• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኢትዮጵያ ማሕበረሰብ ስብስብ በሰሜን ካሊፎርኒያ

July 18, 2016 05:44 am by Editor 1 Comment

የኢትዮጵያ ሕዝብ በአሸባሪውና በፋሽስቱ ወያኔ ቁጥጥር ሥር ወድቆ 25 የመከራና የፍዳ ዓመታትን አሳልፎ 26ኛውን ጀምሮዋል:: በዚህ ረጅም የመከራ ዓመታት አንድም ቀን ወያኔን ከመታገል የተቆጠበበት ጊዜ ግን አልነበረም:: ወያኔም ባደራጀው የመጨቆኛ መሳሪያው: በወታደሩ: በስለላ መረቡ እና በመሳሰሉት የዘረኝነት አገዛዙን ለማራዘምና ኢትዮጵያን የማጥፋት ተልኮውን ከፍጻሜ ለማድረስ ከዚያም የኔ የሚለው አዲስ አገር ለመመስረት ባለው እቅድ ሕዝባችን በዘርና በሃይማኖት ከፋፍሎ እርስ በርሳችን ለማባላት ያደረገው ሙከራ በሕዝባችን እምቢተኝነትና አገር ፍቅር ከመከፋፈል ይልቅ አንድነትን በመምርጡ ያቀደውን ከግብ ለማድረስ ቀላል አልሆነለትም::  ይህን ተልኮውን ከግብ ለማድርስ መጀመሪያ ዓማራውን ለይቶ በሌሎች ጎሳወች ለማጥቃት ሞከረ: አልሆን ሲለው ደረጃ በደረጃ ወደሌሎች ጎሳወችም ፊቱን አዞረ:: በመሆኑም ኦሮሞውን: አፋሩን: ሱማሌውን: ጋምቤላውን ወዘተ ማጥቃቱን ቀጠለ:: በእያንዳንዱ ጎሳ ላይ ያደረሰውን ግፍና በደል ከዚህ ላይ መዘርዘሩ ለቀባሪ ማርዳት ስለሚሆን እናልፈዋለን:: አንድ ነገር ሳንጠቅሰው ማለፍ የማንፈልገው ነገር: ባለፉት ሳምንታት በአዲስ አበባ መኖሪያ ቤታቸውን በላያቸው ላይ ያፈረሰባቸውን ወገኖቻችንን ነው:: መንግሥት በሕዝብ ተጠያቂ በሆነበት አገር: ክረምትና ብርድ ሲመጣ መንግሥት ቤት ለሌላቸውና በጎዳና ለሚያድሩ ጊዜአዊም ቢሆን መጠለያ አዘጋጅቶ ያስጠልላል:: ወያኔ ግን በክረምት ቤት ያላቸውን ሰዎች ቤታቸውን በላያቸው ላይ አፍርሶ ባልቴቶችን: አዛውንቶችን: ህፃናትንና ገና ሳምንት ያልሞላቸውን ጨቅሎችን ለዝናብና ለብርድ አጋልጦአቸዋል:: ይህን አይነት ጭካኔ ለመግለጥ ቃል ወይም ቃላት ፈልገን ለማግኝት አልቻልነም::

በአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ስም አርሶ አደር ወገኖቻችን አፈናቅሎ መሬታቸውን ለመዝረፍ ሲዘጋጅ የወላጆቻቸውን መሬት መነጠቅ በሰላማዊ መንገድ የተቃወሙ ወጣቶችን በጭካኔ ገደለ አሰረ አሰደደ:: ወያኔ ገና ሲጀምር ኢትዮጵያን አጥፍቶ አዲስ አገር ለመመስርት በነደፈው እቅድ መሰረት አዲስ አበባን በተቆጣጠረ ማግስት ከጎንደርና ከወሎ ለምና ሰፊ መሬት ወደትግራይ ከለለ:: የአካባቢውን ነዋሪና ተወላጅ የሆኑትን የወልቃይት: የጠገዴና የጠለምት ዓማራወችን ብትፈልጉ ትግሬነትንና የእኛን የበላይነት ተቀብላችሁ ኑሩ ካልሆነ መሬቱን እንጅ እናንተን አንፈልጋችሁም በማለት የዘር ማጥፋትና ማጽዳት ዘመቻውን ቀጠለ:: የነዚህ ወረዳወች ነዋሪ የሆኑት ዓማራወችም ማንነታቸውን ለማስከበር መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አቁዋቁመው ራሱ ወያኔ ህገመንግስቴ በሚለው መንገድና ህጉን ተከትለው  ያደረጉትን ሙከራ እንደድፍረት በመቁጠር: የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላትን ጎንደር ከተማ በሌሊት መጥቶ በማፈን: የገደለውን እየገደለ የያዘውንም እየያዘ ባለበት ጭቆናውና ግፉ ያንገፈገፈው የጎንደር ከተማና የአካባቢው ሕዝብ ሆ ብሎ ወጥቶ ወያኔን በመፋለም ላይ ይገኛል:: ወያኔም እንደለመደው ያለርህራሄ እየገደለ ነው ለመግደልም ተዘጋጅቶአል::

እኛ የኢትዮጵያ ማሕበረሰብ ስብስብ በሰሜን ካሊፎርኒያ (ESNNC) አባላት የኢትዮጵያ ሕዝብ በጠቅላላ በተለይም ባሁኑ ጊዜ የጎንደር ሕዝብ ለዲሞክራሲያዊ መብቱና እንደሕዝብ ለመኖር ዋስትናው እያደረገ ያለውን ፍትሃዊ ትግል ሙሉ በሙሉ እንደግፋለን:: በምንችለው ሁሉ እገዛ ለማድረግም ዝግጁ ነን:: ቃልም እንገባለን:: ሌላውም ወገንና አገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ ሁሉ አሁኑኑ ድጋፍና ትብብር እንዲያደርግ ጥሪአችን እናስተላልፋለን::

የኢትዮጵያ ሕዝብ በትግሉ መብቱን ያስክብራል ነፃነቱንም ይቀዳጃል!!

ETHIOPIAN SOCIETY NETWORK IN NORTH CALIFORNIA (ESNNC)
P.O. Box 612956
San Jose, CA. 95161
ethiopiansociety1@gmail.com

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. gud says

    July 23, 2016 04:43 pm at 4:43 pm

    Even failure has a name( check the Title $

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule