• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የህዝባችንን የትግል ፈር እንከተል!!

August 18, 2016 12:02 am by Editor Leave a Comment

ለወራት በኦሮሞ ወጣቶች ሲካሄድ የቆየው ለዴሞክራሲ የሚደረገው ህዝባዊ ትግል ሳያቋርጥና እየሰፋም እየሄደ ባለበት በአሁኑ ወቅት ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን እየደጋገሙ ሲታገሉለት የቆየው የህዝቦች ወንድማማችነትና የትግል አንድነት ጥያቄም ባለፉት ሳምንታት በአማራውና በኦሮሞ ክልሎች በሚካሄዱት ሰላማዊና ህዝባዊ ትግሎች አማካኝነት ስር እየሰደደ መሆኑን እየታዘብን

ነው፡፡ በዚያው ልክ ደግሞ በትግሉ ማየልና መስፋት ብርክ የያዛቸው የወያኔ/ ኢህአዴግ መሪዎች ህዝቡ በሰላማዊ መንገድ ለሚያቀርባቸው ጥያቄዎች ለመስጠት የሚሞክሩት አጸፋ በለየለት ጸረ ህዝብ አመጽ መሰማራት ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ በዚህ መልክ ባለፉት ወራት በኦሮሞ ታጋዮች ላይ ያወረዱትና በመቶ የሚቆጠሩ ንጹህ ዜጎችን መግደልና በሽህ የሚቆጠሩ ሌሎችን ለእስር መዳረግ ሳይበቃቸው አሁን ደግሞ በኦሮሞም በአማራም ታጋዮች ላይ ይህንኑ የጥፋት ሂደት እየተከተሉ ይታያሉ፡፡ ከሁሉ አስቀድሞ ድርጅታችን ይህንን የአፈና ውርጅብኝ ሙሉ በሙሉ እያወገዘና ለተሰውት ወገኖች ዘመዶችና ወዳጆች መጽናናትን እየተመኘ በእስር በመንገላታት ላይ ካሉት ታጋዮቻችን ጋር አንድነቱን ለመግለጽ ይፈልጋል፡፡

በጎንደርም ሆነ እንደ ባህር ዳር ባሉ ሌሎች ከተሞች የሚካሄዱት የአካባቢውን ህዝብ በሙሉ ያካተቱ ትግሎች ሰላማዊ ከመሆናቸው ባሻገር የወያኔን የከፋፍለህ ገዛ ፖለቲካ ሙሉ በሙሉ በማክሸፍ በኦሮሚያ ከሚካሄደው ህዝባዊ ትግል ጋር አንድነትን እያነጸባረቁ ናቸው፡፡ የጎንደር ሰልፈኞች ‘በኦሮምያ የሚፈሰው የወንድሞቻችን ደም የኛም ደም ነው’sሲሉ በባህር ዳር በተካሄደው ሰልፍ ደግሞ የአቶ በቀለ ገርባን ፎቶግራፍ በመያዝ ‘በቀለ ገርባ መሪያችን ነው’s ‘በቀለ ገርባ አሸባሪ አይደለም’ በሚሉ መፈክሮች አማካኝነት የአማራው ህዝብ ከኦሮሞ ወንድሞቹና እህቶቹ ጋር ያለውን ትስስርና የትግል አንድነት በይፋ ሲያስተጋባ ተስተውሏል፡፡ በአምቦ፣ ሻሻመኔ፣ ነቀምቴ ጉደር ወዘተ ደግሞ የኦሮሞ ታጋዮች በበኩላቸው ‘አማራ የኛ ነው’ ‘እነ በቀለ ገርባ፣ አንዳርጋቸው ጽጌ፣ በመላ በሃገሪቱ የፖለቲካ እስረኞች ይፈቱ’sወዘተ በሚሉ መፈክሮች የታጀቡ ሰላማዊ ሰልፎች አካሂደዋል፡፡ እያካሄዱም ነው፡፡

በዚህ በጎ ሂደት ክፉኛ የተደናገጡት የወያኔ-ኢህአዴግ መሪዎች ለተፈጠረው አዲስ ሁኔታ በመሞከር ላይ ያሉት አጸፋ ከዚያው ካረጀ ካፈጀ ስትራቴጂያቸው የተለየ ምንም አዲስ ነገር የለውም፡፡ መጀመሪያ ነገር በኦሮምያም ሆነ በአማራው ክልል ከግንቦት 97 ወዲህ ባልታያ ሁኔታ ህዝብ ከዳር እስከዳር የሚሳተፍበትን እንቅስቃሴ ‘‘በጥቂት አክራሪና ሽብርተኛ ግለሰቦች’’ የተጠነሰሰ ጸረ ህዝብና ጸረ ህገመንግስት ትግል አድርጎ የሚያቀርብ ግልጽ የሆነ ቅስቀሳ ይታያል፡፡ ከዚህ አንጻር የወልቃይት ጠገዴን ጉዳይ ‘የህዝብ ሳየሆን የጥቂት አመራሮች ችግር ነው’ በማለት ሃይለ ማርያም ደሳለኝ መግለጫ ሲሰጥ እነ ሬድዮ ፋናና ሌሎች የወያኔ አፈ ቀላጤዎች በዚሁ መልክ ንቅናቄውን ህዝቡ ጨርሶ የማይቀበለው የጥቂት አክራሪዎች ሴራ አድርገው ለማቅረብ ሞክረዋል፡፡ የጎንደር ህዝብ በማያሻማ ሁኔታ ‘የሻብያ ተላላኪ እኛ ሳንሆን ወያኔ ነው’s ብሎ በግልጽ ያስቀመጠውን ሃቅ ጨርሶ በመካድ ይህንን ህዝባዊ ትግል የሻብያ ተላላኪዎች ሴራ አድርጎ ለማቅረብ የሚደረገው ከንቱ ሙከራ አገዛዙ ምንኛ ውጥረት ላይ እንደወደቀ የሚያሳይ አካሄድ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡

የወያኔ ኢህአዴግ መሪዎች እስከዛሬ የህዝብን ትግል ለማክሸፍ ይጠቀሙበት የነበረው የከፋፍለህ ግዛ ፖለቲካ በዚህ መልክ በህዝቦች ወንድማማችነትና የትግል አንድነት መንፈስ እየከሸፈ መሄዱ ትልቅ ህዝባዊ ድል ቢሆንም ይህ በጎ ሂደት በአማራና ኦሮሞ ህዝቦች የወንድማማችነት መንፈስ መጎልበት ብቻ መወሰን የለበትም፡፡ የወያኔ መሪዎች ለህልውናቸው አለን የሚሏቸውን ሁለት ሌሎች ከፋፋይ ስትራጂዎቻቸውንም ከማገዝ ይልቅ ለማክሸፍ መስራት ያስፈልጋል፡፡

አንደኛው የከፋፍለህ ግዛ ስትራጂያቸው ዘርፍ ለትግራይ ህዝብ ይህ ዴሞክራሲያዊና ህዝባዊ ተጋድሎ በሱም ህልውና ላያ ያነጣጠረ ሴራ አድርጎ ማቅረብ እንደሆነ ባለፉት አመታት በተደጋጋሚ ያየነው ነው፡፡ በተያያዝነው ትግል ከተቃዋሚዎች ጎራ የሚሰነዘር ማንኛውም ጸረ ትግራይ ህዝብ ልፈፋ ይህንን የወያኔ ስትራቴጂ የሚያግዝ እንደሆነ ሁሉም ሊገነዘበው ይገባል፡፡ ከዚህ ይልቅ ይህ ለዴሞክራሲ የሚደረገው ታሪካዊ ተጋድሎ በምንም አይነት ጸረ ትግራይ ህዝብ እንዳልሆነ፣ እንዲያውም አንዱ አላማው የትግራይም ህዝብ ከዚህ አፋኝ አመራር ነጻ ወጥቶ በዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ እሱም ተገቢ ቦታውን ይዞ ከቀሩት ወንድሞቹ ኢትዮጵያውያን ጋር በሰላምና በነጻነት የሚኖርበት ህብረተሰብ የመፍጠር አላማ መሆኑን እያበሰሩ በአላሰለሰ ሁኔታ ለትግራይም ህዝብ የትግል አንድነት ጥሪ ማስተላለፍ ያስፈልጋል፡፡

እየሰፈነ በመሄድ ላይ ባለው የህዝቦች ወንድማማችነት መንፈስ ብርክ የያዛቸው የወያኔ/ኢህአዴግ መሪዎች የሚቀራቸው አንድ መውጫ ዘዴ የህዝቡን ትግል በለየለት አመጽና በደም ባህር የማስመጥ ርኩስ ስትራቴጂ እንደሆነ ሰሞኑን በይፋ እያሳዩን ነው፡፡ ይህ እንዲሳካላቸው ደግሞ የማይቀረው አካሄዳቸው ለኢህአዴግ አባላትና ለሰራዊቱም ሆነ ለፖሊሱና ለደህንነቱ ይህንን ህዝባዊ ንቅናቄ በነሱም ህልውና ላይ ያነጣጠረ አድርጎ በማቅረብ እነዚህ ወገኖች በአልሞት ባይ ተጋዳይነት ስሜት እስከመጨረሻው ከአገዛዙ ጎን ጸንተው እንዲቆሙ መሞከር እንደሆነ ግልጽ ነው፡፡ ይህንን አካሄዳቸውን ለማክሸፍ ደግሞ ባላሰለሰ ቅስቀሳ ህዝባዊው ትግል ከነዚህ ወገኖች ጋር ምንም ጸብ እንደሌለው፣ አላማው ብሄራዊ እርቅ የሰፈነባትና ለእነሱም የምትሆን ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን ለመመስረት መሆኑን ለማስጨበጥ መሞከርና በምንም አይነት የወያኔ/ኢህአዴግን መሪዎች ርኩስ ስትራቴጂ ሊያግዙ ከሚችሉ ቅስቀሳዎች መቆጠብ ያስፈልጋል ማለት ነው፡፡

እንዲህ አይነቱ አካሄድ ፖሊሱና ሰራዊቱ በደመ ነፍስ ከሚወስዷቸው ጸረ ህዝብ እርምጃዎች እንዲቆጠቡ፣ የኢህአዴግ አባል ድርጅቶች መሪዎችና አባላት ደግሞ በድርጅታቸው ውስጥ የህንን የጥቂቶች ጸረ ህዝብ ፖለቲካ ለመቃወምና ለማክሸፍ እንዲበራቱና ይህ ካልተሳካላቸው ደግሞ የህንን የጥፋት ድርጅት እየለቀቁ ከህዝቡ ትግል እንዲቀላቀሉ በሩን የሚከፍት አካሄድ በመሆኑ እንደ ትግልችን አንድ የማይናቅ ገጽታ አድርገን መውሰድ ይኖርብናል፡፡

ከዚህ ሁሉ አንጻር ሰሞኑን በሃገራችን የታዩት በጎ ክስተቶች ማንም ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅት ሳይመራቸው ‘ከታች’ ከህዝቡ ከራሱ በፈለቁና በያሉበት ‘ለትግል ተነስ’ የሚሉትን ህዝብ የህልውናም ሆነ የመብትና የማንነት ጥያቄዎች ጠንቅቀው በሚያውቁ በያሉበት የህዝቡን ችግርም ሆነ ህልም በሚጋሩ ዜጎች የሚቀነባበሩ ትግሎች ናቸው፡፡ በዚህ መልክ እየተከሰተ ያለውን በጎ ሂደት ለማገዝና ገፍቶ ለድል እንዲበቃ ለማድረግ ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች፣ ሌሎች ስብስቦችና ሃገር ወዳድ ዜጎች የሚጠበቅባቸውን ሚና ከሁለት አንጻር መጠቆም ይቻላል፡፡

አንደኛ በሰሞኑ ትግል ለተፈጠረው አዲስ ሁኔታ በሚመጥን መልክ ህዝባችን የቀደደውን ፈር በመከተል በውስጥም በውጭም ሃገር ወዳድና ዴሞክራሲያዊ የሆኑ ሃይሎች የወያኔን መሪዎች ቅስም የሰበረውን የህዝቦች ወንድማማችነት መንፈስ ለማገዝና ለማጎልበት በይፋ በአንድነት ቆመው ትግሉን ሲደግፉ መታየት ይኖርባቸዋል፡፡ ለምሳሌ በውጭ በብሄርና በህብረ በብሄር ደረጃ የተቋቋሙ የፖለቲካ ድርጅቶችና ሌሎች ስብስቦች የህዝቡን ትግል በመደገፍ ብቻ ሳይሆን በመካሄድ ላይ ያለውን አፈናና ግድያ በመቃወም የጋራ ሰላማዊ ሰልፎች ማካሄድ ይጠበቅባቸዋል፡፡ ይህ ሲደረግ ደግሞ በተቃዋሚው ጎራ አንዳንዶች አውቀውም ሆነ ሳያውቁ በሚነዟቸው ህዝብን ከህዝብ በሚያጋጩና ብሎም የወያኔ መሪዎችን የከፋፍለህ ግዛ ፖለቲካ በሚያግዙ ቅስቀሳዎች ሲሰማሩ እነዚህን አፍራሽ አካሄዶች በግልጽና በጋራ አውግዞ መውጣት ያስፈልጋል፡፡

ሁለተኛ ሁሉም የሚንቀሳቀስባቸው የህልውና፣ የማንነትም ሆኑ የመብት ጥያቄዎች ዘላቂ መፍትሄ የሚያገኙት የስርአት ለውጥ ተደርጎ ዴሞክራሲና ተጠያቂነት የሰፈኑባት ኢትዮጵያ እውን ስትሆን ብቻ ስለሆነ የህዝቡ ትግል ወደዚህ አገራዊ ግብ ለመድረስ ስለሚከተለው ቅደም ተከተል ወይም ሮድ ማፕና የሂደቱን መቋጠሪያ በተመለከተ አንድ የጋራ ስትራቴጂ ነድፎ ይህንን በትግል ላይ ላለው ህዝብ ማስጨበጥና አሁን በሚያሳየው ቆራጥነትና ብስለት ለዚህ ዘላቂና የጋራ አጀንዳ ከዳር እስከዳር ተንቀሳቅሶ በአንድ አቅጣጫ እንዲታገል መቀስቀስ ያስፈልጋል፡፡

የህዝቦች ወንድማማችነት ይለምለም!!!

መላ ኢትዮጵያ ሶሻሊስት ንቅናቄ (መኢሶን)

ነሃሴ 6 ቀን 2008 ዓ.ም.


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm
  • “ሙሽራው እስኪመጣ የምትቆይ ቤተክርስቲያን እናድርጋት” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ February 15, 2023 03:13 pm
  • በመዝገበ ቃላት የችጋር መጠሪያ የነበረችው ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ስንዴ ወደ ውጭ ላከች February 13, 2023 03:28 am
  • ውዝግቡን በሐዋሪያት መንገድ ለመፍታት ስምምነት ላይ ተደርሷል February 10, 2023 09:06 am
  • የሚከተልህ ሁሉ ወዳጅህ አይደለም – መልዕክት “ለመንፈሳዊው ቄሮ” መሪ ዘመድኩን በቀለ! February 10, 2023 12:48 am
  • በሰማዕትነት ጥሪ ቤተመንግሥቱን ባቋራጭ መቆጣጠር February 9, 2023 01:25 pm
  • የሲኖዶሱ ውዝግብ አካሄድና መጪው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ February 6, 2023 02:03 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule