• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ያለ ነጻ ሚዲያ – ምርጫ ወይስ ቁማር?

January 21, 2015 01:51 am by Editor 3 Comments

* ኢህአዴግ አሸነፈ፤ ፋና መሰከረ!

ምርጫ ያለ ነጻ ሚዲያ ተግባራዊ ሊሆን እንደማይችል ዓለምአቀፉ የሰብዓዊ መብት ተመልካች (Human Rights Watch) በያዝነው ሳምንት ማገባደጃ አካባቢ በኢትዮጵያ የሚዲያ ነጻነትን አስመልክቶ አጠቃላይ ዘገባ እንደሚያወጣ ተሰማ፡፡

ለጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ መረጃውን ያቀረቡና ከዘገባው ጋር ተዛማጅነት ክፍሎች እንደተናገሩት የሰብዓዊ መብት ድርጅቱ ይህንን ዘገባ ያጠናቀረው በተጨባጭ ከሚዲያ ጋር በተያያዘ ሰለባ የሆኑትን በሚዲያው መስክ የተሰማሩትን በማነጋገርና የመጀመሪያ ደረጃ መረጃ በመሰብሰብ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል፡፡

ዘገባው ከዚህ በፊት ከወጡት ዘገባዎች ለየት ባለ መልኩ በፕሬስ ሚዲያው ላይ የተሰማሩትን ክፍሎች በስፋት የዳሰሰ ነው፡፡ በተለምዶው በጋዜጠኞች ላይ የሚደረገው አፈና በብዙ መልኩ የሚነገር ሲሆን በዚህ ዘገባ ግን ኢህአዴግ በአሳታሚነት፣ በአከፋፋይነት፣ በአታሚነት፣ በሻጭነት (አዟሪነት)፣ ወዘተ የተሰማሩትን እንዴት ስልታዊ በሆነ መልኩ እንደሚያዳክም፣ እንደሚያፍን፣ እንደሚያሰቃይና ባጠቃላይ ከሜዳው እንደሚያስወግድ የሚያስረዳ እንደሚሆን ጎልጉል ካገኘው መረጃ ለመገመት ተችሏል፡፡

በመጪው ግንቦት ከሚካሄደው ምርጫ ጋር በማያያዝ ይወጣል ተብሎ የሚጠበቀው ይህ ዘገባ በተለይ የኢህአዴግን ቋት የሚሞሉ ለጋሽ አገራት፣ ዓለምአቀፍ የፍትሕ አካላት፣ የሲቪክ ማኅበረሰቦች፣ ወዘተ ከወዲሁ ግንዛቤ ይዘው ኢህአዴግ አደርገዋለሁ ለሚለው “ዴሞክራሲያዊና ፍትሃዊ” ምርጫ ያለ ነጻ ሚዲያ ተሳትፎ እንዴት ውጤት አልባ እንደሆነ የሚያስረዳና ጠለቅ ያለ ግንዛቤ የሚያስጨብጥ እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡

elec tionበዘንድሮው ምርጫ ባልተጠበቀና ለመቀበል በሚያስቸግር መልኩ የአውሮጳ ኅብረት “በጀት የለም” በሚል ምርጫውን አልታዘብምም ብሏል፡፡ በይፋ የተሰጠው ምክንያት ይህ ቢሆንም ጉዳዩ የበጀት ሳይሆን “ኢህአዴግ ከኢህአዴግ ጋር የሚያደርገውን የ99.6 በመቶ የምርጫ ውጤት መታዘብ በራሱ ያስታዝባል” በሚል ነው ኅብረቱ ምርጫ መታዘቡን በቅድሚያ ትዝብት የተወው በማለት የተሳለቁ መኖራቸው ተሰምቷል፡፡ ሆኖም ግን ኢህአዴግ በበኩሉ “ባትታዘቡ ምን ገደደኝ” በማለት ኅብረቱ ምርጫውን ለመታዘብ አለመፈለጉን በአብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ትዝብት አልፎታል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም በዚህ ስለ ሚዲያ ነጻነት በሚያትተው አዲስ ዘገባና በኅብረቱ ውሳኔ ዙሪያ ኢህአዴግ “ዓለምአቀፋዊ ሽልማት ባገኙ የዘርፉ ባለሙያዎቹ” ተጠቅሞ ኢትዮጵያ ውስጥ እንዴት ባለ “ነጻነት” የሚዲያ ሥራ እንደሚሠሩ በነዚሁ “ሚዲያዎች” ምላሽ እንደሚሰጥ ይጠበቃል፡፡

የአውሮጳ ኅብረትን “ምርጫ አልታዘብም” የማለት ውሳኔን በተመለከተ ከጉዳዩ ጋር ቅርበት ያላቸው ለጎልጉል እንደተናገሩት ኅብረቱ እዚህ ውሳኔ ላይ የደረሰው ከበጀት እጥረት ሳይሆን እየከረረና እየመረረ የመጣውን የኢህአዴግን አምባገነንነት፣ በቀደሙት “ምርጫዎች” የተከሰተውን ዓይንአውጣ ቅጥፈት እንዲሁም የኢህአዴግን የሞራል ዝቅጠት በማገናዘብና ከተሞክሮ በመነሳት የግንቦቱን ምርጫ አስቀድሞ በማጣጣል ዋጋ እንደማይሰጠው ከመናገር አኳያ ነው በማለት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡

ይህንን አስደንጋጭ የአውሮጳ ኅብረት ማዕቀብ ተከትሎ የሰብዓዊ መብት ተመልካቹ ድርጅት በማስረጃ የተደገፈ ዘገባ ከምርጫው በፊት አስቀድሞ ማውጣቱ ታስቦና ታቅዶ የተደረገ ብቻ ሳይሆን የአውሮጳ ኅብረትን እነማን ይከተሉታል የሚል ጥያቄ አስነስቷል፡፡

በግንቦት 2007 አካሂደዋለሁ ለሚለው ምርጫ ኢህአዴግ አጋጣሚውን ተጠቅሞ የውጭ ምንዛሬ ኮሮጆውን እንዲሞሉለት ከአውሮጳ ኅብረት በተጨማሪ ሌሎች አገራትን በተናጠል መለመኑ ይታወቃል፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. እምሩ ዘለቀ says

    January 20, 2015 07:07 pm at 7:07 pm

    ምርጫ የሚባለው ቃል በኢትዮጵያ ዉሎም አያዉቅ፤ አምባገነን ወንበዴዎች የነገሡባት አገር ናት፤ እጅ አዙር የፈረንጆችና ሌሎች የሚገዟት አገር ሁናለች፤ በዚህ አኳሆን ከቀጠለች ህልዉናዋ በጣም ያጠርጥራል፤ ያለዉን ችግር እያወቅን፤ በግልጽ እየተነገርን፤ በግልጽ እየተሰደብን፤ በግልጽ እየተዋረድን፤ በግልጽ እየተገደልን፤
    አንሰማም አናይም አናዉቅም እያልን በራሳችን ላይ ፈረደን የወሬ ቋት ሁነናል፤
    ምርጫ ያሰፈልገናል ወይ፧

    Reply
    • Daniel G/ says

      January 21, 2015 11:12 pm at 11:12 pm

      Kemotnma koytoal

      Reply
  2. dokele says

    January 22, 2015 06:52 am at 6:52 am

    weneteme yewenbede merri

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule