• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ወገንን በመርዳት ለኢትዮጵያ ያለን ፍቅር ይገለጻል!

January 25, 2014 05:39 am by Editor Leave a Comment

የዶክተር ካትሪን ሃምሊን እና የባለቤታቸው በዶ/ር ሬጅ ሃምሊን ግማሽ ክፍለ ዘመን የተጠጋው በጎ ምግባር የሚያሳዩ ድርሳናትን ስፈታትሽ አድሬ አረፋፈድኩበት ። “የፊስቱላ ተጠቂዎች የተስፋ ታሪክ ” በሚል በአንድ ወቅት በፊሱትላ በሽታና በዶክተር ካትሪን እና በቤተሰባቸው በስራ ባልደረቦቻቸው ተጋድሎ ዙሪያ የቀረበ በእጀ ነበረ  ከሲድኒ አውስትራልያ መስፍን ማሞ ተሰማ ያቀረበልንን ድንቅ በበቂ መረጃ ደጋግሜ አነበብኩት። “ዶ/ር ካትሪን ሀምለን በአሁን ሰአት በአውስትርሊያ ግዛት በአንድ የባህር ዳርቻ በሚገኘው ምቾታማና የናጠጠ መኖሪያ ቤታቸው ውስጥ ቀሪውን የህይወት ዘመናቸውን እንኳ ለማሳለፍ አልፈለጉም።

hamlinዛሬም በዚህ እድሜያቸው ከሃገር ሃገር እየዞሩና እየተንከራተቱ ዕርዳታ በመጠየቅ የፊስቱላን በሽታ ከምድረ ኢትዮጵያ ለማስወገድ እንዲቻል የፋይናንስ፤ የማቴሪያልና የባለሙያ ኃይልን እያደራጁ ይገኛሉ።!”  ይላል የመስፍን ነጋሽ መረጃ!  እውነት ነው!  ስለ ዶር ካትሪን ዘመን ተሻጋሪ ስራዎች ታዋቂዋን ቶክ ሾው አቅራቢ ኦፕራን ጨምሮ ከተለያዩ አለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ጋር ያደረጓቸውን ቃለ መጠይቆች ዙሪያ ዳሰሳ አደረግኩ  ። ጥናታዊ ፍልሞችንም ተመለከትኩ  ! የእኛዎቹ ምንዱባን  ልብን ይነካሉ … የነጯ እምቤት ስራ ነፍስን በተስፋ ያድሳል!  የእኛ ኑሮ ውሎ አዳር ያሳስባል እና አሰብኩት! እናም የእኒህ እመቤት ውለታ ቢከብደኝ የእኛ ነገር ቢያሳስበኝ እኔው ራሴ ለራሴን መላልሸ ኢትዮጵያዊነት ምን ማለት ነው ?  ብየ ጠየቅኩት!

ሩቅ ተጉዠ ሃገር ቤት ያሉ የእኛ ሃኪሞችና በሰብአዊ እርዳታ መስሪያ ቤቶች በከባድ ሃላፊነት ተቀምጠው ለወገን በተለመነው እርዳታ የበለጸጉ የማውቃቸው የምናውቃቸውን ወገኖች በአይነ ህሊናየ አስታወስኩ ። በዙሪያየ ካለው የቅርብ ወራት ትዝታ አዝግሜም በሳውዲ የኮንትራት ስራ መጥተው የተለያዩ ጥቃቶች ደርሰውባቸው የጅዳና የሪያድ መጠለያዎች ተሞልተው የከረሙትን ተፈናቃይ ወገኖችና ከቅርብ ርቀት በባንዴራና በመፈክር አሸብርቀው ስብሰባ ድግስ ሲፈራረቅባቸው የከረሙትን አዳራሾች አስታወስኩ! ጉራጌ ፣ አማራ ፣ ትግሬ ፣ኦሮሞ ሁሉንም የሃገሬ ብሔር መወከል የሚችሉ ግፉአን የከፋ በደል ደርሶባቸው ቅስማቸው ተሰብሮ ውለው በሚያደረሩበት ግቢ ጉራጌ ፣ አማራ ፣ ትግሬ ፣ኦሮሞ እና በቀረው ብሔር ብሔረሰብ የቋቋሙት የልማት ማህበራትና ድርጅቶች ዲል ያለ ድግስ ደግሰው የተወለዱ፣ የተቋቋሙበትን፣ የአመት ሪፖርት ገንዘብ ማሰባሰቢያ ድግስ ዲል አድርገው ሲደግሱ የብሔር ብሔረሰብ ልጆችን እንባ መጥረጉ ቀርቶ ችግሩን አንስተው መወያየት የተሳናቸውን አጋጣሚ በንጽጽር አስታወስኩት።

እንዲህ እንዲህ እያልኩ ብዙን አስታወስኩ ።  ” አይ የእኛ ነገር !” አልኩ ከትንነት በስቲያ ወዳጃችን አርአያ ተስፋ ማርያም አንድ መጣጥፍ እንደገና ታውሶኝ … የአርአያ ተስፋ ማርያም ከዋሽንግተን ሆኖ እንደ ሸረሪት ድር በሚያገናኘን የኢንተርኔት መረብ አማካኝነት በፊስቡክ ገጹ የለቀቀው ገጠመኝ  እንዲህ የሚል አለበት “በዲሲ 13ኛው መንገድ አመሻሽ ላይ በእግሬ ሳዘግም በስተግራ በኩል ካለ የተንጣለለ አዳራሽ አንድ ድምፅ ከጆሮዬ ጥልቅ አለ። በአማርኛ የሃይማኖት ስብከት ሲሆን ሰባኪው፥ «ኢየሱስ የተቸገሩ፣ የተራቡ፣ የታመሙ..እርዱ ይላል..» እያለ በአዳራሹ ለተሰበሰበው ህዝብ (ሃበሻ) ይሰብካል። በአዳራሹ ሁለተኛ መግቢያ በኩል ሁለት ሰዎች ጥግ – ጥግ ይዘው በዛ ቁር ኩርምት ብለዋል። … ተጠግቼ አናገርኳቸው። «ለምን እዚህ እንዲያስጠጓችሁ አትጠይቋቸውም?.» ስል ጠየኳቸው። ሙላቱ « ወንድሜ መኖራችንን ካወቁ ፖሊስ ጠርተው ያባርሩናል። ከሰው አይቆጥሩንም።fistula1 እያንቋሸሹ፣ ሊደበድቡን ይቃጣቸዋል። ህይወት ፊቷን ስታዞርብህ ምንም ያልበደልከው ወገንህ ተደርቦ ለምን አሳርህን እንደሚያሳይህ ይገርመኛል!» አለኝ። ንግግሩ አንጀት ይበላል። … እምነት በተግባር ካልታጀበ ምን ዋጋ አለው?…ሰባኪው ስለየትኞቹ ችግረኞች ነው የሚናገረው?..አፍንጫው ስር የወደቁ ወገኖችን ካለመርዳቱ ባሻገር ጭራሽ ለአይን መጠየፍን ምን ይሉታል?..የሃይማኖቱ ተከታዮችስ ይህን እያዩ ማለፋቸው ምን ይባላል?.. ” ይለናል አርአያ በሃብታሟ ሃገር በአሜሪካ የብዙሃን መናህሪያ በዋሽንግተኗ በእኛ መንደር የሚታየውን ምስቅልቅል ህይዎት ሲያስቃኘን ።  …ይህም ያማል!

ይህንና ያንን አውስቸ በራሳችን እየሆነ ባለው አፍሬ ተሸማቀቅኩ ፣ አዛውንቷ የሰው ሃገር ሰው ዶር ካትሪን ባከበሩት 90ኛ አመት የልደት መታሰቢያ ግን መልካም ስራቸውን አውስቸ ደምቅኩ ። ዶ/ር ካትሪን ከልጅነት እስከ እውቀት ለእኛ በኖሩባቸውን ረጅም አመታት የደገፉዋቸውን ወደ 40 ሽህ የሚጠጉ ኢትዮጵያን የማህጸን (የፊስቱላ) ህሙማንን የሰመረ ህይዎት መልሸ መላልሸ አሰብኩት ። ማነጻጸር የማይመቸውን እያነጻጸርኩ ለምን እያልኩ ራሴን ወዘወዝኩት!   “ኢትዮጵያን እንወዳለን!” ለማለት ሰንደቅ ባንዴራ አረንጓዴ ቢጫ ቀለሙን በመላብስ ጌጣ ጌጦች የምንደምቀውን የእኛን ስራ አስታውሸ ውስጤን አንዳች ክፉ ሰሜት ሸነቁጠው … እናም ኢትዮጵያ ማለት ምን ማለት ነው? ብየ ራሴ ላጠየቅኩት ራሴው በመመለስ ቢያንስ ለእኛ ሲሉ የሚሰሩትን በመደገፉ እንበርታ ለማለት ስንደረደር ኢትዮጵያ በሚለው መልስ ይሆናል ያልኩትን የሆዴን ለመናገር መሞነጫጨር ጀመርኩ…

ኢትዮጵያ ማለት ስም ነው ፣ የማይበጥ የማይቧጠጥ ! ምሳሌ ነው ፣ መለያ ነው  ! ኢትዮጵያ ማለት ስም ነው መለያ ፣ በምድሯ የታጨቀው ወገን መታወቂያ ! ኢትዮጵያ ማለት ሰው ነው በቀየዋ የሚኖረው ፣  መሬቷን አርሶ ግሮ ጥሮ የሚኖረው ፣ ኢትዮጵያ ማለት ተምሮ ፣ አስተምሮ ፣ ተመራምሮ ተስፋን ሰንቆ የሚኖረው !  “ኢትዮጵያን እወዳለሁ!” የሚለው ወገኑን ለመታደግ አለፋ ስቅየት የሚከፍለው !  ለክብር ነጻነቷ ቀናኢው ኢትዮጵያ ማለት እሱ ነው በምድሯ የበቀለው ! “ኢትዮጵያን እወዳለሁ!” በሚል ደስኳሪው  ፣ ሃገሩን አሳልፎ ሰጭው ፣ ወገኑን በመታደግ ፋንታ ዘራፊው፣ በራሱ ወገን የሚጨቆን የሚረገጠው  ፣ የሚጨቁነው!  ወገኑን መደገፍ ያቃተው …  ኢትዮጵያዊ እሱ ነው ደጉም ክፉውም ሰው…  !

ኢትዮጵያ ማለት ተራራ ምድር ሸንተረሩ፣ ቆላው፣ ደጋው፣ ወይና ደጋው፣ ለገዛው የሚገዛው መሬት፣ አለያም በተቀደደለት የሚፈሰው ውሃ ማለት አይደለም ኢትዮጵያዊነት ! ኢትዮጵያዊነት ክብሩ ስሙ ነው የሰው ፣ የህዝብ የወገኑ … !  ኢትዮጵያን መውደድ ፣ ባንዴራን ማፍቀር ማለት ህዝብ ወገንን መውደድ፣ መደገፍ ፣ማበልጸግ ማለት ካልሆነ ፍቅር መውደዱ ከንቱ ነው … !

እናማ “ኢትዮጵያ ሃገራችን እንዎዳለን? ”  ካልን በተግባር እናሳየው ! ባገኘነው አጋጣሚ ሁሉ ወገንን በመርዳት ፍቅራችን በድጋፍ እንግለጸው ! የዶር ካትሪንን እና የቀሩትን ፈና ወጊ የሰው ሃገር ሰው ስራዎች ተመልከቱ ! ዛሬ ያነሳሳናቸውን እመቤት በጎ ምግባር ብንመረምረው ሰብዕና አስገድዷቸው ከሃገረ አውስትራልያ በለጋ የልጅነት እድሜ ጀምሮ ዛሬ እስከሚከበረው የ90ኛ እድሜያቸው ፊስቱላን ለማጥፋት ያልፈነቀሉት ድንጋይ የለም ! … ባላቻ ጋብቻና በአስገድዶ መድፈር እኛው ባጠፋነው ጥፋት ፣ በማህጸን በሽታ fistula2በለጋ እድሜ ለሚሰቃዩ እህቶች እና እናቶች ህይዎት ትንሳኤን እያበሰሩ ግማሽ ክፍለ ዘመን የተጓዙ ሃኪም ናቸው! ዶር ካትሪን ፊስቱላን ከእኛ ሃገር ለማጥፋት የጀመሩት ጉዙ በእኛ ካልታገዘ የትም አይደርስም ” ባይባልም ቢያንስ የመልካሙ ዘመቻቸው አካል በመሆን ሰብዕናችን እናሳይ ዘንድ ግድ ይለናል!

“አብዛኛውን እድሜዬን ያሣለፍኩት ኢትዮጵያ ውስጥ ነው። ሌላ ሃገር ኖሬ አላውቃም። ከእንግዲህ ምን አልባት አንድ አመት ወይም አምስት አመት ልኖር እችል ይሆናል። እኔ ካለፍኩ በኋላ የጀመርነውን ሥራ ግቡን ሳይመታ እንዳታቆሙ አደራ!ፊስቱላን ከኢትዮጵያ ገጽ ማጥፋት አለብን።” በማለት የተናገሩት ዶር ካትሪን በኦክቶበር 2009 በአውስትራሊያ ርዕሠ ከተማ ካንቤራ ውስጥ የሳቸውን የኢትዮጵያ ቆይታ ተመርኩዞ በተሰራውን ዶክመተሪ ፊልም የምረቃ ዝግጅት የተናገሩት ቢሆንም ካትሪን በቀረቡባቸው መድረኮች ሁሉ ፊስቱላን በታዳጊ ሃገሮች ለማጥፋት ያላቸውን ቁርጠኝነት አመላክተዋል።

አዎ እውነት ብለው ፣ ስለእውነት እየሰሩ ያሉት እናት የዶ/ር ካትሪንን ፊስቱላ ከሃገረ ኢትዮጵያ ለማጥፋት እንቅስቃሴ እደግፋለሁ!

ዶ/ር ካትሪን እርስዎስ ለኢትዮጵያ እንኳንም ተወለዱ!

እናታችን  ዶ/ር ካትሪን ሃምሊን! እርስዎስ ለኢትዮጵያ እናቶች እንኳንም ተወለዱ!

አክባሪዎ

ነቢዩ ሲራክ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Social Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእምዬ ምኒልክ አዳራሽ October 30, 2023 10:27 am
  • የኢትዮጵያ መከላከያ መሥራች አጼ ምኒልክ መሆናቸውን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ተናገሩ October 26, 2023 01:30 pm
  • ጥቅምት 15 ለምን? October 26, 2023 01:29 am
  • “በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት” October 26, 2023 12:57 am
  • “ውትድርና ሕይወቴ ነው” October 26, 2023 12:13 am
  • መከላከያ በሁሉም መስክ ኢትዮጵያን የሚመጥን ኃይል እየገነባ ነው October 20, 2023 05:07 pm
  • “ሁሉም ኢትዮጵያዊ ትምህርት ቤት እኩል ነው በችሎታው ነው እንጂ የሚመዘነው” ፕ/ር ብርሃኑ October 20, 2023 04:47 pm
  • 42 የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አመራሮች እና ሠራተኞች ታሰሩ October 18, 2023 04:29 pm
  • በተማሪዎች ፈተና ውጤት ለታየው ውድቀት ትምህርት ሚ/ር ኃላፊ መሆን አለበት ተባለ October 18, 2023 04:00 pm
  • ቀይ ባሕር እና ዓባይ “የኅልውና ጉዳይ ናቸው”፤ “መተንፈሻ ወደብ ያስፈልገናል” October 13, 2023 10:04 pm
  • ከ3,106 ትምህርት ቤቶች 1,328ቱ (44%) አንድም ተማሪ አላሳለፉም October 10, 2023 01:51 pm
  • “አቋጥሬ” በአማራ ክልል እያጫረሰ ነው፤ ” ኑሮውን መቋቋም አልቻልንም ” ነዋሪዎች October 10, 2023 09:07 am
  • እሸቴ አሸባሪ፤ ቲዲኤፍ/ትሕነግ “ሰማዕት” – የዘመናችን ጉድ! October 7, 2023 06:47 am
  • በወልቃይት 1.1ሚሊዮን ኩንታል ሰሊጥ ለመሰብሰብ ከ1 ሚሊዮን በላይ ሠራተኛ ይፈለጋል September 27, 2023 10:42 am
  • በአማራ ክልል ሰላም ዕጦት ከ90.5 ቢሊዮን ብር በላይ ፕሮጀክቶች ቆመዋል September 27, 2023 08:41 am
  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule