• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በባሕርዳሩ ሰላማዊ ሰልፍ በትግሬ-ወያኔ ግፍ የተጨፈጨፉትን እንድናውቃቸውና እንድንዘክራቸው!

August 19, 2016 11:20 pm by Editor Leave a Comment

ዘረኛው የትግሬ ወያኔ የወልቃይት ጠገዴን የማንነት ጥያቄ ደግፈው በወጡ የባሕርዳሩ ሰላማዊ ሰልፍ በግፍ የገደላቸው ወገኖቻችን ዝርዝር በከፊል።

«የወልቃይት ጠገዴ የማንነት ጥያቄ፣ የእኛም የዐማራነት ጥያቄ ነው፣» ብለው እሑድ ነሐሴ 1 ቀን 2008 ዓም ላይ በባሕርዳር ከተማ፣ በሰላማዊ መንገድ ድምፃቸውን ለማሰማት በወጡ ዐማሮች ላይ፣ የትግሬ ወያኔ ዘረኛ ቡድን በርካታ፣ ሩቅ አሳቢ፣ ለሥራ የጓጉ፣ ላገርና ለወገን ታላቅ ተስፋ ሰንቅው የነበሩ የአያሌ ወጣቶችን ሕይዎት በግፍ ነጥቋል። በባሕርዳሩ ሰላማዊ ሰልፍ ወያኔ ከገደላቸው በርካታ ቁጥር ያላቸው ወጣቶች መካከል ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት በውስጥ የመረጃ ምንጮቻችን የከፊሎቹን አገኝቷል።

ከሰንጠረዡ ለመረዳት እንደሚቻለው፣ በግፍ ከተገደሉትና ዝርዝራቸውን ማወቅ ከተቻለው አርባ ዘጠኝ(49) ሰዎች ውስጥ፣ ዕድሜአቸው ሰላሳና ከዚያም በላይ የሆኑት ስምንት ( 8) ብቻ ነው። አርባ አንዱ (41) በወያኔ የግፍ አገዛዝ የተወለዱና ወያኔ ሲገባ ከአምስት ዓመት ዕድሜ የማይበልጡ መሆኑ በግልጽ ይታያል።  በመሆኑም  ያለፈውን ሥርዓት የማያውቁ፣ ያልኖሩበት፣ በትህምርትም ያልተማሩት በመሆኑ የሚናፍቁት አንዳች ነገር ይኖራ ተብሎ አይታሰብም።  ወጣቶቹ ሰዎች ናቸው እና እንደማንኛውም ሰብአዊ ፍጡር መልካም ነገርን፣ እንደሰው ዕኩል መታየትን፣ ጥሩና መልክ ነገሮችን የመመኘት፣ ራሳቸውን ከሌሎች አቻዎቻቸው ጋር አመዛዝኖ ለእኛ ለምን ሰብአዊ መብቶቻችን፣ ተዘዋውሮ የመሥራትና ያመኑበትን በግልጽ የመናገር፣ የመደራጀት፣ ወዘት መብትና ነፃነት እንነጠቃለን፣ ከዚህ ሁሉ በላይ ማንነታቸውን ለምን ይካዳል ብለው መጠየቃቸው ሰው ሆኖ በመፈጠራቸው ብቻ የተሰጣቸው መብት እንጂ፣ ያለፈ ሥርዓት የመናፈቅ ወይም ትምክህተኛ የመሆን ውጤት አይደለም።

በሌላም በኩል እነዚህ በወያኔ ዘመን ተወልደው፣ በርሱ የትምህርት ሥርዓት ያለፉ ወጣቶች ያነሱት የማንነት ጥያቄ ሥርዓቱ ገነባሁት ያለው «የነገዶች ዕኩልነትና ሰላም» አስገኘሁት እያለ የሚለፍፈው «ልማት» ውሸት መሆኑን ገላጭ ነው። የዘረኝነት ሥርዓቱ፣ ዐማራውን በጠላትነት ፈርጆ ያወጀበት የዘር ጥፋትና የዘር ማጽዳት ወንጀል፣ እየከፋ መምጣቱን፣ የዐማራው ወጣት ትውልድ ማንነታችን እናስከብር ብሎ በቁርጠኝነት መነሳቱን የሚያመለክት ነው። ባጭሩ ወያኔ  የወልቃይት ጠገዴን የማንነት ዕውነተኛ ጥያቄ «ያለፈው ሥርዓት ናፋቂዎች፣ ትምክህተኞች፣ ነፍጠኞች» እያለ ያልሆነ ስም የሚለጥፍባቸው ንፁሐን ዜጎች የራሱ ከፋፋይ፣ አጥፊና ዘረኛ ሥርዓት ውጤቶች፣ የዘረኛና ብልሹ አስተዳደሩ ውጤት መሆኑን፤ ይህንም ኢትዮጵያዊ ዜጋ ያልተቀበለው እንደሆነ የሚያሳይ አጉሊ መነፀር ነው።

በወያኔ አጋዚ ጦርና ከሕዝቡ መሀል ለዘመናት በኖሩና የባሕርዳር ሕዝብ እንደወገን በሚያያቸው፣ እነርሱ ግን እንደጠላት ቆጥረው  ለገዳዩ ቡድን መረጃ በማቀበል በተሰማሩት የትግሬ ነገድ አባሎች የተጨፈጨፉት ሰላማዊ ዜጎች፣ ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት ስማቸውን ለማግኘት የቻላቸው የሚከተሉት ናቸው። ለወራት ያህል በዘለቀው ሕዝባዊ እንቢተኝነት ሕይዎታቸውን ያጡ ወገኖቻችን ስምና ማንነት እየተከታተልን የማሳወቅ ተግባራችንን በንቃት ለመወጣት የምንችለውን ሁሉ እናደርጋለን። 

ተራ

ቁጥር

 

የተገዳይ ሙሉ ስም

 

ዕድሜ

 

መኖሪያ አድራሻ

1 ዕድሜዓለም ዘውዱ 27 ባሕር ዳር
2 ገረመው አበባው 25 ባሕር ዳር
3 ተፈሪ ባዩ 16 ባሕር ዳር
4 ሰሎሞን አስቻለ 25 ባሕር ዳር
5 ሙሉቀን ተፈራ 27 ባሕር ዳር
6 አደራጀው ኃይሉ 19 ባሕር ዳር
7 አስማማው በየነ 22 ባሕር ዳር
8 ታዘበው ጫኔ 21 ባሕር ዳር
9 አሥራት ካሣሁን 24 ባሕር ዳር
10 የሽዋስ ወርቁ 20 ባሕር ዳር
11 ብርሃን አቡሃይ 29 ባሕር ዳር
12 ሽመልስ ታዬ 22 ባሕር ዳር
13 አዛናው ማሙ 20 ባሕር ዳር
14 ሢሣይ አማረ 24 ባሕር ዳር
15 ሞላልኝ አታላይ 21 ባሕር ዳር
16 መሣፍንት አማራ 22 እስቴ
17 እንግዳው ዘሩ 20 ባሕር ዳር
18 ዝናው ተሰማ 19 ባሕር ዳር
19 ዋለልኝ ታደሰ 24 ባሕር ዳር
20 ይታያል ካሤ 25 ባሕር ዳር
21 እሸቴ ብርቁ 37 ባሕር ዳር
22 ሞገስ 40 ባሕር ዳር
23 አደራጀው ደሣለኝ 30 ባሕር ዳር
24 አበበ ገረመው 27 ጢስ ዐባይ
25 ማኅሌት 23 ባሕር ዳር
26 ተስፋዬ ብርሃኑ 58 ባሕር ዳር
27 ፈንታሁን 30 ባሕር ዳር
28 ሰጠኝ ካሤ 28 ባሕር ዳር
29 ባበይ ግርማ 26 ባሕር ዳር
30 አለበል ዓይናለም 28 ደብረማርቆስ
31 አብዮት ዘሪሁን 20 ባሕር ዳር
32 አበጀ ተዘራ 28 ወረታ
33 ደመቀ ዘለቀ 22 ወረታ
34 አለበል ሃይማኖት 24 ወረታ
35 ሰሎሞን ጥበቡ 30 ቻግኒ
36 ፍሥሃ ጥላሁን 25 አዲስ አበባ
37 ቅዱስ ሀብታሙ 16 አዲስ አበባ
38 በረከት ዓለማየሁ 28 ዳንግላ
39 ያየህ በላቸው 30 ዳንግላ
40 ዓለማየሁ ይበልጣል 27 ዳንግላ
41 በለጠ ካሤ 32 ደብረታቦር
42 ይህነው ሽመልስ 30 ደብረታቦር
43 ይበልጣል ዕውነቱ 24 ጢስ ዐባይ
44 ሀብታሙ ታምራት 27 ባሕር ዳር
45 ታደሰ ዘመኑ 26 አዴት
46 ሽመልስ ወንድሙ 28 ቡሬ
47 ዓይንአዲስ ለዓለም 24 ደብረወርቅ
48 እስቲበል አስረስ 19 አዴት
49 ሞገስ ሞላ 23 ባሕር ዳር

 


ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት      

ቅፅ ፬ ፣ ቁጥር ፳፭      

ሐሙስ ነሐሴ ፲፪ ቀን ፪ሺህ፰  ዓ.ም.  

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Bahir Dar Massacre, Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule