• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ትግሬ ትጠላለህ”

October 7, 2014 12:39 am by Editor 1 Comment

. . . ነፍሱን አይማርና! ያ! ቀጣፊ ከንቱ – የሂትለሩ ጉብልስ፣
አሳልፎ ሄደ፤ መሰሪ ትምህርቱን – ለበረከትና…ለነ አቶ ሽመልስ፤
እነሱም በተራ፣ ለታችኛው አሽከር ነጭ ውሸቱን ዘርተው፣
አጨዱት. . .፣ ከመሩት. . .፣ ማተብ-አልባ አድርገው፤
ከወያኔ ካድሬ፣ የውሸት ፋብሪካ፣ ተመርታ የወጣች፣
የዘረኞች ቋንቋ፣ “ትግሬ ትጠላለህ” የሚሏት ቃል አለች፤
ያገር ወዳዶችን ተቃውሞ ማስቆሚያ፣
በይሉኝታ ገመድ ሸብቦ ማሰሪያ. . .፣
ሆና ታገለግል ዘንዳ የተቃኘች፣
የጥላቻ ዜማ፣ ለጆሮ እምትቀፍ፣ ጩኸት የቁራዎች።

. . . እዩትማ እንግዲህ፣ ወደ ውስጥ ሲሰምጥ፣
መብሰሉን ሲያቅተው፣ ሲላወስ እንደ ሊጥ፣
ራሱ በፈጠረው፣ ራሱን አስጨንቆ፣ ጭቃ ሲንከባለል፣
እኩዮቹን ክዶ፣ ራሱን አሳንሶ፣ ሚጢጢዋን ሲያክል፤
ስልጣኑ አስክሮት፣ የግፍ ሃብት ቆዝሮት፣
ንቀት አሳውሮት፣ ህሊናውን ደፍኖት. . .፣
ደግሞ ከእሱ ብሶ፣ “ጅራፍ ገርፎ ሲጮኽ. . .፡
ይለኛላ እኔኑ፣ “ትግሬ ትጠላለህ”¡

. . .ንገረኝ ካልክማ፣ አንተ ነህ ጥላቻ፣ የጥላቻ ምንጩ፣ ህዝብ የምትጠላ፣
የይሉኝታ ደሃ፣ ምግባረ-ብልሹ፣ የዘመን አሽክላ!
አይገባህም እንጂ፣ ለመቻቻል ብሂል ስንት ዋጋ ከፈልኩ፣
ይኸው አንተን እንኳን፣ ሁለት አስርት ታገስኩ፤
ከያዘህ አባዜ ብትላቀቅ ብዬ፣
ታጥቦ ጭቃነትህን ሲያውቀው ልቦናዬ፤

እኔማ እንዴት ልጥላ! አብሮ አደጎቼን፣
እህት ወንድሞቼን፣ እናት አባቶቼን፣ ዘመድ ስጋዎቼን፣
ወዳጅ ጎረቤቴን. . . የሃገሬን ልጆች፣
የአጥንቴን ክፋይ፣ የደሜን ቅጅዎች፤
እንዴት ብዬ ልጥላ?!

. . . ይጠየቃ አክሱም፣ የቆመው ሐውልቱ፣
የዘመናት ታሪክ፣ ስረ-መሰረቱ፤
ትጠየቅ እምዬ፣ ወላዲት ማሪያሟ፣
የጽላተ-ሙሴ፣ ማደሪያ ጽዮኗ፤
ትጠየቅ ማይጨው፣ ትመስክር አድዋ፣ የታሪክ ማማዋ፣
ያያቶቼ. . . አጥንት ታዛ ከለላዋ፤
ካሻህም ላስመስክር፣ የሰው እማኝ ልጥራ፣ ለማተብ የቆሙ፣
ከዘመናት ታሪክ..እስካለንበቱ . . . በክብር የታደሙ፤
ሲዘከር፣ ሲተረክ፣ ሲጠራ፣ ሲወሳ . . . ዝነኛ ስማቸው፣
ምንኛ እንደምከንፍ፣ ለወገን ፍቅራቸው!
. . . አሉላ፣ ዮሃንስ፣ ዘርዓይ፣ አብርሃ፣ አውዓሎም፣ ሐጎስ፣
ገ/ሕይወት፣ አስገዶም፣ ባህታ፣ አሰገድ፣ ገ/መድኅን፣ ኪሮስ፣
ጋይም፣ አረጋዊ፣ ዘርዑ፣ ደበሳይ. . .፣
አቤሰሎም፣ አርዓያ፣ ግደይ፣ ገብረ-ተንሣይ. . .፤
አደይ፣ አታክልቲ፣ ጸሐይቱ፣ ሐዳስ. . .፣
ጽዮን፣ ትብለጽ፣ ምጽላል፣ አብርኸት፣ ትርሃስ. . .፤
ይልቁን ልምከርህ፣ ያገር ልጅ ወንድሜ፣
እኔስ ተስፋ አልቆርጥም፣ አሁንም ደግሜ፤
የቁማር ገድ-አልባ፣ የዘረኞች “አኪር”፣
ያለፈባት ካርታ፣ የነተበች “ጆከር”. . .
መምዘዙን አቁመህ፣
መስሎህም ከሆነ፣ ባገር የተጠላህ፣
ዘለህ የሕዝብ ስም ማንጠልጠሉን ትተህ፣
ራስህን ቻልና፣ ጠመንጃህን ጥለህ፣
“እኔን ትጠላለህ?” በልና ጠይቀው፣
ዞረህ ያገሬን ሰው፤

ተጠልተህ ከሆነም. . .፣
“ለምን እጠላለሁ?” ብለህ ራስህን ጠይቅ፣
ከዚያም መለስ ብለህ፣ ከህሊናህ ታረቅ፤
ያኔ! ዙሪያህን ስትቃኝ፣ ውስጥህን ስትመረምር፣
ይከሰትልሃል፤ እውነተኛው ምስጢር!

እስኪ ምክር ስማ፣ አያዋጣም ከንቱ ይኼ ነውረኝነት፣
ልቦናህ እያወቀው፣ ለፍርፋሪ አድረህ፣ በእሳት አትጫወት፤
እየለበለበ፣ መልሶ አንተኑ፣ ሊያቃጥል በቀኑ፣
ፈጥነህ ልብ ግዛ፤ ከእኩይ መንፈስ ታቀብ፤ ሳይብስ ሰቀቀኑ!

ልምከርህ ደግሜ፤ ያገር-ልጅ ወገኔ!
መልካም በመከወን፣ ደፍረህ በመጠመቅ፣ በሕዝብ ፍቅር ጸበል፣
“ይጠሉኛል” ብለህ ራስህን ከማስጨነቅ፣ ህመም ተገላገል!!

መስከረም 2007 ዓ/ም
(ኦክቶበር 2014)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. dereje says

    October 14, 2014 01:43 pm at 1:43 pm

    ማር አይጣፍጣትም ለአህያ ለዶሮ
    ምክርም እንዲህ ነች ለደደብ ወያኔ ለልበ ድንቆሮ።
    ምን ያረጋል ወንድሜ ምክርህ ቆንጆ ነበር። ግን አሁን ኢትዮጵያን
    አንቀጥቅጦ ለሚገዛት ሻዕቢያ ይህ አባባልህ ፍፁም
    አይገባውም።ያ ሁሉ ትግላችንንና ደማችን
    ህወሀት ለሻዕቢያ እንደዋዛ እንደሸጠው ደስ በሚለው
    መጣጥፍህ ለየዋሁና ለምስኪኑ የትግራይ ህዝብ ግለፅልኝ።
    መርሻ ዘ ዐዲግራት።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am
  • የኦነግ ሸኔ አባላትን ዕድሜ ለማሳጠር የጂፒኤስ ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ እየዋለ ነው December 7, 2020 12:38 am
  • የቆሰሉ ወታደሮች በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተጎበኙ December 6, 2020 11:41 pm
  • “ከዚህ በኋላ ይዘን እንታገላለን እንጂ ሠጥተን አንጠይቅም” ኮሎኔል ደመቀ December 2, 2020 12:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule