• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የግንቦት 20 አከባበር

May 28, 2016 07:22 am by Editor 1 Comment

* ግንቦት 20 ሲከበር
* አሸርጋጁ አደባባይ
* የግንቦት 20 ፍሬዎች

ልክ የዛሬ 25 ዓመት … የድሉ እወጃ!

በዚያች ቀን ነፍስ ያወቅን ሁላችንም  የምናስታውሳት አዋጅ ተነገረች  …”የዘመናት የህዝብ ብሶት የወለደው ጀግናው የኢህአዴግ ሠራዊት ደርግ ሲጠቀምበት የነበረውን የአዲስ አበባ ሬዲዮ ለሰፊው ህዝብ ጥቅም ሲል ተቆጣጥሮታል፣ ግንቦት 20፣ 1983 ዓ.ም!”

ግንቦት 20፣ 2008 ዓ.ም ማለዳ …

25 ዓመት የድል ነጻነት ኢዮቤልዩ የድል በአላቸውን የሚያከብሩት የኢህአዴግና ሹማምንትና ደጋፊዎች በአደባባዩ ተገኝተዋል፣ በኢህአዴግ ከፍተኛ ሹማምንት፣ በአዲስ አበባ ነዋሪዎች ታድመውበታል … ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ኋይለ ማርያም ደሳለኝ ድሮ ሀገሬው “ሰው በላ”  እያለ ያወግዘው የነበረበትን ቃል ተጠቅመው ዛሬ እሳቸው “ሰው በላ” ያሉት ደርግ የተገረሰሰበትን የግንቦት 20 የኢህአዴግ የኢዩቤልዩ በዓል ምክንያት በማድረግ ንግግር እያደረጉ ነው … የ25 ዓመቱ የሰመረ የልማት ትራንስፎርሜሽን ስኬት በጠቅላይ ሚኒስትሩ እየተዘረዘረ ነው፣ በንግግራቸው ባይመስጥም በ25 ዓመታት ተደረጉ ያሏቸው እድገቶች፣ ልማቶች፣ የተፈጥሮ አደጋ ጋር የተደረገው ፈታኝ ግብግብ፣ ዲሞክራሲያዊ መንግስት፣ የመልካም አስተዳደር ግንባታ፣ ኪራይ ሰብሳቢነትን ለማጥፋት እየተደረገ ስላለው ትግል ዘራዘሩ  … እንዲህ የሚሏት ሀገር ሀገሬ ስለመሆኗ ተጠራጠርኩ፣ የሆነው እውነት ከሆነ መልካም ነው ስል በትዝብት አንገቴን ደፋ አድርጌ ቆዘምኩ …

ከ25 ዓመቱን የኢህአዴግ አገዛዝ 4 ያህሉን አመታት ብቻ በሀገር ቤት ሆኘ የማውቅ፣ ከ20 ዓመት በላይ በሳውዲ ስደት የከተምኩ ኢትዮጵያዊ ነኝ!  25  ዓመቱን አገዛዝ፣ ኢትዮጵያውያንን  እንደ መረጃ ተቀባይና አቀባይ ማሰብ በራሱ ያማል … እናም ጠቅላይ ሚኒስትራችን ያሉት እድገት እያለ ዛሬ ድረስ፣ ድህነት፣ የኑሮ ውድነት፣ መልካም አስተዳደርና ፖለቲካው ገፍቶት ከሀገር የሚሰደደው ዜጋ እልፍ አእላፍ እየሆነ በመጣበት የታሪክ አጋጣሚ የጠቅላያችን ንግግር አልገባኝ አለ! የእድገት ትሩፋቱ ተጠቃሚዎች ከመላው ሀገሬ ምን ያህሉ ናቸው?  በ25 ዓመቱ አገዛዝ መብታችን ይከበር ባሉ የተረገጡት፣ በጻፉና በተናገሩ ወጣትነታቸውን እድሜ የተቀሙ፣ ለአመታት ለእስር የተዳረጉ፣ በህገ መንግስቱ የተሰጠው መብት ይከበር ባሉ ወህኒ የወረዱ … እኒህኞቹስ? አልኩ … አዎ በአሉ የእነሱ ሊሆን አይችልም! ድፍን 20 ዓመት በአረብ ሀገር ስደት የተጎሳቆሉት፣ አሁን ድረስ የመብት አስከባሪ አጥተው ለሚንገላቱት “በአሉ በአላችን አይሆንም!”  ቢሉ አልፈርድባቸውም፣  በአንጻሩ “በ25 ዓመቱ እድገትና ትራንስፎርሜሽን ተጠቅመናል” ያሉ ሰንጋ አርደው በዓሉን ቢያከብሩት አይደንቀኝም፣ ተጠቅመዋልና! ለእኔ ቁም ነገሩ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለአብዛኛው ሀገሬ የመጣው ድል አብዛኛው ሀገሬ ተጠቃሚ ነው ወይ? የሚለው ነው! ታዲያ ተጠቃሚ ከሆነ ሰው  ሞትን እየተጋፈጠ ለምን ስደትን ይመርጣል? ይህ አልገባኝ ብሏልና ዛሬም አጠይቃለሁ! ginbot20

አሸርጋጁ አደባባይ …

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ንግግን አብቅቶ ትርኢት መታየት ሲጀምር የመስቀል አደባባይ ትዝ አለኝ … አሸርጋጁ አደባባይ ያልኩትን የመስቀል አደባባይ “ይህ የተረገመ አደባባይ!” አልኩት በልቤ … መንግስት በሄደ  በመጣ ቁጥር ሰው ተመርጦ፣ በደቦ ተጠርቶ፣ ይሰበሰብበታል፣ ሰው ተመርጦ ” … ይህን መፈክር በል፣ ይህን መፈክር ያዝ … በዚህ ሂድ … ” ይባልና እንደ እውነተኛ የህዝብ ስሜት ይነገርበታል … ይህ አደባባይ፣ ሀገሬው በኑሮ ውድነት፣ በፖለቲካው ግለት እየታመሰ መሪዎች የሚመሯት ሀገር እድገቷ የመጠቀ፣ መጻኤ ህይወቷ ብሩህ እንደሆነ የሚደሰኩሩባት አደባባይ በእርግጥም የመቀል አደባባይ መባል አልነበረበትም! ቢያንስ ለሰው ልጅ ድህነት ምልክት የሆነው የመስቀሉ በዓል የሚከበርበት ቦታ ከዘመነ ደርግ እስከ ኢህአዴግ የውሸት ዲስኩር መናገሪያ፣ የውሸት ሰልፍና ሽለላ ማሳያ አደባባይ ባልሆነ በመረጥኩ ስል ከራሴ ጋር ተሟገትኩ …

በአደባባዩ የብሔር ብሔረብ ብዝሃ ህዝብ …ትርኢቱ እንደ ቀጠለ ነው፣ በስደቱ አለም የ 20 ዓመት መብት ማስከበር ክሽፈት ምስክር ነኝና ጠባቂ ባጣው ስደተኛ የሆነው ሁሉ ከፊቴ ድቅን አለ …

ግንቦት 20 ሳስታሰውስ ደግሞ ደርግ ትዝ አለኝ፣ ደርግ ክፉ ነበር፣ እንኳንም ወደቀ! በደርግ ግፍና ጭቆና ተማርራችሁ ስለ እውነተኛ ዲሞክራሲ ደክማችሁ ላለፋችሁ፣ ጭቆናን ተጸይፋችሁ ለኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን ስትሉ ከአባገነኑ ደርግ ጋር ለተፋለማችሁ ክብር አለኝ ፣ እንኳን ደርግ ከወደቀበት 25 ዓመት አደረሳችሁ!

… ግን የታገላችሁበት፣ የመጣው ድል ከብዝሃነት እስኪደርስ  የሆነው ያኮራል አልልም … ሌላው ቀርቶ ሀገር የተባለውን ያህል ካደገች ለምን ሰው ይሰደዳል?  አልኩ፣ እንደሞኝ ነገር ደጋግሜ የጠቅላያችን የዛሬ ንግግር አስታውሸ … ከራሴ ጋር መጃጃሉን ተውኩት፣ ዝግጅቱን መከታተሉንም አቁሜ ራሴን አቀርቅሬ የአረብ ሀገሩ ስደትና የግንቦት 20 ፍሬዎች ስል በማለዳ ወጌን  መሞነጫጨር ቀጠልኩ …! የግንቦት 20 ፍሬዎች … ይቀጥላል!

ቸር ያሰማን
ነቢዩ ሲራክ
ግንቦት 20 ቀን 2008 ዓም


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. ሸመልስይማም says

    June 2, 2016 09:18 am at 9:18 am

    ጨካኙና አረመኔው ህወሀት ኢሀዴግ አባታቸው ሻቢያ ዘሬ Is Is የሚፈፅመውን ዘግነኝ ድርጊት በንፁሀን አትዮጵያን ላይ ፈፅመዉታል የኔ አንዲህ አንደ አሁኑ ቴክኖሎጂ ያልተስፋፋበተ ሰለነበር አለም አላወቃቸዉም ነበር አናም ከነዚ ገንጣይ አስገንጣይ ቡደኖቸ ልማተም ሆነ እድገት የለም

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule