• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የህዝባችንን የትግል ፈር እንከተል!!

August 18, 2016 12:02 am by Editor Leave a Comment

ለወራት በኦሮሞ ወጣቶች ሲካሄድ የቆየው ለዴሞክራሲ የሚደረገው ህዝባዊ ትግል ሳያቋርጥና እየሰፋም እየሄደ ባለበት በአሁኑ ወቅት ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን እየደጋገሙ ሲታገሉለት የቆየው የህዝቦች ወንድማማችነትና የትግል አንድነት ጥያቄም ባለፉት ሳምንታት በአማራውና በኦሮሞ ክልሎች በሚካሄዱት ሰላማዊና ህዝባዊ ትግሎች አማካኝነት ስር እየሰደደ መሆኑን እየታዘብን

ነው፡፡ በዚያው ልክ ደግሞ በትግሉ ማየልና መስፋት ብርክ የያዛቸው የወያኔ/ ኢህአዴግ መሪዎች ህዝቡ በሰላማዊ መንገድ ለሚያቀርባቸው ጥያቄዎች ለመስጠት የሚሞክሩት አጸፋ በለየለት ጸረ ህዝብ አመጽ መሰማራት ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ በዚህ መልክ ባለፉት ወራት በኦሮሞ ታጋዮች ላይ ያወረዱትና በመቶ የሚቆጠሩ ንጹህ ዜጎችን መግደልና በሽህ የሚቆጠሩ ሌሎችን ለእስር መዳረግ ሳይበቃቸው አሁን ደግሞ በኦሮሞም በአማራም ታጋዮች ላይ ይህንኑ የጥፋት ሂደት እየተከተሉ ይታያሉ፡፡ ከሁሉ አስቀድሞ ድርጅታችን ይህንን የአፈና ውርጅብኝ ሙሉ በሙሉ እያወገዘና ለተሰውት ወገኖች ዘመዶችና ወዳጆች መጽናናትን እየተመኘ በእስር በመንገላታት ላይ ካሉት ታጋዮቻችን ጋር አንድነቱን ለመግለጽ ይፈልጋል፡፡

በጎንደርም ሆነ እንደ ባህር ዳር ባሉ ሌሎች ከተሞች የሚካሄዱት የአካባቢውን ህዝብ በሙሉ ያካተቱ ትግሎች ሰላማዊ ከመሆናቸው ባሻገር የወያኔን የከፋፍለህ ገዛ ፖለቲካ ሙሉ በሙሉ በማክሸፍ በኦሮሚያ ከሚካሄደው ህዝባዊ ትግል ጋር አንድነትን እያነጸባረቁ ናቸው፡፡ የጎንደር ሰልፈኞች ‘በኦሮምያ የሚፈሰው የወንድሞቻችን ደም የኛም ደም ነው’sሲሉ በባህር ዳር በተካሄደው ሰልፍ ደግሞ የአቶ በቀለ ገርባን ፎቶግራፍ በመያዝ ‘በቀለ ገርባ መሪያችን ነው’s ‘በቀለ ገርባ አሸባሪ አይደለም’ በሚሉ መፈክሮች አማካኝነት የአማራው ህዝብ ከኦሮሞ ወንድሞቹና እህቶቹ ጋር ያለውን ትስስርና የትግል አንድነት በይፋ ሲያስተጋባ ተስተውሏል፡፡ በአምቦ፣ ሻሻመኔ፣ ነቀምቴ ጉደር ወዘተ ደግሞ የኦሮሞ ታጋዮች በበኩላቸው ‘አማራ የኛ ነው’ ‘እነ በቀለ ገርባ፣ አንዳርጋቸው ጽጌ፣ በመላ በሃገሪቱ የፖለቲካ እስረኞች ይፈቱ’sወዘተ በሚሉ መፈክሮች የታጀቡ ሰላማዊ ሰልፎች አካሂደዋል፡፡ እያካሄዱም ነው፡፡

በዚህ በጎ ሂደት ክፉኛ የተደናገጡት የወያኔ-ኢህአዴግ መሪዎች ለተፈጠረው አዲስ ሁኔታ በመሞከር ላይ ያሉት አጸፋ ከዚያው ካረጀ ካፈጀ ስትራቴጂያቸው የተለየ ምንም አዲስ ነገር የለውም፡፡ መጀመሪያ ነገር በኦሮምያም ሆነ በአማራው ክልል ከግንቦት 97 ወዲህ ባልታያ ሁኔታ ህዝብ ከዳር እስከዳር የሚሳተፍበትን እንቅስቃሴ ‘‘በጥቂት አክራሪና ሽብርተኛ ግለሰቦች’’ የተጠነሰሰ ጸረ ህዝብና ጸረ ህገመንግስት ትግል አድርጎ የሚያቀርብ ግልጽ የሆነ ቅስቀሳ ይታያል፡፡ ከዚህ አንጻር የወልቃይት ጠገዴን ጉዳይ ‘የህዝብ ሳየሆን የጥቂት አመራሮች ችግር ነው’ በማለት ሃይለ ማርያም ደሳለኝ መግለጫ ሲሰጥ እነ ሬድዮ ፋናና ሌሎች የወያኔ አፈ ቀላጤዎች በዚሁ መልክ ንቅናቄውን ህዝቡ ጨርሶ የማይቀበለው የጥቂት አክራሪዎች ሴራ አድርገው ለማቅረብ ሞክረዋል፡፡ የጎንደር ህዝብ በማያሻማ ሁኔታ ‘የሻብያ ተላላኪ እኛ ሳንሆን ወያኔ ነው’s ብሎ በግልጽ ያስቀመጠውን ሃቅ ጨርሶ በመካድ ይህንን ህዝባዊ ትግል የሻብያ ተላላኪዎች ሴራ አድርጎ ለማቅረብ የሚደረገው ከንቱ ሙከራ አገዛዙ ምንኛ ውጥረት ላይ እንደወደቀ የሚያሳይ አካሄድ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡

የወያኔ ኢህአዴግ መሪዎች እስከዛሬ የህዝብን ትግል ለማክሸፍ ይጠቀሙበት የነበረው የከፋፍለህ ግዛ ፖለቲካ በዚህ መልክ በህዝቦች ወንድማማችነትና የትግል አንድነት መንፈስ እየከሸፈ መሄዱ ትልቅ ህዝባዊ ድል ቢሆንም ይህ በጎ ሂደት በአማራና ኦሮሞ ህዝቦች የወንድማማችነት መንፈስ መጎልበት ብቻ መወሰን የለበትም፡፡ የወያኔ መሪዎች ለህልውናቸው አለን የሚሏቸውን ሁለት ሌሎች ከፋፋይ ስትራጂዎቻቸውንም ከማገዝ ይልቅ ለማክሸፍ መስራት ያስፈልጋል፡፡

አንደኛው የከፋፍለህ ግዛ ስትራጂያቸው ዘርፍ ለትግራይ ህዝብ ይህ ዴሞክራሲያዊና ህዝባዊ ተጋድሎ በሱም ህልውና ላያ ያነጣጠረ ሴራ አድርጎ ማቅረብ እንደሆነ ባለፉት አመታት በተደጋጋሚ ያየነው ነው፡፡ በተያያዝነው ትግል ከተቃዋሚዎች ጎራ የሚሰነዘር ማንኛውም ጸረ ትግራይ ህዝብ ልፈፋ ይህንን የወያኔ ስትራቴጂ የሚያግዝ እንደሆነ ሁሉም ሊገነዘበው ይገባል፡፡ ከዚህ ይልቅ ይህ ለዴሞክራሲ የሚደረገው ታሪካዊ ተጋድሎ በምንም አይነት ጸረ ትግራይ ህዝብ እንዳልሆነ፣ እንዲያውም አንዱ አላማው የትግራይም ህዝብ ከዚህ አፋኝ አመራር ነጻ ወጥቶ በዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ እሱም ተገቢ ቦታውን ይዞ ከቀሩት ወንድሞቹ ኢትዮጵያውያን ጋር በሰላምና በነጻነት የሚኖርበት ህብረተሰብ የመፍጠር አላማ መሆኑን እያበሰሩ በአላሰለሰ ሁኔታ ለትግራይም ህዝብ የትግል አንድነት ጥሪ ማስተላለፍ ያስፈልጋል፡፡

እየሰፈነ በመሄድ ላይ ባለው የህዝቦች ወንድማማችነት መንፈስ ብርክ የያዛቸው የወያኔ/ኢህአዴግ መሪዎች የሚቀራቸው አንድ መውጫ ዘዴ የህዝቡን ትግል በለየለት አመጽና በደም ባህር የማስመጥ ርኩስ ስትራቴጂ እንደሆነ ሰሞኑን በይፋ እያሳዩን ነው፡፡ ይህ እንዲሳካላቸው ደግሞ የማይቀረው አካሄዳቸው ለኢህአዴግ አባላትና ለሰራዊቱም ሆነ ለፖሊሱና ለደህንነቱ ይህንን ህዝባዊ ንቅናቄ በነሱም ህልውና ላይ ያነጣጠረ አድርጎ በማቅረብ እነዚህ ወገኖች በአልሞት ባይ ተጋዳይነት ስሜት እስከመጨረሻው ከአገዛዙ ጎን ጸንተው እንዲቆሙ መሞከር እንደሆነ ግልጽ ነው፡፡ ይህንን አካሄዳቸውን ለማክሸፍ ደግሞ ባላሰለሰ ቅስቀሳ ህዝባዊው ትግል ከነዚህ ወገኖች ጋር ምንም ጸብ እንደሌለው፣ አላማው ብሄራዊ እርቅ የሰፈነባትና ለእነሱም የምትሆን ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን ለመመስረት መሆኑን ለማስጨበጥ መሞከርና በምንም አይነት የወያኔ/ኢህአዴግን መሪዎች ርኩስ ስትራቴጂ ሊያግዙ ከሚችሉ ቅስቀሳዎች መቆጠብ ያስፈልጋል ማለት ነው፡፡

እንዲህ አይነቱ አካሄድ ፖሊሱና ሰራዊቱ በደመ ነፍስ ከሚወስዷቸው ጸረ ህዝብ እርምጃዎች እንዲቆጠቡ፣ የኢህአዴግ አባል ድርጅቶች መሪዎችና አባላት ደግሞ በድርጅታቸው ውስጥ የህንን የጥቂቶች ጸረ ህዝብ ፖለቲካ ለመቃወምና ለማክሸፍ እንዲበራቱና ይህ ካልተሳካላቸው ደግሞ የህንን የጥፋት ድርጅት እየለቀቁ ከህዝቡ ትግል እንዲቀላቀሉ በሩን የሚከፍት አካሄድ በመሆኑ እንደ ትግልችን አንድ የማይናቅ ገጽታ አድርገን መውሰድ ይኖርብናል፡፡

ከዚህ ሁሉ አንጻር ሰሞኑን በሃገራችን የታዩት በጎ ክስተቶች ማንም ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅት ሳይመራቸው ‘ከታች’ ከህዝቡ ከራሱ በፈለቁና በያሉበት ‘ለትግል ተነስ’ የሚሉትን ህዝብ የህልውናም ሆነ የመብትና የማንነት ጥያቄዎች ጠንቅቀው በሚያውቁ በያሉበት የህዝቡን ችግርም ሆነ ህልም በሚጋሩ ዜጎች የሚቀነባበሩ ትግሎች ናቸው፡፡ በዚህ መልክ እየተከሰተ ያለውን በጎ ሂደት ለማገዝና ገፍቶ ለድል እንዲበቃ ለማድረግ ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች፣ ሌሎች ስብስቦችና ሃገር ወዳድ ዜጎች የሚጠበቅባቸውን ሚና ከሁለት አንጻር መጠቆም ይቻላል፡፡

አንደኛ በሰሞኑ ትግል ለተፈጠረው አዲስ ሁኔታ በሚመጥን መልክ ህዝባችን የቀደደውን ፈር በመከተል በውስጥም በውጭም ሃገር ወዳድና ዴሞክራሲያዊ የሆኑ ሃይሎች የወያኔን መሪዎች ቅስም የሰበረውን የህዝቦች ወንድማማችነት መንፈስ ለማገዝና ለማጎልበት በይፋ በአንድነት ቆመው ትግሉን ሲደግፉ መታየት ይኖርባቸዋል፡፡ ለምሳሌ በውጭ በብሄርና በህብረ በብሄር ደረጃ የተቋቋሙ የፖለቲካ ድርጅቶችና ሌሎች ስብስቦች የህዝቡን ትግል በመደገፍ ብቻ ሳይሆን በመካሄድ ላይ ያለውን አፈናና ግድያ በመቃወም የጋራ ሰላማዊ ሰልፎች ማካሄድ ይጠበቅባቸዋል፡፡ ይህ ሲደረግ ደግሞ በተቃዋሚው ጎራ አንዳንዶች አውቀውም ሆነ ሳያውቁ በሚነዟቸው ህዝብን ከህዝብ በሚያጋጩና ብሎም የወያኔ መሪዎችን የከፋፍለህ ግዛ ፖለቲካ በሚያግዙ ቅስቀሳዎች ሲሰማሩ እነዚህን አፍራሽ አካሄዶች በግልጽና በጋራ አውግዞ መውጣት ያስፈልጋል፡፡

ሁለተኛ ሁሉም የሚንቀሳቀስባቸው የህልውና፣ የማንነትም ሆኑ የመብት ጥያቄዎች ዘላቂ መፍትሄ የሚያገኙት የስርአት ለውጥ ተደርጎ ዴሞክራሲና ተጠያቂነት የሰፈኑባት ኢትዮጵያ እውን ስትሆን ብቻ ስለሆነ የህዝቡ ትግል ወደዚህ አገራዊ ግብ ለመድረስ ስለሚከተለው ቅደም ተከተል ወይም ሮድ ማፕና የሂደቱን መቋጠሪያ በተመለከተ አንድ የጋራ ስትራቴጂ ነድፎ ይህንን በትግል ላይ ላለው ህዝብ ማስጨበጥና አሁን በሚያሳየው ቆራጥነትና ብስለት ለዚህ ዘላቂና የጋራ አጀንዳ ከዳር እስከዳር ተንቀሳቅሶ በአንድ አቅጣጫ እንዲታገል መቀስቀስ ያስፈልጋል፡፡

የህዝቦች ወንድማማችነት ይለምለም!!!

መላ ኢትዮጵያ ሶሻሊስት ንቅናቄ (መኢሶን)

ነሃሴ 6 ቀን 2008 ዓ.ም.


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule