ሻቢያ ዘሬ Is Is የሚፈፅመውን ዘግነኝ ድርጊት በንፁሀን አትዮጵያን ላይ ፈፅመዉታል የኔ አንዲህ አንደ አሁኑ ቴክኖሎጂ ያልተስፋፋበተ ሰለነበር አለም አላወቃቸዉም ነበር አናም ከነዚ ገንጣይ አስገንጣይ ቡደኖቸ ልማተም ሆነ እድገት የለም

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule