• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ትግሬ ትጠላለህ”

October 7, 2014 12:39 am by Editor 1 Comment

. . . ነፍሱን አይማርና! ያ! ቀጣፊ ከንቱ – የሂትለሩ ጉብልስ፣
አሳልፎ ሄደ፤ መሰሪ ትምህርቱን – ለበረከትና…ለነ አቶ ሽመልስ፤
እነሱም በተራ፣ ለታችኛው አሽከር ነጭ ውሸቱን ዘርተው፣
አጨዱት. . .፣ ከመሩት. . .፣ ማተብ-አልባ አድርገው፤
ከወያኔ ካድሬ፣ የውሸት ፋብሪካ፣ ተመርታ የወጣች፣
የዘረኞች ቋንቋ፣ “ትግሬ ትጠላለህ” የሚሏት ቃል አለች፤
ያገር ወዳዶችን ተቃውሞ ማስቆሚያ፣
በይሉኝታ ገመድ ሸብቦ ማሰሪያ. . .፣
ሆና ታገለግል ዘንዳ የተቃኘች፣
የጥላቻ ዜማ፣ ለጆሮ እምትቀፍ፣ ጩኸት የቁራዎች።

. . . እዩትማ እንግዲህ፣ ወደ ውስጥ ሲሰምጥ፣
መብሰሉን ሲያቅተው፣ ሲላወስ እንደ ሊጥ፣
ራሱ በፈጠረው፣ ራሱን አስጨንቆ፣ ጭቃ ሲንከባለል፣
እኩዮቹን ክዶ፣ ራሱን አሳንሶ፣ ሚጢጢዋን ሲያክል፤
ስልጣኑ አስክሮት፣ የግፍ ሃብት ቆዝሮት፣
ንቀት አሳውሮት፣ ህሊናውን ደፍኖት. . .፣
ደግሞ ከእሱ ብሶ፣ “ጅራፍ ገርፎ ሲጮኽ. . .፡
ይለኛላ እኔኑ፣ “ትግሬ ትጠላለህ”¡

. . .ንገረኝ ካልክማ፣ አንተ ነህ ጥላቻ፣ የጥላቻ ምንጩ፣ ህዝብ የምትጠላ፣
የይሉኝታ ደሃ፣ ምግባረ-ብልሹ፣ የዘመን አሽክላ!
አይገባህም እንጂ፣ ለመቻቻል ብሂል ስንት ዋጋ ከፈልኩ፣
ይኸው አንተን እንኳን፣ ሁለት አስርት ታገስኩ፤
ከያዘህ አባዜ ብትላቀቅ ብዬ፣
ታጥቦ ጭቃነትህን ሲያውቀው ልቦናዬ፤

እኔማ እንዴት ልጥላ! አብሮ አደጎቼን፣
እህት ወንድሞቼን፣ እናት አባቶቼን፣ ዘመድ ስጋዎቼን፣
ወዳጅ ጎረቤቴን. . . የሃገሬን ልጆች፣
የአጥንቴን ክፋይ፣ የደሜን ቅጅዎች፤
እንዴት ብዬ ልጥላ?!

. . . ይጠየቃ አክሱም፣ የቆመው ሐውልቱ፣
የዘመናት ታሪክ፣ ስረ-መሰረቱ፤
ትጠየቅ እምዬ፣ ወላዲት ማሪያሟ፣
የጽላተ-ሙሴ፣ ማደሪያ ጽዮኗ፤
ትጠየቅ ማይጨው፣ ትመስክር አድዋ፣ የታሪክ ማማዋ፣
ያያቶቼ. . . አጥንት ታዛ ከለላዋ፤
ካሻህም ላስመስክር፣ የሰው እማኝ ልጥራ፣ ለማተብ የቆሙ፣
ከዘመናት ታሪክ..እስካለንበቱ . . . በክብር የታደሙ፤
ሲዘከር፣ ሲተረክ፣ ሲጠራ፣ ሲወሳ . . . ዝነኛ ስማቸው፣
ምንኛ እንደምከንፍ፣ ለወገን ፍቅራቸው!
. . . አሉላ፣ ዮሃንስ፣ ዘርዓይ፣ አብርሃ፣ አውዓሎም፣ ሐጎስ፣
ገ/ሕይወት፣ አስገዶም፣ ባህታ፣ አሰገድ፣ ገ/መድኅን፣ ኪሮስ፣
ጋይም፣ አረጋዊ፣ ዘርዑ፣ ደበሳይ. . .፣
አቤሰሎም፣ አርዓያ፣ ግደይ፣ ገብረ-ተንሣይ. . .፤
አደይ፣ አታክልቲ፣ ጸሐይቱ፣ ሐዳስ. . .፣
ጽዮን፣ ትብለጽ፣ ምጽላል፣ አብርኸት፣ ትርሃስ. . .፤
ይልቁን ልምከርህ፣ ያገር ልጅ ወንድሜ፣
እኔስ ተስፋ አልቆርጥም፣ አሁንም ደግሜ፤
የቁማር ገድ-አልባ፣ የዘረኞች “አኪር”፣
ያለፈባት ካርታ፣ የነተበች “ጆከር”. . .
መምዘዙን አቁመህ፣
መስሎህም ከሆነ፣ ባገር የተጠላህ፣
ዘለህ የሕዝብ ስም ማንጠልጠሉን ትተህ፣
ራስህን ቻልና፣ ጠመንጃህን ጥለህ፣
“እኔን ትጠላለህ?” በልና ጠይቀው፣
ዞረህ ያገሬን ሰው፤

ተጠልተህ ከሆነም. . .፣
“ለምን እጠላለሁ?” ብለህ ራስህን ጠይቅ፣
ከዚያም መለስ ብለህ፣ ከህሊናህ ታረቅ፤
ያኔ! ዙሪያህን ስትቃኝ፣ ውስጥህን ስትመረምር፣
ይከሰትልሃል፤ እውነተኛው ምስጢር!

እስኪ ምክር ስማ፣ አያዋጣም ከንቱ ይኼ ነውረኝነት፣
ልቦናህ እያወቀው፣ ለፍርፋሪ አድረህ፣ በእሳት አትጫወት፤
እየለበለበ፣ መልሶ አንተኑ፣ ሊያቃጥል በቀኑ፣
ፈጥነህ ልብ ግዛ፤ ከእኩይ መንፈስ ታቀብ፤ ሳይብስ ሰቀቀኑ!

ልምከርህ ደግሜ፤ ያገር-ልጅ ወገኔ!
መልካም በመከወን፣ ደፍረህ በመጠመቅ፣ በሕዝብ ፍቅር ጸበል፣
“ይጠሉኛል” ብለህ ራስህን ከማስጨነቅ፣ ህመም ተገላገል!!

መስከረም 2007 ዓ/ም
(ኦክቶበር 2014)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. dereje says

    October 14, 2014 01:43 pm at 1:43 pm

    ማር አይጣፍጣትም ለአህያ ለዶሮ
    ምክርም እንዲህ ነች ለደደብ ወያኔ ለልበ ድንቆሮ።
    ምን ያረጋል ወንድሜ ምክርህ ቆንጆ ነበር። ግን አሁን ኢትዮጵያን
    አንቀጥቅጦ ለሚገዛት ሻዕቢያ ይህ አባባልህ ፍፁም
    አይገባውም።ያ ሁሉ ትግላችንንና ደማችን
    ህወሀት ለሻዕቢያ እንደዋዛ እንደሸጠው ደስ በሚለው
    መጣጥፍህ ለየዋሁና ለምስኪኑ የትግራይ ህዝብ ግለፅልኝ።
    መርሻ ዘ ዐዲግራት።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule