• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በባሕርዳሩ ሰላማዊ ሰልፍ በትግሬ-ወያኔ ግፍ የተጨፈጨፉትን እንድናውቃቸውና እንድንዘክራቸው!

August 19, 2016 11:20 pm by Editor Leave a Comment

ዘረኛው የትግሬ ወያኔ የወልቃይት ጠገዴን የማንነት ጥያቄ ደግፈው በወጡ የባሕርዳሩ ሰላማዊ ሰልፍ በግፍ የገደላቸው ወገኖቻችን ዝርዝር በከፊል።

«የወልቃይት ጠገዴ የማንነት ጥያቄ፣ የእኛም የዐማራነት ጥያቄ ነው፣» ብለው እሑድ ነሐሴ 1 ቀን 2008 ዓም ላይ በባሕርዳር ከተማ፣ በሰላማዊ መንገድ ድምፃቸውን ለማሰማት በወጡ ዐማሮች ላይ፣ የትግሬ ወያኔ ዘረኛ ቡድን በርካታ፣ ሩቅ አሳቢ፣ ለሥራ የጓጉ፣ ላገርና ለወገን ታላቅ ተስፋ ሰንቅው የነበሩ የአያሌ ወጣቶችን ሕይዎት በግፍ ነጥቋል። በባሕርዳሩ ሰላማዊ ሰልፍ ወያኔ ከገደላቸው በርካታ ቁጥር ያላቸው ወጣቶች መካከል ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት በውስጥ የመረጃ ምንጮቻችን የከፊሎቹን አገኝቷል።

ከሰንጠረዡ ለመረዳት እንደሚቻለው፣ በግፍ ከተገደሉትና ዝርዝራቸውን ማወቅ ከተቻለው አርባ ዘጠኝ(49) ሰዎች ውስጥ፣ ዕድሜአቸው ሰላሳና ከዚያም በላይ የሆኑት ስምንት ( 8) ብቻ ነው። አርባ አንዱ (41) በወያኔ የግፍ አገዛዝ የተወለዱና ወያኔ ሲገባ ከአምስት ዓመት ዕድሜ የማይበልጡ መሆኑ በግልጽ ይታያል።  በመሆኑም  ያለፈውን ሥርዓት የማያውቁ፣ ያልኖሩበት፣ በትህምርትም ያልተማሩት በመሆኑ የሚናፍቁት አንዳች ነገር ይኖራ ተብሎ አይታሰብም።  ወጣቶቹ ሰዎች ናቸው እና እንደማንኛውም ሰብአዊ ፍጡር መልካም ነገርን፣ እንደሰው ዕኩል መታየትን፣ ጥሩና መልክ ነገሮችን የመመኘት፣ ራሳቸውን ከሌሎች አቻዎቻቸው ጋር አመዛዝኖ ለእኛ ለምን ሰብአዊ መብቶቻችን፣ ተዘዋውሮ የመሥራትና ያመኑበትን በግልጽ የመናገር፣ የመደራጀት፣ ወዘት መብትና ነፃነት እንነጠቃለን፣ ከዚህ ሁሉ በላይ ማንነታቸውን ለምን ይካዳል ብለው መጠየቃቸው ሰው ሆኖ በመፈጠራቸው ብቻ የተሰጣቸው መብት እንጂ፣ ያለፈ ሥርዓት የመናፈቅ ወይም ትምክህተኛ የመሆን ውጤት አይደለም።

በሌላም በኩል እነዚህ በወያኔ ዘመን ተወልደው፣ በርሱ የትምህርት ሥርዓት ያለፉ ወጣቶች ያነሱት የማንነት ጥያቄ ሥርዓቱ ገነባሁት ያለው «የነገዶች ዕኩልነትና ሰላም» አስገኘሁት እያለ የሚለፍፈው «ልማት» ውሸት መሆኑን ገላጭ ነው። የዘረኝነት ሥርዓቱ፣ ዐማራውን በጠላትነት ፈርጆ ያወጀበት የዘር ጥፋትና የዘር ማጽዳት ወንጀል፣ እየከፋ መምጣቱን፣ የዐማራው ወጣት ትውልድ ማንነታችን እናስከብር ብሎ በቁርጠኝነት መነሳቱን የሚያመለክት ነው። ባጭሩ ወያኔ  የወልቃይት ጠገዴን የማንነት ዕውነተኛ ጥያቄ «ያለፈው ሥርዓት ናፋቂዎች፣ ትምክህተኞች፣ ነፍጠኞች» እያለ ያልሆነ ስም የሚለጥፍባቸው ንፁሐን ዜጎች የራሱ ከፋፋይ፣ አጥፊና ዘረኛ ሥርዓት ውጤቶች፣ የዘረኛና ብልሹ አስተዳደሩ ውጤት መሆኑን፤ ይህንም ኢትዮጵያዊ ዜጋ ያልተቀበለው እንደሆነ የሚያሳይ አጉሊ መነፀር ነው።

በወያኔ አጋዚ ጦርና ከሕዝቡ መሀል ለዘመናት በኖሩና የባሕርዳር ሕዝብ እንደወገን በሚያያቸው፣ እነርሱ ግን እንደጠላት ቆጥረው  ለገዳዩ ቡድን መረጃ በማቀበል በተሰማሩት የትግሬ ነገድ አባሎች የተጨፈጨፉት ሰላማዊ ዜጎች፣ ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት ስማቸውን ለማግኘት የቻላቸው የሚከተሉት ናቸው። ለወራት ያህል በዘለቀው ሕዝባዊ እንቢተኝነት ሕይዎታቸውን ያጡ ወገኖቻችን ስምና ማንነት እየተከታተልን የማሳወቅ ተግባራችንን በንቃት ለመወጣት የምንችለውን ሁሉ እናደርጋለን። 

ተራ

ቁጥር

 

የተገዳይ ሙሉ ስም

 

ዕድሜ

 

መኖሪያ አድራሻ

1 ዕድሜዓለም ዘውዱ 27 ባሕር ዳር
2 ገረመው አበባው 25 ባሕር ዳር
3 ተፈሪ ባዩ 16 ባሕር ዳር
4 ሰሎሞን አስቻለ 25 ባሕር ዳር
5 ሙሉቀን ተፈራ 27 ባሕር ዳር
6 አደራጀው ኃይሉ 19 ባሕር ዳር
7 አስማማው በየነ 22 ባሕር ዳር
8 ታዘበው ጫኔ 21 ባሕር ዳር
9 አሥራት ካሣሁን 24 ባሕር ዳር
10 የሽዋስ ወርቁ 20 ባሕር ዳር
11 ብርሃን አቡሃይ 29 ባሕር ዳር
12 ሽመልስ ታዬ 22 ባሕር ዳር
13 አዛናው ማሙ 20 ባሕር ዳር
14 ሢሣይ አማረ 24 ባሕር ዳር
15 ሞላልኝ አታላይ 21 ባሕር ዳር
16 መሣፍንት አማራ 22 እስቴ
17 እንግዳው ዘሩ 20 ባሕር ዳር
18 ዝናው ተሰማ 19 ባሕር ዳር
19 ዋለልኝ ታደሰ 24 ባሕር ዳር
20 ይታያል ካሤ 25 ባሕር ዳር
21 እሸቴ ብርቁ 37 ባሕር ዳር
22 ሞገስ 40 ባሕር ዳር
23 አደራጀው ደሣለኝ 30 ባሕር ዳር
24 አበበ ገረመው 27 ጢስ ዐባይ
25 ማኅሌት 23 ባሕር ዳር
26 ተስፋዬ ብርሃኑ 58 ባሕር ዳር
27 ፈንታሁን 30 ባሕር ዳር
28 ሰጠኝ ካሤ 28 ባሕር ዳር
29 ባበይ ግርማ 26 ባሕር ዳር
30 አለበል ዓይናለም 28 ደብረማርቆስ
31 አብዮት ዘሪሁን 20 ባሕር ዳር
32 አበጀ ተዘራ 28 ወረታ
33 ደመቀ ዘለቀ 22 ወረታ
34 አለበል ሃይማኖት 24 ወረታ
35 ሰሎሞን ጥበቡ 30 ቻግኒ
36 ፍሥሃ ጥላሁን 25 አዲስ አበባ
37 ቅዱስ ሀብታሙ 16 አዲስ አበባ
38 በረከት ዓለማየሁ 28 ዳንግላ
39 ያየህ በላቸው 30 ዳንግላ
40 ዓለማየሁ ይበልጣል 27 ዳንግላ
41 በለጠ ካሤ 32 ደብረታቦር
42 ይህነው ሽመልስ 30 ደብረታቦር
43 ይበልጣል ዕውነቱ 24 ጢስ ዐባይ
44 ሀብታሙ ታምራት 27 ባሕር ዳር
45 ታደሰ ዘመኑ 26 አዴት
46 ሽመልስ ወንድሙ 28 ቡሬ
47 ዓይንአዲስ ለዓለም 24 ደብረወርቅ
48 እስቲበል አስረስ 19 አዴት
49 ሞገስ ሞላ 23 ባሕር ዳር

 


ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት      

ቅፅ ፬ ፣ ቁጥር ፳፭      

ሐሙስ ነሐሴ ፲፪ ቀን ፪ሺህ፰  ዓ.ም.  

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Bahir Dar Massacre, Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule