• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኢትዮጵያ ሃገራዊ ንቅናቄ ተመሠረተ

November 1, 2016 12:04 am by Editor Leave a Comment

የኢትዮጵያ ሃገራዊ ንቅናቄ በሚል ስም የሚጠራ የፖለቲካ ድርጅት ዕሁድ ዋሺንግተን ዲ.ሲ. ላይ በተፈረመ ስምምነት መቋቋሙ ተገለፀ፡፡

ድርጅቱን የመሠረቱት አርበኞች ግንቦት ሰባት፣ የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግንባር፣ የአፋር ሕዝብ ፓርቲና የሲዳማ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ መሆናቸውን አደራዳሪና አፈራራሚ ከነበሩት መካከል አንዱ የሆኑት በኢሊኖይ ቺካጎ የኢኮኖሚክስ ፕሮፌሰር ዶ/ር ጌታቸው በጋሻው ለአሜሪካ ድምፅ በሰጡት ማብራሪያ ገልፀዋል፡፡

የንቅናቄው ዓላማ የግዛት አንድነቷ የተጠበቀ፣ ዴሞክራሲያዊ የሕዝብ መብቶች የተከበሩባት፣ የፖለቲካ ሥልጣን ከላይ እስከታች በተዋረድ ያሉትና በምርጫ የሚጨበጥ ሥልጣን የሚኖራትን ፌደላዊት ኢትዮጵያን መመሥረት መሆኑን ዶ/ር ጌታቸው ገልፀዋል፡፡

የትግላቸው ግብ የሽግግር መንግሥት እንዲቋቋም፤ አዲስ ሕገመንግሥት እንዲቀረፅና ሁሉም ዜጋ እኩል የሆነባት ፌደራል ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መፍጠር መሆኑንም አደራዳሪው አስታውቀዋል፡፡

ንቅናቄው አኀዳዊ ፓርቲ እንዳልሆነ የገለፁት የምሥረታው ሂደት አመቻች ከሁሉም አባል ድርጅቶች የተውጣጣ የወኪሎች ምክር ቤት፣ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴና የአማካሪዎች ምክር ቤት የሚኖረው አባላቱ በተናጠል የሚያደርጓቸው እንቅስቃሴዎች እንደተጠበቁ ሆነው በአንድ አመራር ሥር የሚንቀሣቀሱበት መሆኑንም አመልክተዋል፡፡

የትግላቸው ሥልት ለሰላማዊ የሕዝብ እምቢተኝነት መሥራት መሆኑን ዶ/ር ጌታቸው ገልፀው ሁሉም ድርጅቶች ግን የየራሣቸውን የትግል ሥልት መከተል እንደሚችሉ ተናግረዋል፡፡

የንቅናቄው መሪዎች እንዲሆኑ የተመረጡት አቶ ሌንጮ ለታ፣ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋና ዶ/ር ዲማ ኖጎ መሆናቸውንም ዶ/ር ጌታቸው አክለው አመልክተዋል፡፡

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል እዚህ ላይ ያዳምጡ፡፡

(ምንጭ: የአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የሲኖዶሱ ውዝግብ አካሄድና መጪው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ February 6, 2023 02:03 am
  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule